TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba ታህሳስ 7 ቀን 2016 ዓ/ም ምሽት አዲስ አበባ ቦሌ ኤድና ሞል አካባቢ አንድ ሰው በጥይት ተመቶ ተገድሏል። ድርጊቱ የተፈፀመው ቦሌ ከኤድናሞል ወረድ ብሎ በሚገኝ አንድ የመዝናኛ ስፍራ አካባቢ ነው። ምሽት አራት ሰዓት ገደማ ሟች #አባተ_አበበ በአንድ #መሳሪያ_በታጠቀ ግለሰብ በጥይት ተመቶ መገደሉ ታውቋል። አባተ አበበ ተወልዶ ባደገበት ፣ በሚኖርበት  አካባቢ እንዲሁም ደግሞ በስራ…
#ግድያ #የፖሊስ_ምላሽ

" ፖሊስ ሥራውን እየሰራ ነው። ግልጽ ማድረግ በሚገባን ሰዓት ላይ ግልጽ እናደርጋለን " - ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ

አቶ አባተ አበበ የተባሉ ግለሰብ ታህሳስ 7 ቀን 2016 ዓ/ም አዲስ አበባ ቦሌ ኤድናሞል አካባቢ ዝቅ ብሎ በሚገኝ መዝናኛ 'በጥይት ተመትቶ ተገደለ' መባሉን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ " ፖሊስ ሥራ እየሰራ ነው። ግልጽ ማድረግ በሚገባን ሰዓት ላይ ግልጽ እናደርጋለን " ብለዋል።

ኮማንደሩ በሰጡት ማብራሪያ፣ " ሰው ወዲያው እንደሞተ ወደ ሚዲያ መውጣት አለበት ? " ሲሉ ጠይቀው፣ " በጣም አሁን እኮ አንዳንድ ፀሐፊዎች እንዳውም ፎቶ ግራፉን ሁሉ ' ተጠርጣሪ ይሄ ነው ' እያሉ እየለጠፉ ነው። ይሄ ኢቲካል እኮ አይደለም " ብለዋል።

አክለውም፣ " ይሄን ሰውየ እኮ ፍርድ ቤት ነው 'ጥፋተኛ ነህ' ብሎ ጥፋተኛ መሆኑን የሚገልጽለት እንጂ ግለሰብ እየተነሳ 'ጥፋተኛ ነው' ብሎ ፎቶ እየለጠፉ ትክክል እኮ አይደለም " ብለዋል።

ምክትል ኮማንደር ማርቆስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ሲያስረዱም ፦

- " ፍርድ ቤት እኮ ጥፋተኛ እስከሚለው እኮ ነፃ ሆኖ የመቆጠር መብት አለው። "

- " ከሕግ አንጻር እኮ ማዬት መቻል አለብን። ይሄ ነገር #የሚያስከትለውን ነገር ማየት መቻል አለበት። "

- " ቤተሰቦቹን ማሰብ መቻል አለበት። አሁን እነዚህ ሰዎች #ጎረቤታሞች ቢሆኑ እኮ የዛ ቤተሰብ መጥቶ እዚህ ልጅ ላይ እርምጃ ሊወስድ ነው። እንዴት እንደዚህ አይታሰብም ? ብቻ በአጠቃላይ በጣም ቀውሷል ሚዲያው ፤ ከባድ ቀውስ ላይ ነው ያለነው " ሲሉ አስረድተዋል።

የሟቹን ጉዳይ በተመለከተ ፖሊስ ያገኘው መረጃ እና የጀመረው ምርመራ እንዳለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ኮማንደር ማርቆስ፣ " ፖሊስ ሥራ እየሰራ ነው። ግልጽ ማድረግ በሚገባን ሰዓት ላይ ግልጽ እናደርጋለን። አሁን ሥራ እየተሰራ ነው " ሲሉ አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

የአባተ አበበን ጉዳይ በተመለከተ እየተከታተልን የምናቀርብ ይሆናል።

ይህን መረጃ አዘጋጅቶ የላከው የአ/አ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ግድያ #የፖሊስ_ምላሽ " ፖሊስ ሥራውን እየሰራ ነው። ግልጽ ማድረግ በሚገባን ሰዓት ላይ ግልጽ እናደርጋለን " - ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ አቶ አባተ አበበ የተባሉ ግለሰብ ታህሳስ 7 ቀን 2016 ዓ/ም አዲስ አበባ ቦሌ ኤድናሞል አካባቢ ዝቅ ብሎ በሚገኝ መዝናኛ 'በጥይት ተመትቶ ተገደለ' መባሉን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጠይቋል። የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት…
#AddisAbaba

ፖሊስ በአቶ አባተ አበበ ግድያ ሲፈለግ የነበረውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ዛሬ ምሽት አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ የግድያ ተጠርጣሪው አቶ ተስፋዬ ሆርዶፋ የተባሉ ግለሰብ መሆናቸውን ገልጿል።

አቶ አባተ አበበ ታህሳስ 7/2016 ዓ/ም አዲስ አበባ ቦሌ ኤድናሞል አካባቢ ዝቅ ብሎ በሚገኝ ጭፈራ ቤት ' በጥይት ' ተመተው መገደላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አመልክቷል።

@tikvahethiopia
#AfricanDevelopmentBank

የአፍሪካ ልማት ባንክ ዓለም አቀፍ ሰራተኞቹን በአስቸኳይ #ከኢትዮጵያ ሊያስወጣ ነው።

ባንኩ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከአንድ ወር በፊት ዋና የኢትዮጵያ ተወካዩ እና ሌላ የባንኩ ሰራተኛ ላይ በፀጥታ አካላት ድብደባ መፈፀሙን ተከትሎ ነው።

በወቅቱ ባንኩ ቅሬታውን ለመንግስት አቅርቦ የነበረ ሲሆን መንግስትም አስቸኳይ ማጣራት አድርጎ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርግ ገልፆ ነበር።

አሁን ባንኩ ዓለም አቀፍ ሰራተኞቹን " በአስቸኳይ " ከኢትዮጵያ እንዲወጡ ሊያደርግ የወሰነው ድብደባውን ፈፅመዋል በተባሉት የፀጥታ አካላት ዙርያ ስለተደረገው ምርመራ የኢትዮጵያ መንግስት ለባንኩ መረጃ ባለማጋራቱ እንዲሁም በሰራተኞቹ ዘንድ በደህንነታቸው ዙርያ ሙሉ እምነት ሊያገኝ ባለመቻሉ እንደሆነ የባንኩ ፕሬዝደንት ዶ/ር አኪንዉሚ አዴሲና አሳውቀዋል።

ምንም እንኳን ባንኩ ዓለም አቀፍ ሰራተኞቹን ከኢትዮጵያ በአስቸኳይ ለማስወጣት ውሳኔ ላይ ቢደርስም በኢትዮጵያ ያለው ቢሮው ክፍት ሆኖ እንደሚቆይና ውሳኔው ከኢትዮጵያ የተቀጠሩ ሰራተኞችን እንደማይመለከት ገልጿል።

እነዚህ ከኢትዮጵያ የተቀጠሩ ሰራተኞች በስራ ገበታቸው እንደሚቀጥሉና በባንኩ ሙሉ የስራ ስምሪት ውስጥ / የባንኩ ሰራተኞች ሆነው እንደሚቆዩ ማረጋገጫ ተሰጥቷል።

አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የባንኩ የኢትዮጵያ ቢሮ ሰራተኛ ከኢትዮጵያ ባስቸኳይ እንዲወጡ የሚደረጉት ዓለም አቀፍ ሰራተኖች ወደ ደቡብ አፍሪካ እና ኬንያ ሊዛወሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

እንደ ሬውተርስ ዘገባ የአፍሪካ ልማት ባንክ ኢትዮጵያ ውስጥ የ308 ሚልዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው ስምንት ፕሮጀክቶች አሉት።

Credit - Journalist Elias Meseret

@tikvahethiopia
አስተማማኝ የባትሪ ቆይታ ከ Tecno Pop 8 !

የTecno ሞባይል ምርት የሆነው Pop 8 በ5000mAh የባትሪ አቅም ለረጅም ሰዐት ያለምንም እንከን ስልኮን መጠቀም የሚያስችል ሲሆን፣ በ6.6 ኢንች ሰፊ ስክሪን ፊልም ቢያዩ፣ ጌም ቢጫወቱ ባትሪው ንቅንቅ አይልም። ከዚም በተጨማሪ በ10 ዋት ፋስት ቻርጅ ቴክኖሎጂ ስልኮን በፍጥነት ቻርጅ ማረግ ያስችላል።

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Pop8 #TecnoMobile #TecnoEthiopia
#ኢትዮጵያ

በፕሪቶሪያ የተፈረመው #የሰላም_ስምምነት ለዘላቂ ሰላም አስተዋፅኦ ያደርጋል ? ወይስ አያደርግም ? በሚሉት ነጥቦች ክርክር እና ውይይት እንዲደረግ ከ #USAID በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ " ሀበጋር " (የደበበ ኃ/ገብርኤል የህግ ክርክር ፕሮግራም) ባለፈው ቅዳሜ አንድ የውይይት እና ክርክር መድረክ ተዘጋጅቶ ነበር።

በመድረኩ ላይ የተጋበዙ ምሁራን ፣ የሕግና የፖለቲካ ባለሙያዎች ፣ የፖለቲካ ፖርቲዎች በየፊናቸው ሀሳብ ሲሰጡ ፤ የተለያዩ ጥያቄዎችንም ሲሰነዝሩ ተስተውለዋል።

የታሪክ ምሁር እና የቀድም #የአብን ብሔራዊ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም (ዶ/ር) የፕሪቶሪያው ስምምነት " #ዘላቂ ሰላምን አያመጣም " በማለት፣ እንዲሁም የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አበበ ገ/ህይወት " ስምምነቱ ዘላቂ ሰላም ያመጣል " በማለት ክርክር አድርገዋል።

በአንድ ወገን ያሉት ተሳታፊዎች ስምምነቱ ከነችግሩም ቢሆን ዘላቂ ሰላም ያመጣል፣ በሌላ ወገን ደግሞ ስምምነቱ አሳታፊና ግልፅኝት፣ ተጠያቂነት መርሆችን ካላሟላ ዘላቂ የሆነ ሰላም ሊመያመጣ አይችልም ፣ ቀድሞውንም አሳታፊነት እና ግልጸኝነት የጎደለው ነው በማለት ሀሳባቸውን አቅርበዋል።

በመድረኩ ፦

- የፕሪቶሪያው ስምምነት ዘላቂ ሰላም ያመጣል ? አያመጣም ?
- የተፈናቃዮች ጉዳይ
- የራያ እና ወልቃይት ጉዳይ ተነስተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ክርክርና ውይይት መድረኩ የተሳተፉ አካላትም አነጋግሯል።

ያንብቡ - https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-19
#GERD🇪🇹

" ግብፅ #የቅኝ_ግዛት ዘመን አስተሳሰቧን ይዛ በመቀጠል ወደ ስምምነትና ትብብር የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች " - ኢትዮጵያ

ባለፉት ቀናት ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን አዲስ አበባ ውስጥ የሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እንዲሁም ዓመታዊ የሥራ ሂደትን የተመለከተ መመሪያ ላይ የሦስትዮሽ ድርድር ሲያካሂዱ ነበር።

ድርድሩ ያለ ስምምነት ነው የተጠናቀቀው።

ኢትዮጵያ ምን አለች ?

- ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ እና በፍትሐዊ ድርድር የሶስቱን ሀገራት ጥቅም የሚያስጠብቅ የመፍትሔ ሀሳብ ላይ ለመድረስ ያላትን ቁርጠኝነት ይዛ እንደምትቀጥል ገልጻለች።

- አራት ዙር ድርድር ተካሂዷል ፤ ይህ ድርድር የተካሄደው በጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና በፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ኤል ሲሲ የጋራ መግባባት ነው።

- በአራት ዙሮች ኢትዮጵያ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ጋር ልዩነቶችን ለመፍታትና የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረት አድርጋለች።

- ግብፅ #የቅኝ_ግዛት ዘመን አስተሳሰቧን ይዛ በመቀጠል ወደ ስምምነትና ትብብር የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች።

- የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ አሞላል እና ዓመታዊ አሰራር መመሪያ እና ደንቦች ላይ የተደረገው ድርድር በሶስቱ ሀገራት መካከል መተማመን ለመፍጠር እንጂ በአባይ ውሃ አጠቃቀም ላይ የኢትዮጵያን መብት ለመንጠቅ ያለመ አይደለም።

- ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በፍትሃዊና ምክንያታዊ አጠቃቀም መርህ ላይ በመመስረት የአሁንና የመጪውን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት ጥረቷን አጠናክራ ትቀጥላለች።

- አራተኛው ዙር ድርድር ከተጠናቀቀ በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ቻርተር እና የአፍሪካ ህብረት ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌን የሚጻረር መግለጫ ግብጽ አውጥታለች። ኢትዮጵያ በግብፅ በኩል የቀረበባትን የተሳሳተ መረጃ አትቀበለውም።

ግብፅ ምን እያለች ነው ?

* " ኢትዮጵያ የሦስቱንም አገራት ጥቅም ሊያስጠብቅ እና ሊያስማማ የሚችል የሕግም ሆነ የቴክኒክ መፍትሄዎችን ለመቀበል ዝግጁ አይደለችም " የሚል ነገር ይዛ ብቅ ብላለች።

* " የግድቡን አሞላል እና ኦፕሬሽን በቅርበት በመከታተል መብቴን አስከብራለሁ " ስትልም ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥታለች።

* ግብፅ " በግድቡ ምክንያት የትኛውም አይነት ጉዳት ቢደርስብኝ በዓለም አቀፍ ቻርተሮች እና ስምምነቶች መሠረት የውሃ ድርሻዬን እና ብሔራዊ ደኅንነቴን የመጠበቅ መብቴ የተጠበቀ ነው " ስትልም መግለጫ አውጥታለች።

🇪🇹 ኢትዮጵያ #በተደጋጋሚ ጊዜ አንዳቸውም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በአባይ ግድብ ምክንያት ጉዳት እንደማይደርስባቸው ይልቁንም እነሱኑ እንደሚጠቅም አሳውቃለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ የትግራይ የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ፤ ሁሉም የወረዳ ትምህርት ፅህፈት ቤቶች የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ምዝገባ እንዲያካሂዱ አዘዘ። የ12ኛ ክልፍ ፈተና በጥር ወር ውስጥ እንደሚሰጥም አሳውቋል። ኤጀንሲው ህዳር 12/2016 ዓ.ም ለሁሉም የክልሉ የወረዳ የትምህርት ፅህፈት ቤቶች በላከው ሰርኩላር ደብዳቤ እንደስታወቀው ፤ በጦርነቱ ምክንያት ከመላ አገር በትግራይ…
#Tigray

የ12ኛ ክፍል ፈተና ተራዘመ።

" በሚቀጥለው ጥር ወር 2016 ዓ.ም ለመስጠት የታቀደው የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ላልታወቀ ጊዜ ተራዝሟል " ሲል የትግራይ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

ቢሮው ለሚድያ ባሰራጨው ፅሑፍ እንዳለው ፤ የትግራይ ትምህርት ከትምህርት ሚኒስቴር በመግባባት በክልሉ በነበረው ደም አፋሳሽ ጦርነት ምክንያት ሳይሰጥ የቆየው የ12ኛ ከፍል አገር አቀፍ ፈተና መስከረም 29/2016 ዓ.ም ፣ ጥር 6 /2016 ዓ.ም እና ግንቦት 2016 ዓ.ም ለመስጠት አቅዶ በሚድያ ለህዝብ ይፋ ማድረጉ አስታውሷል።

ይሁን እንጂ በሚቀጥለው ጥር 6/2016 ዓ.ም ለመስጠት ያቀደው የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙ ታህሳሰ 9/2016 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ደብዳቤ አስታውቋል።

ቢሮው ፈተናውን ለማራዘም ያስገደዱት ሶስት ምክንያቶች ዘርዝሯል። እነሱም ፦

1. ፈተና የሚሰጥባቸው ዩኒቨርስቲዎች ዘግይተው ተማሪዎች በመቀበላቸው ምክንያት ሊሰጥ የታቀደው ፈተና ዩኒቨርስቲዎቹ ካወጡት የትምህርት ፕሮግራም የማይጣጣም በመሆኑ፤

2. የአገር አቀፍ የትምህርት ፈተናና ምዘና አገልግሎት የዝግጅት ጊዜ እጥረት እንደገጠመው በመግለፁ፤

3. ተማሪዎች ለፈተና መዘጋጃ የሚሆን የጊዜ እጥረት መኖሩ በመረዳት፤

ጥር 6/2016 ዓ.ም ለመስጠት የታቀደው የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል ብሏል። 

በተያያዘ ከታህሳስ 18 አስከ 20/2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥ ሲሆን ፈተናውን ለመፈተን 60 ሺህ ተማሪዎች መመዝገባቸው ቢሮው ማስታወቁ ጠቅሶ የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
                  
@tikvahethiopia            
#GlobalBankEthiopia

ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ ለምናዘጋጃቸው የጥያቄ ውድድሮች የቴሌግራም ገፃችንን https://publielectoral.lat/Globalbankethiopia123 በመቀላቀል ይሳተፉ! ይሸለሙ!
#SafaricomEthiopia

ቅመም ITEL PROን እንግዛ ፤ ለኛ በተሰራ ቀላል እና ቀልጣፋ ስልክ ማርሻችንን ቀይረን ዲጂታል አለሙን እንቀላቀል።

ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://publielectoral.lat/Safaricom_Ethiopia_PLC

#SafaricomEthiopia
#FurtherAheadTogether
" ወንጀሉ እየረቀቀ በመምጣቱ ከህብረተሰቡ ጋር ለመስራት የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል " - የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ

➡️ ጥቆማ መስጫ ነፃ የስልክ መስመር  6073

የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ከዓለም አቀፍ ፍልሰተኞች ድርጅት(IOM) በጋራ በመተባበር  በሰው የመነገድ ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ለመከላከል የሚያስችለውን አሰራር በመዘርጋት ህብረተሰቡ መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ አቀረበ።

ቢሮው ከተማው የወንጀሉ መነሻ፣ መተላለፊያና መዳረሻ በመሆኑ ወንጀሉ የሚፈፀመው በህብረተሰቡ ውስጥ በመሆኑ  በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብሏል።

ወንጀሉ እየረቀቀ እና እየተወሳሰበ መምጣቱን የገለፀው ቢሮው ከህብረተሰቡ ጋር ለመስራት የሚያስችለውን አሰራር ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር መዘርጋቱን ይፋ አድርጓል።

በዚህም ፤ ህብረተሰቡ ወንጀሉን በጋራ ለመከላከል እንዲቻል በነጻ የስልክ መስመር 6073 ላይ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር  ጥሪ አቅርቧል።

በሌላ በኩል ፥ ወንጀሉን በትብብር መከላከል የሚያስችሉ የተለያዩ አደረጃጀቶችን እስከ ወረዳ ድረስ በማደራጀት ወንጀሉን በተመለከተ  ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የግንዛቤ ፈጠራ ስራ በመስራት ላይ እንዳለ ይፋ አድርጓል።

@tikvahethiopia
" ለአላህ ብላችሁ ተባበሩኝ እያለቀስኩ ነው…ልጄ ልትገደልብኝ ነው አስመጡልኝ " - አረጋዊያኖቹ የለይላ  አባትና እናት

ከአሰሪዎቿ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ግጭት ተፈጥሮ በመካከል የአንድ ታዳጊ ሕይወት በማለፉ በሳዑዲ መንግሥት ሕግ መሠረት የሞት ፍርድ የተፈረደባት ኢትዮጵያዊት የሟች ቤተሰቦች የሞት ፍርዱ ወደ ካሳ እንዲቀየር ተስማምተዋል።

በዚህም የተጠየቀው 2 ሚሊዮን ሪያል ከወዳድ ዘመድ ተሰብስቧል። ይሁን እንጂ ገንዘቡ ቢሰበስብም የሚላከው በመንግሥት በኩል በመሆኑና ገና ስላልተላከ ፍርደኛዋ በሳዑዲ የሞት ፍርድ እየተጠባበቀች መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቤተሰቦቿ ገለጻ ተረድቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አረጋዊ የፍርደኛዋ አባት አቶ ኑርሰቦ፣ " ለአላህ ብላችሁ ተባበሩኝ #እያለቀስኩ ነው። እናቶች፣ አባቶች እባካችሁ ተባበሩኝ። የኢትዮጵያ ልጆች፣ የዓለም ልጆች ተባበሩኝ እባካችሁ ትመጣልኛለች እያልኩ 11 ዓመታት ሙሉ ጠበኳት እባካችሁ " ሲሉ እንባቸውን እያፈሰሱ ተማጽነዋል።

" ልጄን ልትገደልብኝ ነው አስመጡልኝ " ያሉት፣ የፍርደኛዋ አረጋዊት እናት ወ/ሮ ነፊሳ ሙሳ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ከወዳጅ ዘመድ የተሰበሰበውን ገንዘብ በባንክ በኩል ወደ ሳዑዲ መንግሥት በፍጥነት በመላክ ልጃቸውን ከሞት እንዲታደግላቸው በአጽንኦት ጠይቀዋል።

የ21 ዓመቷ ለይላ ኑርሰቦ ሰርቸ እለወጣለሁ በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ ወደ ሳዑድ አረቢያ ከወጣች 11 ዓመታትን እንዳስቆጥረች ወላጆቿ አስረድተዋል። 

ይሁን እንጂ በሳዑዲ አረቢያ ከአሰሪዎቿ ጋ በተፈጠረ ግጭት የ11 ዓመት ታዳጊ በፀቡ ወቅት በመጎዳቱ  #ለአምስት_ወራት በሆስፒታል ሲረዳ ቢቆይም ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም።

ይህን ተከትሎም 'የገደለ ይገደል' በሚል የሳዑዲ ሕግ ለይላ ነፍስ ማጥፋት ወንጀል ለ11 ዓመታት እስራትና የሞት ፍርድ እንደተፈረደባት ቤተሰቦቿ እንዲሁም የቲም ለይላ አስተባባሪዎች ገልጸዋል።

እንደ ገለጻው ከሆነ፣ የሟች ቤተሰቦች የሞት ፍርድ በካሳ ክፍያ እንዲቀየር ተስማምተዋል።

በዚህም 2 ሚሊዮን ሪያል፣ በኢትዮጵያ ብር ሲሰላ ደግሞ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲከፈላቸው ተብሎ በሳዑዲ መንግሥት ውሳኔ ተላልፎበታል።

ወዳጅ ዘመድ፣ በጎ አድራጊ ድርጆቶች ድጋፋ እንዲያደርጉ በማኀበራዊ ሚዲያ በተደረገ የ54 ቀናት ዘመቻ በቤተሰቦቿ በኢትዮጵያ በተከፈተ የባንክ አካውንት 30 ሚሊየን ብር፣ በሳውዲ በሟች ቤተሰቦችና በፍርደኛዋ በተከፈተ የባንክ አካውንት 230,000 ሪያል ተሰብስቧል።

መንግሥት የተሰባሰበውን ገንዘብ በፍጥነት ካልከ #ከ39 ቀናት በኋላ ለይላ የሞት ፍርዱ ሊፈጸምባት እንደሚችል በመግለጽ ቤተሰቦቿ እርዳታ እንዲደረግላቸው ተማጽነዋል።

በዛሬው ዕለት በሸራተን ሆቴል በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ የ'ለይላን እንታደጋት' የሶሻል ሚዲያ ንቅናቄ፣ "በሳዑዲ የሞት ፍርድ የተፈረደባት እህታችንን እንታደጋት" የሚል ጥሪ ተላልፏል።

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
የማባያ ምርጫችሁ በቀኑ ይወሰናል? ለሀሙስ የሚሆን ቅመም የትኛው ነው? ከ #ሰንቺፕስ 😋 ጋር #ሰኒሞመንትስ ☀️
What’s your tip for a dip? Which one goes best for a Thursday? - with #SunChips 😋 and #SunnyMoments. ☀️

Facebook: https://www.facebook.com/sunchipsethiopia
Instagram: https://instagram.com/sunchipsethiopia