TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፎቶ🔝ርዕሰ መስተዳድር #ገዱ_አንዳርጋቸው እና ርዕሰ መስተዳድር #ለማ_መገርሳ በኔዘርላንድ በሚገኙ ኩባንያዎች ያደረጉት ጉብኝት።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ሴክተሮች የ6 ወራት አፈፃፀም ግምገማ በአዲስ አበባ በኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት እየተካሄደ ነው። ግምገማው በግብርና፣ መሰረተ ልማትና የከተማ ልማት ላይ ትኩረት ያደርጋል፡፡ በግምገማው መድረክ ላይ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ #ለማ_መገርሳ፣ ምክትል ፕሬዝዳንት ወ/ሮ #ጠይባ_ሀሰን እና የሴክተር ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዳማ🔝

ለ7ኛ ጊዜ የሚከበረውን የመከላከያ ሰራዊትን ቀንን አስመልክቶ ህዝባዊ ውይይት በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው። በዚህ ውይይት የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር #አይሻ_መሀመድ ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ለማ_መገርሳ ፣ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል #ሰዓረ_መኮንንን ጨምሮ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች፣ ሚኒስትሮችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዳማ🔝

7ኛው የመከላከያ ሰራዊትን ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ በአዳማ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። በዓሉ ” ህገ መንግስታዊ ታማኝነታችንና ህዝባዊ ባህሪያችን ጠብቀን የተጀመረው ሀገራዊ ለውጥ እናስቀጥላለን ” በሚል መሪ ቃል ነው በሀገር አቀፍ ደረጃ በመከበር ላይ ያለው። በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም እየተከበረ ባለው የመከላከያ ሰራዊት ቀን ላይም የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ፣ የኦሮሚያ ክልል ርእስ መስተዳድር አቶ #ለማ_መገርሳ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር #አይሻ_መሀመድ፣ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል #ሰዓረ_መኮንን ጨምሮ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች፣ ሚኒስትሮችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምዕራብ ወለጋ🔝

ጠ/ሚር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ ከኦሮምያ ርዕሰ መስተዳድር #ለማ_መገርሳ ጋር በመሆን በምዕራብ ወለጋ የቄለም ወለጋ ዞን ካሉ ወረዳዎች አንዷ የሆነችው ቤጊ ወረዳ የማኅበረሰብ አባላት ጋር ውይይት እያደረጉ ነው።

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Fake FB Page‼️

"Lemma Megersa" በሚል ስም የተከፈተ ከ150,000 በላይ ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገፅ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት ክቡር አቶ #ለማ_መገርሳ ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ አይደለም። በገፁ ላይ የሚተላለፉት መልዕክቶችም የክቡር ፕሬዘዳንቱን አቋም የሚገልፁ እንዳልሆነ #ሊታወቅ ይገባል።

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በምዕራብ ኦሮሚያ በነበረው #ሁከት ተሳትፈዋል የተባሉ የመንግስት አመራሮች እየተመረመሩ ነው!
.
.
.
በምዕራብ ኦሮሚያ ዞኖች ባለፉት ወራት በነበረው የፀጥታ ቀውስ ሀላፊነታቸውን አልተወጡም ተሳትፎም አድርገዋል ተብለው የተጠረጠሩ አንድ መቶ ያህል የክልሉ አመራሮችና የፀጥታ አካላት ላይ ምርመራ እየተካሄደ ሲሆን ስምንት መቶ የሚጠጉ ፖሊሶችም ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ ነው።

ባለፉት ወራት የምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ ፤ ሆሮ ጉዱሩ እና ቄለም አካባቢዎች በኦሮሞ ነፃነት ግንባር ታጣቂዎችና በመንግስት የፀጥታ ሀይሎች መካከል ከፍተኛ ግጭት እንደነበረ ይታወሳል። በዚህ ግጭት ደግሞ የዞኑ አመራሮችን ከመግደል እስከ ባንኮች ዘረፋ የሚደርስ ሰፊ ወንጀል መፈጸሙ በክልሉ መንግስት መግለጫ የተሰጠበት እንደነበርም አይዘነጋም፡፡በተለይ አባቶርቤ ተብሎ የሚጠረ ህቡዕ ቡድን የተለያዩ ግለሰቦችን በመግደል ድርጊት ተሰማርቶ እንደነበርም መንግስት ራሱ ይፋ አድርጓል።

አሁን አካባቢው ላይ በኦሮሞ ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) እና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መካከል የተፈጸመውን እርቅ ተከትሎ አንጻራዊ ሰላም የወረደ መስሏል፡፡ ሁለቱን ወገኖች በማሸማገል ስራ ላይ የነበሩት አባ ገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎችም( እናቶች) ውጥረት እና ግጭት ሲንጣቸው በነበሩ ዞኖች ተንቀሳቅሰው ባሳለፍነው ሳምንት ሁኔታውን መቃኘታቸው ይታወቃል፡፡ ታጥቀው የነበሩ የኦነግ አባላትንም ትጥቅ በማስፈታት ወደተዘጋጀላቸው ካምፕ እንዲገቡ እየተደረገ ነው። ከሁሉም በላይ ግን የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እና የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ #ለማ_መገርሳ አካባቢው ድረስ በመጓዝ ያደረጉት ጉብኝት እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር የነበራቸው ውይይት ይበልጥ በስፍራው የሰላም አየር መንፈስ መጀመሩን ለማመላከት የታሰበ ይመስላል፡፡

አሁን ይህ ውጤት ይገኝ እንጂ ለወራት የተስተዋለውን ግጭት ያባባሰው እና ለቁጥጥር አዳጋች ያደረገው ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ የክልሉ የጸጥታ አካላት #በሁከቱ መሳተፋቸው መሆኑን ዋዜማ ሬድዮ መረጃ አግኝቻለሁ ብሏል፡፡ በተለይ አባቶርቤ ተብሎ ሲንቀሳቀስ በነበረው የህቡዕ ቡድን ውስጥም ሆነ አከባቢው ላይ በነበረው ሁከት የቀጥታ ተሳትፎ ነበራቸው ተብለው የተጠረጠሩ ከ800 በላይ የኦሮሚያ ክልል የፖሊስ አባላት በአሁኑ ወቅት አምቦ በሚገኘው ሰንቀሌ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የተሃድሶ ስልጠና እየተሰጣቸው እንደሚገኝም ጭምር ነው ራድዮ ጣቢያው አረጋግጫለሁ ብሎ የዘገበው፡፡

ዋዜማ ራድዮ ከምንጮቼ ሰማሁ እንዳለው ይበልጥ #ሁከቱን_በመምራት በማደራጀትና በማስተባበር #አባቶርቤ በተሰኘው ቡድን ውስጥም በቀጥታ በመሳተፍ ደግሞ በ100 ግለሰቦች ላይ ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል፡፡ ከነዚህ መካከልም #የዞን_አመራሮች እና #በፖሊስ_አመራርነት ደረጃ የሚገኙ መኖራቸው ጭምርም ታውቋል፡፡

አካባቢውን ያረጋጋሉ ተብለው ከአዲስ አበባ የተላኩት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አመራርም #ተጠርጥረው በምርመራ ላይ ናቸው፡፡

ምንጭ፦ ዋዜማ ራዲዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ #ለማ_መገርሳ በለገጣፎ ቤት የማፍረሱ እንቅስቃሴ እንዲቆም አዘዋል። ከነዋሪዎቹ ጋርም ውይይት ለማድረግ ቀጠሮ ይዘዋል።" (በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ)
.
.
አቶ #አዲሱ_አረጋ፦ "እኔ ከአቶ #ለማ እንዲህ አይነት ትእዛዝ እንደተላለፈ #አላውቅም። የህግ ማስከበሩ ተግባር #እንደቀጠለ ግን አውቃለሁ።"

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት(አቶ አዲሱ አረጋን በስልክ ጠይቆ የተሰጠው ምላሽ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለገጣፎ ለገዳዲ‼️

(አቶ አዲሱ አረጋ)

ሰሞኑን በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ ህገ ወጥ ግንባታዎች ላይ ህግን ለማስከበር በተደረገ እንቅስቃሴ በመንግስት ይዞታ ስር ባሉ በትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ፣ በአረንጓዴ ቦታዎች፣ በወንዝ ዳር እና የመሰረተ ልማት መገንቢያ ቦታዎች ላይ የተገነቡ እና ከከተማዉ የመሬት አጠቃቃም ፕላን ጋር የሚቃረኑ 347 ቤቶች እና በአጥር የተከለሉ ቦታዎች ላይ እርምጃ መወሰዱ ይታወቃል። የተወሰደዉን እርምጃ ተከትሎ ሰፊ #ቅሬታ በመቅረብ ላይ ይገኛል፡፡

ህገ ወጥነት መከላከል #ለድርድር የማይቀርብ ጉዳይ ባይሆንም በአፈጻጸሙ ሂደት የተፈጠሩ #ግድፈቶች እና #ስህተቶች ካሉ ለይቶ ማረም አስፈላጊ በመሆኑ ይህንን ጉዳይ የሚያጣራ አንድ ግብረ ሀይል ተደራጅቶ ወደ አካባቢዉ እንዲሰማራ ክቡር ፕረዚዳንት #ለማ_መገርሳ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ በዚህም መሰረት ግብረሃይሉ በጥቂት ቀናት ዉስጥ ወደማጣራት ስራ የሚገባ ይሆናል፡፡ ግብረሃይሉ አጣርቶ በሚያቀርበዉ ሪፖርት መሰረትህገወጥ ግንባታን በማፍረስ ሂደት የተፈጸሙ ስህተቶች ካሉ ህግን ተከትለዉ የሚታረሙ ይሆናል።

ህገ ወጥ ግንባታ የፈረሰባቸዉ የደሃ ደሃ የሆኑ ወገኖቻችን ያለ #መጠለያ እንዳይቀሩ ግብረሃይሉ አጣርቶ በሚያቀርበዉ መሰረት ህግና ስርኣትን በተከተለ መንገድ በአጭር ጊዜ ዉስጥ መፍትሄ እንዲያገኙ ይደረጋል፡፡

የተወሰደዉ ዕርምጃ #አንድ_ብሄር ላይ ያተኮረ ጥቃት አስመስሎ በማህበራዊ ሚዲያ እና በሌሎች ሚዲያዎች እየቀረበ ያለዉ ዘገባ #ሀሰት መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

#Addisu_Arega_Kitessa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጨፌ ኦሮሚያ🔝

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት አቶ #ለማ_መገርሳ የ6 ወራት የስራ አፈጻጸምን ለጨፌ ኦሮሚያ ያቀረቡ ሲሆን፣ በሪፖርታቸው የመሬት ወረራና ሕግ ወጥ ግንባታን ለመከላከል ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው፣ ህዝቡ #የሕግ_የበላይነትን የማስከበር ሂደት ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ በክልሉ ተከስቶ የነበረውን የጸጥታ ችግር ለመፍታት ባለፉት 6 ወራት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አቶ ለማ ተናግረዋል፡፡

የክልሉ መንግስት #ሰላም_እንዲኖር እየሰራ ቢሆንም በክልሉ አንዳንድ አከባቢዎች የጸጥታ ችግሮች መከሰታቸውን የገለጹት አቶ ለማ፣ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ችግሩ እንዲከሰት ያደረጉ አካላትን ወደ ሕግ የማቅረብ ስራዎች እየተሰሩ ናቸው ብለዋል፡፡

በተለይ በጉጂና በምዕራብ ጉጂ ዞኖች የተከሰቱትን #የጸጥታ_ችግሮች በትዕግስትና በሳል አመራር በመስጠት ሁኔታው ወደ #ሰላም እንዲመጣ መደረጉን አቶ ለማ በሪፖርታቸው ገልጸዋል፡፡ ህዝቡ ከመጣው ለውጥ ተጠቃሚ እንዲሆን ለማድረግ ስራዎች መሰራታቸውንም አቶ ለማ ገልጸዋል፡፡ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት በተሰራው ስራ የተለያዩ ፓርቲዎች ወደ አገር ገብተው የፖለቲካ እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆናቸው በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

#OBNLive

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ህዝቡ አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳ ለማድረግ እየተፈፀሙ ያሉ ሴራዎችን መታገል አለበት"– የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት
.
.
የተለያዩ የአገሪቱ የፖለቲካ ጉዳዮችን ሌላ መልክ በመስጠት አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳና እርስ በእርሱ እንዲጋጭ ለማድረግ እየተፈፀሙ ያሉ ሴራዎችን መላው ህዝብ እንዲታገል የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ #ለማ_መገርሳ ጥሪ አቀረቡ።

የክልሉ ፕሬዚዳንት ጥሪውን ያቀረቡት በአዳማ ከተማ ዛሬ በተጀመረው 9ኛው የጨፌው ጉባኤ ላይ ከጨፌው አባላት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነው።

አባላቱ በክልሉ ሰላም፣ የህግ የበላይነትን ማስከበር፣ ህገ-ወጥነትን በመከላከል፣ ክልሉ በአዲስ አበባ ላይ ካለው ጥቅም ጋር የተያያዘ እና ሌሎች በርካታ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጥያቄ አንስተዋል።

የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ለማ በዚሁ ወቅት ህዝቡ ጠረፍ አካባቢ ይፈፀም የነበረውን የፖለቲካ #ሴራ ወደመሃል አገር ለማምጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት ሊገታ ይገባል ብለዋል።

ህገ-ወጥነትን ለመከላከል የሚወሰደውን እርምጃ እንደአብነት ያነሱት አቶ ለማ የህዝቡን ጥቅም ማእከል አድርጎ የሚሰራ አመራር እና ህዝቡ ሌሎች በሚቀርፁለት አጀንዳ መመራት እንደሌለበት አስገንዝበዋል።

እንዲያም ሆኖ “ህገ-ወጥ ቤቶች ሲገነቡ ቁጭ ብሎ የሚመለከት አመራር እያለ ቤት እንዲፈርስ መደረጉ በራሱ #ጥፋት ነው” ሲሉም ገልፀዋል።

የቀበሌና የጎጥ አመራር እንዲሁም የከተሞቹ ካቢኔዎች ቤቶቹ ሲገነቡ ያለእነርሱ እውቅና መገንባታቸው፤ ከዚህም አልፎ ግንባታዎቹን በእጅ አዙር ህጋዊ ሲያስደርጉ በመቆየታቸው ግንባር ቀደም ተጠያቂ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

ኦሮሞ እና ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ ያላቸውን ጥቅም አስመልክቶ በተነሳው ጥያቄ ላይ ማብራሪያ ሲሰጡም ለውጡን ለመቀልበስ በዳራ አገር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች አሁን በአዲስ አበባ ጉዳይ አንዱን በሌላው በማስነሳት እርስ በእርስ ለማበላላት የሚፈፅሙት ተግባር ስለሆነ ህዝቡ ጉዳዩን በጥንቃቄ ማየት እንዳለበት አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ ጉዳይ በታሪክና በህገ-መንግስቱ መሰረት በምክክርና ህግን በተከተለ ሁኔታ ብቻ የሚፈታ እንደሚሆነም ነው አቶ ለማ ያብራሩት።

የልማት ፕሮጀክቶች መጓተት ዋነኛው ምከንያቶች የፋይናንሰ ችግር፣ የተቋራጮች አቅም ማነስ እንደሆነም አነሰተዋል።

የእነዚህ ሁለት ችግሮች ውጤት ተደማምሮ በልማት ፕሮጀክቶቹ ላይ ጫና ማሳደሩን የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ለማ ተናግረዋል።

ከዚሀም በተጨማሪ የክልሉ መንግስት በሰላም ማስከበርና በተፈናቃዮች ጉዳይ ላይ መጠመዱ የልማት ፕሮጀክቶቹ ቁጥጥር እንዲላላ ማድረጉንም አንስተዋል።

በሰላም ማስፈን ተግባር ላይ የክልሉ መንግስት ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ጋር ሰላም ለማውረድ በትእግስት ያከናወነውን ተግባር እንደ ድል መቁጠር ይገባል ሲሉም ፕሬዚዳንቱ ገልፀዋል።

አስከ ነገ የሚቆየው ጉባኤው በአስፈጻሚ አካላት የተከናወኑ ስራዎችን ይገመገማሉ፣ አዋጆችን ይጸድቃል፤ ልዩ ልዩ ሹመቶችን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ህዝቡ አንዱ በሌላው ላይ #እንዲነሳ ለማድረግ እየተፈፀሙ ያሉ #ሴራዎችን መታገል አለበት" – የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት #ለማ_መገርሳ

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"አድዋ ላይ #የወደቅነው፤ ሶማሊያን ስንዋጋ #ደማችንን ያፈሰስነው ተከፍሎን አይደለም፤ ቅጥረኞች ሆነን አይደለም። የሞትነው ለአገራችን ነው፤ የሞትነው ለኢትዮጵያ ነው።" ኦቦ #ለማ_መገርሳ (የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሚኒሶታ🔝

ኢትዮጵያ በአሜሪካ ጆርጂያ ካለው ቆንስላ ጽ/ቤቷ በተጨማሪ 2ኛ ቆንስላ ጽህፈት ቤቷን በሚኒሶታ መክፈቷን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል፡፡

ቆንስላ ጽ/ቤቱ የተከፈተው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አምና ነሃሴ ወር ላይ በአሜሪካ ባደረጉት ጉብኝት በገቡት ቃል መሰረት ነው።

በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ #ለማ_መገርሳ እንዳሉት የቆንስላ ጽ/ቤቱ መከፈት ለአካባቢው ብሎም በመላው አሜሪካ የሚኖረውን ዳያስፖራ ለማገልግል የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል።

ዳያስፖራው በኢትዮጵያ እየተካሄደ ባለው የኢኮኖሚና ፖለቲካ ለውጥ የበኩሉን ሚና እንዲወጣ የተናገሩት አቶ ለማ፤ ለዚህም መንግስት ከምን ጊዜውም በላይ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።

አዲስ የተከፈተው ቆንስላ ጽ/ቤት ቆንሱል ጄኔራል አምባሳደር እውነቱ ብላታ በበኩላቸው የጽ/ቤቱ መከፈት በሚኒሶታ ለሚኖሩ በሺዎች ለሚቆጠሩ የዳያስፖራ አባላት ምቹ ሁኔታና መነቃቃትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

የሴይንት ፖል ከተማ ከንቲባ ማልቪን ካርተር በዚሁ ወቅት ሲናገሩ ከቆንስላ ጽ/ቤቱ ጋር ተቀራርቦ ለመስራትና አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። ማርች 2 ቀን በከተማ ደረጃ “የኢትዮጵያ ቀን” ተብሎ እንዲከበርም መወሰኑን ጠቁመዋል።

በመርዓ-ግብሩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዴኤታ ብርቱካን አያኖን ጨምሮ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ከቤተ መንግስት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም በርካታ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የዳያስፖራ አባላት ተገኝተዋል።

ምንጭ፦ የወጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቱ🔝

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ ከኦሮሚያ ክልል ዋና አስተዳዳሪ አቶ #ለማ_መገርሳ ጋር በመሆን ከኢሉባቡር ዞን ነዋሪዎች ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቱ🔝

በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ እና በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝደንት አቶ #ለማ_መገርሳ የተመራውና መቱ ከተማን በመጎብኘት ላይ የሚገኘው ልኡክ በከተማው ወደ 66 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ በ3ሺህ 2 መቶ ሔክታር መሬት ላይ ለሚገነባው የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ማዕከል መቱ ቅርንጫፍ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጧል። ልዑኩ በማረሚያ ቤት የተገነባውን የመዝናኛ ማዕከልን በመጎብኘት የመቱ ዩንቨርስቲ መንገድ ፕሮጀክት የመረቀ ሲሆን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋርም ተወያይቷል።

Via waltainfo.com
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር አብይና አቶ ለማ🚁በደሌ🔝

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድና የኦሮሚያ ክልል ርእስ መስተዳድር አቶ #ለማ_መገርሳ ቡኖ በደሌ ዞን በደሌ ከተማ ናቸው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና የኦሮሚያ ክልል ርእስ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ ዛሬ ማለዳ ላይ ነው በደሌ ከተማ የገቡት።

በበደሌ ከተማ በሚኖራቸው ቆይታም ከቡኖ በደሌ ዞን ከተውጣጡ የህብረተሰብ ተወካዮች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የሚወያዩ ይሆናል።

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮምያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ለማ_መገርሳ ለመከላከያ ሚንስትርነት በእጩነት ቀረቡ። #ebc

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ #ተሿሚ ሚኒስትሮች ቃለ መሃላ ፈጽመዋል!

--- አቶ #ለማ_መገርሳ - ሀገር መከላከያ ሚኒስትር
--- አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
--- ኢንጂነር #አይሻ_መሀመድ - የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር

@tsegabwolde @tikvahethiopia