TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Israel #Palestine

እስራኤል ለፍልሥጤም በቅርቡ ጊዜው የሚያበቃ አንድ ሚሊዮን ዶዝ ፋይዘር የኮቪድ-19 ክትባት ልትሰጥ ነው።

ዛሬ ይፋ በሆነው ስምምነት እስራኤል 1 ሚሊዮን የኮቪድ - 19 ክትባት ለፍልስጤም ትልካለች። ፍልስጤም በተመድ በሚደገፈው ፕሮግራም ክትባት ለሚያስፈልጋቸው ሀገራት ክትባት ሲላክላት አንድ ሚሊዮን ዶዝ ክትባቱን ለእስራኤል ትመልሳለች ተብሏል።

እስራኤል 85% ጎልማሳ ዜጎቿን የኮቪድ-19 ክትባት የከተበች ሲሆን በዌስት ባንክ እና ጋዛ ለሚገኙ 4.5 ሚሊዮን ፍልስጤማውያን ክትባት አላካፈለችም በሚል ስትተች ነበር።

ዛሬ ይፋ የሆነው ክትባት የመላክ ስምምነት በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናፍታሊ ቤንት በሚመራው መንግስት የተደረሰ እንደሆነ ተገልጿል ፤ እስካሁን ግን ከፍልስጤም ባለስልጣናት ምንም የተባለ ነገር የለም።

በዓለማችን ካሉ ሀገራት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በመከላከል ረገድ ከፍተኛ ስራ የሰራችው እስራኤል ዜጎቿን በመከተቡ ረገድም አመርቂ ስራን ሰርታለች ፤ በዚህ ሳምንት የሀገሪቱ ባለስልጣናት ቀሪ ነበር የተባለውን የመጨረሻ ገደብ በህዝብ መካከል ማስክ የማድረግ ገደብ እንዳነሱ ታውቋል።

@tikvahethiopia
#Seychelles #Palestine #Jordan

በኢትዮጵያ አዲስ የተሾሙት የጆርዳን፣ የሲሼልስ እና የፍልስጤም አምባሳደሮች በዛሬው ዕለት የሹመት ደብዳቤያቸውን ቅጂ አቅርበዋል።

አምባሳደሮቹ የደብዳቢያቸውን ቅጂ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ምክትል ሹም አምባሳደር አለማየሁ ሰዋገኝ ነው ያቀረቡት።

የአሁን የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተም ለአምባሳደሮቹ ገለፃ እንደተደረገለቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Palestine

ዛሬ አይርላንድ ፣ ኖርዌይ እንዲሁም ስፔን ለፍልስጤም የነጻ ሀገርነት እውቅና እንደሚሰጡ በይፋ አስታወቁ።

" የዛሬው ቀን ለፍልስጤም እጅግ ታሪካዊ ቀን ነው " ተብሏል።

የአየርላንድ ጠ/ሚኒስትር ሲሞን ሃሪስ " ዛሬ አየርላንድ ፣ ኖርዌይ እና ስፔን ለፍልስጤም የነጻ ሀገርነት እውቅና ሰጥተናል። ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ እያንዳንዳችን ማንኛውንም አይነት ብሔራዊ እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ ፥ " #በሚቀጥሉት_ሳምንታት ተጨማሪ ሀገራት ይህን ጠቃሚ እርምጃ ለመውሰድ ከእኛ ጋር እንደሚተባበሩ እርግጠኛ ነኝ " ሲሉ አክለዋል።

የአይርላንድ መንግሥት ይህ የሀገርነት እውቅና የሁለት ሀገር መፍትሄን እንደሚደግፍና ለቀጠናው ዘላቂ ሰላም አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል።

የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ እና የኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ኢስፔን ባርት ኢይድ ሀገራቸው ከግንቦት 28 (እ.ኤ.አ) ጀምሮ ለፍልስጤም ግዛት እውቅና እንደሚሰጡ በይፋ አሳውቀዋል።

የስፔኑ ጠ/ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ፥ " ምንም እንኳን ከአሸባሪው ቡድን #ሃማስ ጋር የሚደረገው ውጊያ ህጋዊ ቢሆንም ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ለፍልስጤም የሰላም ፕሮጀክት የላቸውም " ብለዋል።

የኖርዌይ ጠ/ ሚኒስትር ጆናስ ጋህር ስቶር በበኩላቸው ፥ " እውቅና ከሌለ (የፍልስጤም) በመካከለኛው ምስራቅ ምንም ሰላም ሊኖር አይችልም " ብለዋል።

" ሽብር የተፈፀመው በሃማስና የሁለት ሀገር መፍትሄን በማይቀበሉ እንዲሁም የእስራኤልን መንግሥት በማይደግፉ ታጣቂ ቡድኖች ነው። " ሲሉ አክለዋል።

" ፍልስጤም ነጻ አገር የመሆን መሠረታዊ መብት አላት " ብለዋል።

የፍልስጤም #የነጻ_ሀገርነት እውቅና መስጠት በይፋ ከተሰማ በኃላ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር #በኖርዌይ እና #በአይርላንድ የሚገኙ አምባሳደሮችን በአስቸኳይ ወደ እስራኤል እንዲመለሱ አዘዋል።

ሚኒስትሩ፤ " የዛሬው ውሳኔ ሽብርተኝነት እንደሚከፍል ለፍልስጤማውያን እና ለዓለም መልእክት ያስተላለፈ ነው " ብለዋል።

መረጃው የስካይ ኒውስ ነው።

More - @thiqahEth