TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ሁለቱም ወገኖች ሰላም፣ ጸጥታና የኢትዮጵያ መረጋጋት ምኞታቸው መሆኑን ገልፀውልኛል " - ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ

በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ የመንግስትን እና የህወሃትን አመራሮችን ማነጋገራቸውን ካስታወቁ በኋላ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ኦባሳንጆ ሁሉም ወገኖች ወታደራዊ ፍልሚያውን እንዲያቆሙ ጠይቀዋል፡፡

ከመንግስትም ሆነ ሽብርተኛ ተብሎ ከተፈረጀው ህወሃት በኩል የሰላም ፍላጎቶች መኖራቸውን የገለጹት ከፍተኛ ተወካዩ ‘የሰላም መንገዱ ምን ይሁን’ የሚለው ግን ልዩነታቸው እንደሆነ ጠቅሰዋል።

የአፍሪካ መሪዎችና ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ሕብረቱ የጀመረውን የማሸማገል ጥረት እንዲደፉ እና ግጭቱን ሊያባብሱ ከሚችሉ ነገሮች እንዲቆጠብም ኦባሳንጆ ጥሪ አቅርበዋል።

ኦባሳንጆ፥ "ሆን ተብሎም ይሁን ባለማወቅ ግጭቱን የሚባብሱና ወደከፋ ደረጃ ከሚያደርሱ ንግግሮች መቆጠብ ያስፈልጋል" ብለዋል ።

ኦባሳንጆ፤ ውጊያው ከቆመ የንግግር ዕድል እንደሚኖር የገለጹ ሲሆን አሁን ባለው ሁኔታ ውጊያ እየተደረገ ግን ለመነጋጋር የሚመች እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

ኦባሳንጆ ፥ የኦሮሚያ እና አማራ ክልል አመራሮችን ማግኘታቸውን በመግለጫቸው ላይ የገለፁ ሲሆን በቀጣይ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የአፋር ክልል አመራሮችን እንደሚያገኙ አሳውቀዋል።

ኦባሳንጂ ይህ የማሸማገል ስራ እንዲሳካ ቁርጠኛ እንደሆኑ የገለጹ ሲሆን ፦
- #የኬንያ
- #ኡጋንዳ
- #ጅቡቲ
- #ደቡብ_ሱዳን
- #ሶማሊያ እና ሱዳን መሪዎችን ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡

ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አስማሚ ሁኔታ ይፈጠራል ብዬ አስባለሁ ያሉት ኦባሳንጆ ሁለቱም ወገኖች ሰላም፣ ጸጥታና የኢትዮጵያ መረጋጋት ምኞታቸው መሆኑን እንደገለጹላቸው አሳውቀዋል።

Credit : #Al_AIN
Pic : AU

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በጎረቤታችን ሶማሊያ እየተካሄደ በሚገኘው ምርጫ የ2ኛው ዙር ድምፅ አሰጣጥ ሂደት አብቅቷል ፤ ይህን ተከትሎ የድምጽ ቆጠራው ይካሄዳል። #ማስታወሻ ፦ የመጀመሪያው ዙር ውጤት ፦ 👉 ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ➡️ 65 👉 ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 59 👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 52 👉 ሀሰን አሊ ኻይሬ ➡️ 47 @tikvahethiopia
#ሶማሊያ

እጅግ ከባድ ፉክክር እየታየበት በሚገኘው የሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ የሁለተኛው ዙር ድምፅ አሰጣጥ ተጠናቆ የድምፅ ቆጠራው እየተካሄደ ይገኛል።

የ2ኛው ዙር የምርጫ ውጤትን እንዲሁም አጠቃላይ የምርጫውን ሂደት ከሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እየተከታተል እንልክላችኃለን።

ቀጣዩ የጎረቤታችን ሶማሊያ ፕሬዜዳንት ማን ይሆን ? አብረን የምናየው ይሆናል።

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ 🌍

➡️ #ሶማሊያ ፦ በሶማሊያ እየተባባሰ ያለው የድርቅ ሁኔታ ለምግብ እጦት እና ለውሃ እጥረት የተጋለጠው ህዝብ ቁጥር 8 ሚሊየን ሊደርስ ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል። አሁን ላይ በሀገሪቱ ያለው ድርቅ በገጠር 66 ወረዳዎችና ሰፊ አካባቢዎች ክፉኛ መቷል።

➡️ #ዩክሬን ፦ ዩክሬን በጦርነቱ ምክንያት 243 ህጻናት መሞታቸውን እና 444 ህፃናት መቁሰላቸውን አረጋግጫለሁ ስትል አስታውቃለች።

➡️ #ግብፅ ፦ የግብፅ ፍርድ ቤት በቀድሞው የፕሬዚዳንት እጩ አብደል ሞኒም አቡል ፎቱህ እና በሙስሊም ወንድማማች ቡድን ውስጥ ያሉ ታዋቂ ግለሰቦችን " የሀሰት ዜና በማሰራጨት " እና መንግስትን ለመገልበጥ አሲረዋል በሚል በእስራት እንዲቀጡ ወስኗል። አቡል ፎቱህ 70 ዓመታቸው ሲሆን የ15 አመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፣ መሐመድ አል-ካሳስ የአቡል ፎቱህ " Strong Egypt Party " ምክትል ኃላፊ የ10 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፣ እንዲሁም የ15 አመት እስራት የተፈረደባቸው የወንድማማችነት የቀድሞ የበላይ መሪ ማህሙድ ኢዛት ሲሆኑ እሳቸው ቀደም ሲልም በሌሎች ክሶች የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው ነበር።

➡️ #ሱዳን ፦ የሱዳኑ ወታደራዊ መሪ ጄኔራል አብደል ፈታህ አል ቡርሃን ጥቅምት 25 የተደረገውን መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ ተጥሎ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መነሳቱን አሳውቀዋል። ቡርሃን " የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በአገር አቀፍ ደረጃ ተነስቷል " ብለዋል።

➡️ #ሩስያ ፦ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ የዩክሬን #ዶንባስ ግዛትን ነፃ ማውጣት ለሞስኮ ምንም ቅድመ ሁኔታ የሌለው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልፀው ሌሎች ግዛቶች የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን ለራሳቸው መወሰን አለባቸው ብለዋል።

#ቲአርቲ #AJ #ኤፒ #SNTV

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ ፦

#ካናዳ ፦ የካናዳው ጠ/ሚ ጀስቲን ትሩዶ አነስተኛ የእጅ ሽጉጥ መግዛትም ሆነ መታጠቅ እንዲከለከል ጠይቀዋል። የትሩዶ መንግሥት በጠቅላላው የእጅ ሽጉጥ መግዛት ሆነ ቤት ማስቀመጥ በሕግ እንዲያስቀጣ ረቂቅ እያወጣ ነው። ረቂቁ እንደሚለው ካናዳዊያን የእጅ ሽጉጦቻቸውን ባይነጠቁም ከዚህ በኋላ አዲስ መግዛት ግን አይችሉም። ትሩዶ ይህን ሐሳብ ያፈለቁት በአሜሪካዋ ቴክሳስ ግዛት አንድ አፍላ ታጣቂ 19 ሕፃናትን ተኩሶ ከገደለ በኋላ ነው።

➡️ #እስራኤል #UAE ፦ እስራኤል እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የነፃ ንግድ ስምምነት ተፈራርመዋል ፤ ይህ እስራኤል ከአረብ ሀገር ጋር ያደረገችው የመጀመሪው ትልቅ ስምምነት ነው።

➡️ #ሴኔጋል ፦ የሴኔጋል ፖሊስ በአንድ ሆስፒታል ውስጥ በደረሰው እና የ11 ህጻናት ህይወት ከቀጠፈው የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተሰምቷል።

➡️ #ሩስያ ፦ በያዝነው ዓመት 70ኛ ዓመታቸውን የሚደፍኑት የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጤና እክል ምናልባትም በካንሰር ህመም እየተሰቃዩ ሳይሆን አይቀርም የሚሉ ያልተረጋገጡ የመገናኛ ብዙኃን ሪፖርቶች እየወጡ ናቸው። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ግን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታመዋል መባሉን ሀሰት ሲሉ አስተባበሉ። ላቭሮቭ ፕሬዚዳንት ፑቲን በየቀኑ በአደባባይ እንደሚታዩ እና እንደማኛውም ጤነኛ ሰው የህመም ምልክት አያታይባቸውም ብለዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ የሶማሊያ ባይዶዋ ከተማ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ነች። ከተማዋ ፕሬዝዳንቱ ፈርማጆን አሸንፈው ዳግም የፕሬዜዳንትነት መንበሩን ከተረከቡ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚጎበኟት ከተማ ትሆናለች።

#ቢቢሲ #ቲአርቲ #ሲጂቲኤን #SNTV

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ 📣

➡️ #ካሜሮን፦ በካሜሩን መገንጠልን አላማቸው አድርገው ይንቀሳቀሳሉ የተባሉ ታጣቂዎች ናይጄሪያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ መንደር በፈጸሙት ጥቃት በትንሹ 20 ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል። ጥቃቱ ባሳለፍነው እሁድ በደ/ምዕራብ የካሜሩን ክፍል ኦቦኒ ሁለት በተሰኘ መንደር የተፈፀመ ሲሆን ከሞቱ ሰዎች ባሻገር ከ60 በላይ ሰዎች ቆስለዋል። ታጣቂዎቹ ነዋሪዎቹ በየወሩ ገንዘብ እንዲከፍሏቸው ይፈልጋሉ፤ ነዋሪዎቹ ደግሞ ፍቃደኛ አልሆኑም። ለዚህም ነው ጥቃት ያደረሱባቸው ተብሏል።

➡️ #ሜክሲኮ ፦ በደቡባዊ ሜክሲኮ በተፈጠረ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ በትንሹ 10 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የገቡበትን ማወቅ እንዳልተቻለ ተሰምቷል።

➡️ #ቻይና ፦ የሻንጋይ ነዋሪዎች ከሁለት ወር በኃላ የኮቪድ-19 የእንቅስቃሴ ገደብ መነሳቱን ተከትሎ ነፃ ሆነዋል። ነዋሪዎች ባለፉት 2 ወር ኮቪድ-19ኝን ለመከላከል በተጣለ የእንቅስቃሴ ገደብ ምክንያት ከእንቅስቃሴ ርቀው ቆይተዋል።

➡️ #ዩክሬን ፦ የየክሬን ኬርሰን ግዛት በሩስያ ቁጥጥር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ሁሉንም የግንኙነት መስመሮች እንዲዘጉ ማድረጋቸው ተነግሯል።

➡️ #አሜሪካ ፦ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ሀገራቸው ለዩክሬን 'ቁልፍ ኢላማዎችን' ለመምታት የሚያስችላትን እጅግ የዘመኑ ሮኬቶችን እንደምትልክ አሳውቀዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ ወደ ባይዶዋ እንደሚሄዱ የተነገረላቸው አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ፕሬዝዳንት ከሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ግዛት መሪ አብዲአዚዝ ሀሰን ሞሀመድ እና ከባህላዊ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ፕሬዜዳንቱ ወደ ባይዶዋ ያደረጉት ጉዞ ዳግም ፕሬዜዳንት ሆነው ከተመረጡ በኃላ የመጀመሪያቸው ነው።

#ቲአርቲ #ቢቢሲ #ፍራንስ24 #ሲጂቲኤን

@tikvahethiopia
#Somalia

አልሸባብ ዛሬ #ሶማሊያ ውስጥ ባደረሰው ጥቃት የሰዎች ህይወት ጠፋ።

በሽብር ቡድኑ በሶማሊያ ደቡባዊ አቅጣጫ በተለያዩ ቦታዎች በተፈፀሙ ሁለት የቦንብ ጥቃቶች በርካቶች ተገድለዋል።

በመጀመርያው ጥቃት ታችኛው ሸበሌ ክልል በአፍጎዬ ከተማ በእንስሳት የገበያ ቦታ በተወረወሩ 2 ቦምቦች በትንሹ 4 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን ተነግሯል።

ሁለተኛው ጥቃት ማርካ በተባለችው የወደብ ከተማ የተፈፀመ ሲሆን የወረዳው ኮሚሽነር አብዱላሂ አሊ ዋፎው በጥቃቱ መገደላቸው ተዘግቧል።

ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል።

የአካባቢው ፖሊስ እንዳስታወቀው ጥቃቱ የተፈፀመው የማርክ ወረዳ ኮሚሽነር በወረዳዉ ጽሕፈት ቤት ቅጥር ግቢ ዉስጥ ለተሰበሰቡ ነዋሪዎች ንግግር ሲያደርጉ ነው።

ንግግር ሲያደርጉ የነበሩት ኮሚሽነሩ አብዱላሒ ዓሊ አሕመድ ዋፎው እና ሌሎች ስምንት ተሰብሳቢዎች ወዲያዉ ሞተዋል።

ምንጭ፦ ሮይተርስ እና ዶቼ ቨለ

@tikvahethiopia
#ሶማሊያ

በጎረቤታችን ሶማሊያ " አልሸባብ " የሽብር ቡድን በፈፀመው ጥቃት በትንሹ 20 ሰዎች ሲገደሉ 7 ተሽከርካሪዎች በቡድኑ ተቃጥለዋል።

የሶማሊያ ብሄራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ ፤ ጨካኙ የሽብር ቡድን ትላንት ምሽት በሂራን ክልል 20 ሰዎችን ገድሎ ምግብና ሌሎች የንግድ ሸቀጦችን ጭነው ለማሃስ ወረዳ የአካባቢው ነዋሪዎች ይዘው ሲጓዙ የነበሩ 7 ተሽከርካሪዎችን አቃጥሏል ብሏል።

አንድ የአካባቢው ባለስልጣናት ደግሞ ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል  ፤ ጥቃቱ የተፈፀመው በክልሉ ዋና ከተማ በለድዋይ እና በማሃስ ወረዳ መካከል ባለው ጎዳና ላይ መሆኑን ገልፀው 22 ሰዎች መገደላቸውን አስረድተዋል።

ጥቃቱ የተፈፀመው ምግብ ጭኖ ይጓዝ በነበረ ልዑክ ላይ መሆኑን አመልክተው ቡድኑ 17 ሰዎች እዛው ገድሎ ተጎጆዎቹን ሊረዱ በመጡ ሲቪሎች እና ቆፋሪዎች ላይ በተቀበረ ፈንጂ በማነጣጠር 5 ሰዎችን ገድሏል ብለዋል።

አልሻባብ ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደ ሲሆን በጥቃቱ 20 የአካባቢውን ታጣቂዎች መግደሉን ገልጿል።

የሶማሊያ መንግስት ባወጣው መግለጫ ጥቃቱን አጥብቆ አውግዞ " አረመኔ እና አሳፋሪ " ሲል ገልጿል።

መንግስት ከአካባቢው ማኅበረሰብ ጎን እንደሚቆም ገልጾ ለደረሰው " አሰቃቂ " ጥቃት ጠንከር ያለ ምላሽ እንደሚሰጥ ቃል መግባቱን ቪኦኤ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ ኤርትራ ያሉ የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር አባላት ዛሬ በፎቶ ታይተዋል። አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሃሙድ ላለፉት 2 ዓመታት በኤርትራ ስልጠናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙትን የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር አባላትን ጎብኝተዋል። ፕሬዜዳንቱ ኤርትራ ያሉ የሶማሊያ ጦር አባላትን ከኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በመሆን ነው የጎበኙት ተብሏል። የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ከትላንት ጀምሮ በኤርትራ የስራ…
#ሶማሊያ #ኤርትራ

የ5 ሺህ የሶማሊያ ወታደሮች ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ፤ የሶማሊያ ወታደሮች ከኤርትራ ያልተመለሱበት ምክንያት ፤ ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሀገሪቱ ውስጥ (በሶማሊያ) ባለው የፖለቲካ ልዩነት ምክንያት ሊመልሷቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው መሆኑን ገልፀዋል።

ኤርትራ የሶማሊያን ኃይል በማሰልጠን ረገድ ጥሩ ሀሳብ እንዳላትም ፕሬዜዳንቱ ተናግረዋል።

ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ፤ ኤርትራ 5000 የሶማሊያ ወታደሮችን ማሰልጠን ብቻ ሳይሆን እያስታጠቀችም ነው ብለዋል።

የሶማሊያ መንግስት በኤርትራ የሰለጠኑ ወታደሮቹን ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ እየሰራ መሆኑን የገለፁት ፕሬዜዳንቱ ለዚህም የአሜሪካን ድጋፍ መጠየቁን (ወታደሮቹን ለመመለስ) አሳውቀዋል።

ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ በቅርቡ ወታደሮቹ እንደሚመለሱና ከአልሸባብ ጋር በሚደረገው ጦርነት የራሳቸውን አስተዋፆ እንደሚያበረክቱ " አረጋግጣለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።

በነገራችን ላይ የሶማሊያው ፕሬዜዳንት በአሁን ሰዓት አሜሪካ የሚገኙ ሲሆን ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር ጨምሮ ከሌሎች የአሜሪካ ባለስልጣናት እና የዓለም አቀት ተቋማት ኃላፊዎች ጋር በሀገራቸው ጉዳይ መክረዋል።

ከአንቶኒ ብሊንከን ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ በሶማሊያ ሽብርተኝነትን መዋጋት፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን እና ለድርቅ ምላሽ መስጠት ላይ መስማማታቸውን ገልፀዋል። አሜሪካ በሶማሊያ የዘላቂ ልማት እና እድገት ስትራቴጂክ አጋር መሆኗንም ገልጸዋል።

መረጃ ምንጭ፦ የቪኦኤ ሶማሊኛ ክፍል ጋዜጠኛ ሀሩን ማሩፍ ፣ ቪላ ሶማሊያ እና የፕሬዜዳንቱ (ሀሰን ሼክ ሞሀመድ) ትዊተር ገፅ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሶማሊያ

በጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ለ13 ዓመታት አልሸባብ ሲቆጣጠረው የነበረው ዋና መንገድ ነፃ መደረጉ ተገለፀ።

ለ13 አመታት በአልሸባብ ቁጥጥር ስር የነበረው በሂራን ክልል ቡልቡርዴ እና በለድዌይን ወረዳዎች መካከል ያለው ዋና መንገድ የሶማሌ ብሄራዊ ጦር በአካባቢው ነዋሪዎች እገዛ ነፃ ማድረጉን አሳውቋል።

የፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሙሀሙድ አስተዳደር በአልሸባብ ይዞታዎች ላይ እያካሄደ ያለውን እጅግ መጠነ ሰፊ ዘመቻ አጠናክሮ መቀጠሉ የተገለፀ ሲሆን በተለይም በሂራን ክልል በርካታ ቦታዎችን ከአልሸባብ ነፃ ማድረግ ተችሏል።

በዚህ የፀረ ሽብር ዘመቻ ላይ አሜሪካም በአየር የአልሸባብ ይዞታዎችን በመደብደብ እገዛ እያደረገች መሆኑን ከሀገሪቱ መንግስት የወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።

የአፍሪካ ህብረት ኃይልም ለፀረ ሽብር ዘመቻው የአየር ድጋፍ እየሰጠ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ETHIOPIA🇪🇹

ከቀናት በፊት በጎረቤታችን #ሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ በ "አልሸባብ" በተፈፀመ የሽብር ጥቃት እጅግ በርካታ ሰዎች መሞታቸው እና መቁሰላቸው ይታወሳል።

በወቅቱ ፕ/ት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ፤ የተጎዱትን ለማከም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የህክምና ዶክተሮች እና የህክምና ቁሳቁሶችን እንዲልክ ተማፅነው እንደነበር አይዘነጋም።

ይህንን ጥሪ ተከትሎ የተለያዩ ሀገራት ዶክተሮችና የህክምና ቁሳቁሶችን እየላኩ ይገኛሉ።

ዛሬ ሀሙስ የሀገራችን #ኢትዮጵያ ዶክተሮች ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የሚደረገውን የአደጋ ጊዜ ምላሽ ለመቀላቀል ሞቃዲሾ ገብተዋል።

የኢትዮጵያ ዶክተሮች አዳን አብዱሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በሶማሊያ የጤና ሚኒስትር ዶክተር አሊ ሀጂ የተመራ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አቀባበል እንደተደረገላቸው ከሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#ሶማሊያ

ዛሬ ሶማሊያ ውስጥ ከሶማሊያ ጋር ጎረቤት የሆኑ ሀገራት መሪዎች በ " አልሸባብ " ጉዳይ ስብሰባ ያካሂዳሉ።

እንደ ሶማሊያ መንግስት መረጃ በስብሰባው የሶማሊያ፣ የኬንያ፣ የኢትዮጵያ፣ እና ጅቡቲ መሪዎች ይካፈላሉ።

የሶማሊያው ፕሬዜዳንት የሀሰን ሼክ ሙሀሙድ ይመሩታል በተባለው ስብሰባ የሀገራችን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድም እንደሚካፈሉ በሶማሊያ መንግስት በኩል ተገልጿል።

ለዛሬው ስብሰባ ዝግጅት ለማድረግ የሶማሊያ፣ የኢትዮጵያ፣ የኬንያ ፣ ጅቡቲ መከላከያ አመራሮች ሞቃዲሾ ይገኛሉ።

ሙቃዲሾ ለስብሰባው ሰላም እና ደህንነት ከፍተኛ የሆነ የፀጥታ ጥበቃ እያደረገች ትገኛለች ተብሏል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
#ሶማሊያ #ኢትዮጵያ #ኤርትራ

የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼይክ መሐሙድ " የሶማልያ እና የኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ስልታዊ አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ ነኝ " ሲሉ አሳውቀዋል።

ፕሬዝደንቱ ይህን የገለጹት ዛሬ በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሞሐመድ ዋሬ የሹመት ደብዳቤ በተቀበሉበት ወቅት እንደሆነ የሶማሊያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

ፕሬዝደንት ሐሰን ሼይክ መሐሙድ ዛሬ የአምባሳደሩን የሹመት ደብዳቤ የተቀበሉት ለሥራ ጉብኝት ከተጓዙበት አስመራ ወደ ሞቃዲሾ ከተመለሱ በኃላ ነው።

ፕሬዝደንቱ በአስመራ ከኤርትራው አቻቸው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ተገናኝተው መወያየታቸው ታውቋል።

ውይይቱ " የጋራ ጠቀሜታ ባላቸው የቀጠናዊ ጉዳዮች " ላይ እንደነበረ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል መናገራቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ወደ ስልጣን ከመጡ በኃላ ለስራ ጉብኝት ወደ ኤርትራ በተደጋጋሚ ጊዜ መጓዛቸው ይታወቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ቲክቶክ " ኬንያ ውስጥ እንዲታገድ አቤቱታ ቀረበ። የኬንያ ፓርላማ " #ቲክቶክ " የተሰኘው የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ እንዲያግድ አቤቱታ እንደቀረበለት የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። " ወጣቶች ትምህርታቸውን ትተው የ 'ቲክቶክ' ቁራኛና የአዕምሮ ህመምተኛ እየሆኑ ነው " የሚለው አቤቱታው ፓርላማው አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ ጠይቋል። የፓርላማው አፈጉባኤ ሞሰስ ዋታንጉላ፣ " ሁከትን እና የጥላቻ ንግግርን…
#ሶማሊያ

ሶማሊያ ቲክቶክ እና ቴሌግራም እንዲሁም 1ኤክስቤት (1XBet) የተባለውን የስፖርት ውርርድ ገጽን እንዲዘጉ አዘዘች።

" ቲክቶክ " እና " ቴሌግራም " የአሸባሪዎች መረጃ ማስተላለፊያ ሆነዋል ብሏል የሶማሊያ መንግሥት።

መተግበሪያዎቹ " አሸባሪ ድርጅቶች እና ቡድኖች አሰቃቂ የሆኑ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን እንዲሁም ፎቶግራፎችን በማሰራጨት ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ጥቅም ላይ ውለዋል " ሲል ገልጿል።

የሀገሪቱ መንግሥት የኢንተርኔት አግልግሎት አቅራቢዎች እስከ ሐሙስ ነሐሴ 18/2015 ዓ.ም. ድረስ  " እንዲዘጉ " የሚለውን ትዕዛዝ ተግባራዊ እንዲያደርጉ ፤ የማያደርጉ ከሆነ ግን ቅጣት እንደሚጠብቃቸው አስጠንቅቋል።

ይህ ውሳኔ የተሰማው የሶማሊያ መንግሥት አልሸባብን ለማጥፋት ዘመቻ ከጀመረ በኃላ ነው።

በቅርቡ በሞቃዲሹ ኢንተርኔት እና ማኅበራዊ ሚዲያን በተመለከተ በተካሄደ ኮንፈረንስ ላይ ማኅበራዊ ሚዲያዎች እና ኢንተርኔት በአጠቃላይ በተለይ በወጣቱ ላይ " ሕይወት እስከ ማሳጣት " የሚደርስ ጉዳት እያደረሰ ነው የሚል ሃሳብ በስፋት ተንጸባርቆ ነበር ተብሏል።

በኬንያም እንዲሁ በተለይም በወጣቶች ዘንድ ከፍተኛ ተጠቃሚ ያለውን " ቲክቶክ "ን ለማገድ የሚያስችል ሃሳብ ለምክር ቤት ከሰሞኑም መቅረቡ ይታወሳል።

ቲክቶክ እንዲታገድ የተጠየቀው ፤ ኬንያ ቲክቶክን ለመቆጣጠር የሚያስችል ጠንካራ ሕግ ስለሌላት ጉዳት የሚያስከትሉ እና ተገቢ ያልሆኑ ይዘቶች በመድረኩ ላይ በስፋት እንዲቀርቡ ምክንያት ሆኗል በሚል ነው።

የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ሞሰስ ዊታንጉላ ፤ " ቲክቶክ በኬንያውያን በወጣቶች ዘንድ ተዘውታሪ በመሆኑ ፦
- ግጭቶችን በማባባስ፣
- ልቅ ወሲብን በማስፋፋት፣
- የጥላቻ ንግግሮችን በማስፋፋት፣
- የብልግና ቃላትን በማስፋፋት፣
- አደገኛ ባሕሪያትን በማስፋፋት ለአገሪቱ ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ እሴቶች ጠንቅ እየሆነ ነው " ብለዋል።

ቲክቶክ እንዲታገድ ጥያቄ ያቀረቡት ግለሰብ ምክር ቤቱ ቲክቶክን የሚያግደው ከሆነ፣ በወጣቶች ዘንድ እየተስፋፋ ያለውን ሱሰኝነት እና የአእምሮ ጤና ችግርን ለመከላከል ይቻላል ብለዋል።

የቲክቶክ መተግበሪያ በሕገወጥ መንገድ የኬንያውያንን ግላዊ መረጃ በመሰብሰብ እና በማጋራት ተጠያቂ ነውም ብለዋል።

የቀረበውን ሃሳብ አንዳንድ የምክር ቤት አባላት የደገፉት ሲሆን ሌሎች ደግሞ እገዳው ኬንያውያንን ከቴክኖሎጂ የሚያርቅ እና በቲክቶክ ላይ ይዘቶችን በማቅረብ ገቢ የሚያገኙ ወጣቶችን የሚጎዳ ነው በማለት ተቃውመውታል።

ከፍተኛ ተደማጭነት ያላቸውን የምክር ቤቱ አባላትን ጨምሮ አንዳንድ እንደራሴዎች ደግሞ ተክቶክን ሙሉ ለሙሉ ከማገድ ይልቅ በይዘቶቹ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ ደንብ እንዲወጣ ጠይቀዋል።

#BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አውሮፓ ህብረት ምን አለ ? የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ እና በራዝ ገዟ ሶማሊላንድ መካከል የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት በተመለከተ አጭር መግለጫን ትላንት ምሽት አውጥቶ ነበር። በዚህ መግለጫው፤ እ.ኤ.አ. ጥር 1 ቀን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እና የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ የኢትዮጵያ  የባህር በር አገልግሎት (በሊዝ) ማግኘት የሚያችላትን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል…
#ኢጋድ #ሶማሊያ

ዛሬ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ) ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህም መግለጫ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዲላፕሎማሲው መስክ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ግንኙነት መካከል እያታየ ያለው ሁኔታ በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

ኢጋድ ሁኔታውን በንቃት እየተከታተለ መሆኑን እና በቀጠናው መረጋጋት ላይ ያለውን ተፅእኖ እንደሚገነዘብ አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ሁኔታዎችን በሰላማዊ እና በመግባባት መንፈስ ለመፍታት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ዶክተር ወርቅነህ በመግለጫቸው በኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ መካከል ስለተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ያነሱት ነገር የለም።

የሶማሊያ መንግሥት የዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ መግለጫ እንዳበሳጨው ለመረዳት ተችሏል።

የሶማሊያ መንግሥት " የመግለጫው ሃሳብ ለኢትዮጵያ ያደላ ነው " በማለት ዶ/ር ወርቅነህ በአስቸኳይ ይቅርታ እንዲጠይቁ፣ የይቅርታ መግለጫም በማውጣት አስፈላጊ እርምጃ እንዲወስዱ ብሏል።

ሶማሊያ ፤ የኔ አንድ ግዛት ናት በምትላት ሶማሊላንድ እና ኢትዮጵያ መካከል የተረፈመው ስምምነት ያበሳጫት ሲሆን ስምምነቱ የግዛት አንድነቴን እና ሉዓላዊነትን የጣሰ ነው በማለት እየተቃወመች ትገኛለች።

(የሁለቱም መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia