TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Aspiring women entrepreneurs, this is your golden moment to realize your entrepreneurial dreams! Apply for the Jasiri Talent Investor Cohort 5 at http://jasiri.org/application to find your co-founder and build the business venture you've been dreaming of. #Jasiri4Africa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቴሌብር ስኩልፔይ

በአዲሱ የትምህርት ዘመን፤ ለትምሕርት ተቋማት፣ ለተማሪዎች እና ለወላጆች የቀረበ ልዩ መላ!

ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#WFP

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለኢትዮጵያ ሲያቀርበው የነበረው እርዳታ በተወሰነ መልኩ ማቅረብ መጀመሩ ተገለፀ።

በተመድ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ወደ ኢትዮጵያ ሲያቀርበው የነበረው የሰብአዊ እርዳታ ከአምስት ወራት ብኋላ እጅግ አነስተኛ በሚባል መልኩ እርዳታ መላክ መጀመሩን " አሶሸትድ ፕሬስ " ገልጿል።

ድርጅቱ ለአሶሸትድ ፕሬስ እንደገለፀው ፤ በትግራይ 4 አካባቢዎች በመቶ ሺህ እርደታ ፈላጊ ዜጎች ላይ አዲሱ የተቋሙ አሰራር ትግበራ ሙከራ በሐምለ መጨረሻ መጀመሩን አሳወቋል።

የተለያዩ ተቋማት ፣ ሃይማኖት መሪዎች እና የተለያዩ አካላት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለተቸገሩ ወገኖች ሲያቀርብ የነበረው  እርዳታ ማቋረጡን ተገቢ አለመሆኑ እና ከሞራል አንፃር ኢሞራላዊ ነው ብለው ሲተቹት እንደነበር ያወሳው ዘገባው በ21ኛው ክፍለ ዘመን የሰው ልጅ በምግብ እጦት ምክንያት በትግራይ የሞት አደጋ ማጋጠሙን አስታውሷል።

የአሜሪካ ህዝብ ተራድኦ ድርጅት / USAID ኃላፊ የሆኑት ሳማንታ ፓወር በበኩላቸው ፤ " ተፈጠሩ የተባሉ ችግሮችን በማጣራት እንዲሁም እርዳታው ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች በትክክል መድረሱን ማረጋገጥ ተገቢ ነው " ያሉ ሲሆን የሰብአዊ እርዳታው በአጭር ግዜ ለማስጀመር ጥረት ይደረጋል ማለታቸው ተዘግቧል።

ከአምስት ወራት በፊት የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ለኢትዮጵያ ሲያቀርበው የነበረው የሰብአዊ  ድጋፍ ስርቆትና ላልተገባ ተግባር ውሏል በመባሉ እንዲቆም መደረጉን የሚታወስ ነው።

መረጃው የድምፂ ወያነ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

" ግለሰቡ ህፃናቱን በተለያዩ ቀናት ከረሜላ እየገዛ በማታለል መኖሪያ ቤቱ ውስጥ አስገብቶ ወንጀሉን ፈፅሞባቸዋል " - ፖሊስ

በአዲስ አበባ ከተማ ፤ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በሶስት ህፃናት ላይ የ ' ግብረሰዶም ወንጀል ' የፈፀመ ግለሰብ  በፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንደተላለፈበት ተገለፀ።

የ43 ዓመት ዕድሜ ያለው ተከሳሽ ወንጀሉን የፈፀመው በክ/ከተማው ወረዳ 01 ልዩ ቦታው ማር ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ ያሳያል።

ግለሰቡ የጎረቤቱ ልጆች የሆኑ የ5 ፣ የ6 እና የ10 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ህፃናትን በተለያዩ ቀናት ከረሜላ እየገዛ በማታለል መኖሪያ ቤቱ ውስጥ አስገብቶ ወንጀሉን ፈፅሞባቸዋል።

ወንጀሉ ከተፈፀመባቸው ህፃናት መካከል የ6 ዓመቱ ህፃን ስለሁኔታው ለወላጅ እናቱ በመናገሩ ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል፡፡

ይህንን ተከትሎ ሌሎቹ 2 ህፃናትም ተመሳሳይ ድርጊት እንደፈፀመባቸው በመግለፃቸው በ3 የምርመራ መዝገቦች ክስ ተመስርቶበት ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ ቆይቷል፡፡

መዝገቡን ሲመረምር የቆየው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት የተከሳሹን ጥፋተኝነት በሰው እና በህክምና ማስረጃ በማረጋገጡ በ19 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ አስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል፡፡

ህብረተሰቡ ከህግ እና ከማህበራዊ እሴቶች ያፈነገጡ ህገ-ወጥ ተግባራት ሲያጋጥሙ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

#ግብረሰዶማዊነት በሀገራችን ህግ ፍፁም የተከለከና በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር በመሆኑ ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘ  መረጃ እና ጥቆማ ያለው ማንኛውም ሰው በአቅራቢያው በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ በግንባር በመቅረብ እንዲሁም በነፃ የስልክ መስመር 991 እና 987 እንዲሁም በ011-1- 11-01-11 እና 011-5-52-63-02 በመጠቀም መረጃና ጥቆማ መስጠት ይችላል ሲል ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
(ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ) " የስራ ሀላፊነትን በፈቃድ ስለመልቀቅ ! በ2011 ዓ.ም ታህሳስ ወር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ በመሆን ስራዬን ስጀመር ተቋማችንን ተአማኒ እና ራሱን ችሎ ምርጫን ማከናወን የሚችል ተቋም ለማድረግ በማለም ነበር። ባለፉት አራት አመት ከስድስት ወራት ሶስት ህዝበ ውሳኔዎችን እና አገራዊ ምርጫን በማካሄድ እና ፓለቲካ ፓርቲዎችን በማስተዳደር የተሰጡኝን ሃላፊነቶች…
ወ/ሪት ብርቱካን ሽኝት ተደረገላቸው።

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነታቸው በገዛ ፍቃዳቸው መልቀቃቸውን ያሳወቁት ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ሽኝት ተደረገላቸው።

ወ/ሪት ብርቱካን ፤ ጤናቸውን በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ከነሀሴ 1/ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነታቸው በገዛ ፍቃዳቸው መልቀቃቸውን ለተወካዮች ም/ቤት አፈጉባኤ ጽህፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም ማሳወቃቸው አይዘነጋም።

ፎቶ፦ NEBE

@tikvahethiopia
Audio
#Gondar

የጎንደር ግጭት ከተማዋን አስከፊ ሁኔታ ላይ እንደጣላት አንድ በጎንደር ሆስፒታል የሚሰራ የቲክቫህ የቤተሰብ አባል የሆነ የሕክምና ዶክተር አሳውቆናል።

የጎንደር ሁኔታ #እጅግ_አስከፊ እንደነበር የገለፀልን የህክምና ዶክተሩ " በግጭቱ ምክንያት የመጨረሻ ኢሰብአዊ ድርጊት ተፈጽሟል ፤ ሰላማዊ ዜጎች እዚህም እዚያም ተገድለዋል " ሲል አስረድቷል።

በሆስፒታሉ ውሃ ፣ ኦክስጂን ፣ እንዲሁም ደግሞ መድሃኒት ቤት ከመድሃኒት ውጭ እየሆኑ መሆኑን ገልጿል።

" የከባባድ መሳሪያ ድምጾች ከሆስፒታሉ ውስጥ ሆነን ይሰማን ነበር " ያለው ዶክተሩ ላለፉት ቀናት ከተማዋ በተኩስ ስትናጥ መቆየቷን አመልክቷል።

እስከ ትላንት ሰኞ ከሰዓት ድረስ በግጭቱ ምክንያት የተጎዱ ሰዎችን ወደ ሆስፒታል የሚያመላልስ እና አገልግሎት ሲሰጥ የነበረ አንድ አምቡላንስ ብቻ እንደነበር እሱም በሚያስዝን ሁኔታ ዒላማ መደረጉን የጎንደር ሆስፒታል ዶ/ር የሆነው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል አሳውቆናል።

የንፁሃን ነዋሪዎች ጉዳይ ትኩረት የሚሻው መሆኑን አስገንዝቧል።

(ድምፅ ዛሬ ጥዋት ላይ የተቀዳ)

@tikvahethiopia
"  ምግብ ካገኘን ሦስት ቀን አልፎናል " - ጎንደር የሚገኙ መምህር

የ12ኛ ክፍል የብሔራዊ ፈተና ለመስጠት አማራ ክልል ወዳሉ ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የሄዱ መምህራን በክልሉ በተቀሰቀሰው ግጭት ምክንያት ወደየመጡበት አካባቢ ለመመለስ እንዳልቻሉ ገልጸዋል።

እንጃባራ ዩኒቨርሲቲ ፈታኝ የነበሩ አንድ መምህር ለቪኦኤ በሰጡት ቃል፤ በክልሉ " የሰላም ሁኔታው አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነው ያለው ፤ ለመፈተን ሄደን በማናውቀው ሁኔታ ውስጥ ገብተናል " ብለዋል። " መንገዱ ዝግ ነው ነገሩ የደፈረሰ ነው ፤ ያለው ሁኔታ ያስፈራል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት በመጣልን መልዕክት ' እዛው ባላችሁበት ፔንስዮን ቆዩ፣ አልጋ ይከፈላል ' የሚል ሲሆን እኛ ደግሞ ችግራችን የአልጋ አይደለም ፤ ችግር ውስጥ ነው ያለነው ፤ የየራሳችን ፕሬዜዳንቶችም እየደወሉ አይዟቹ እዛው ሁኑ ነው የሚሉን ፤ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር እየተነጋገርን ነው ኮማንድ ፖስቱ ያለውን ነገር እስኪያሳውቅ ጠብቁ ነው ያሉን ፤ ያለው ሁኔታ ግን ያስፈራል " ሲሉ ገልጸዋል።

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ መምህር ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ፤ በከተማው ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት መሃል ከተማ ከሚገኘው የሆቴል ክፍላቸው ከወጡ ሦስት ቀናት መቆጠራቸውን ገልፀዋል።

" በከተማዋ ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም " ያሉት መምህሩ " የሆቴሉ ሠራተኞችም ወደ ሥራ እየገቡ ስላልሆነ ምግብ ማግኘት እጅግ ከባድ ሆኗል " ብለዋል።

" ምግብ ካገኘን ሦስት ቀን አልፎናል። ባለፈው ሳምንት የገዛነውን ቆሎ ነው እየቆጠብን እየበላን ያለነው። ከሆቴሉ እያገኘን ያለነው ውሃ ብቻ ነው " ሲሉ ሁኔታውን አስረድተዋል።

ቃላቸውን ለቢቢሲ የሰጡ በደብረ ማርቆስ የሚገኙ መምህር ደግሞ በከተማው ግጭት ባይኖርም የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እና የንግድ ተቋማት ዝግ መሆናቸውን ተናግረዋል።

" ከተማው ከሞላ ጎደል ሰላም ነው። የደረሰብን ጉዳት የለም። ዋናው ችግራችን ወደ መጣንበት ለመመለስ አለመቻላችን ነው " ብለዋል።

አሁን ላይ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በከተማዋ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ የሚገልጹት መምህሩ ፤ በአካባቢው ያለው የፀጥታ ሁኔታ ከዚህ በላይ ተባብሶ የበለጠ ችግር ውስጥ ከመግባታቸው በፊት ሚመለከተው አካል ትኩረት እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

በተመሳሳይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት ያደረሱ የተለያዩ ተቋማት መምህራን ከግጭት ቀጠና የሚወጡበት መንገድ በፍጥነት እንዲመቻችና ወደቤተሰቦቻቸው የሚመለሱበት መንገድ እንዲፋጠን ጠይቀዋል።

በአማራ ክልል ያሉ የዩኒቨርሲቲ መምህራን እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንደሆኑ አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Amahra

" የባልደረባችንን አስክሬን ማምጣት አልቻልንም ፤ እዛው ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ ነው ያለው " -ዶ/ር ፋሪስ ደሊል

ተቋማት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመፈተን ወደ አማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የሄዱ እና በክልሉ ባለው ግጭት ምክንያት  መመለስ ያልቻሉ መምህራንን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን አሳውቀዋል።

በርከታ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የ12ኛ ክፍል ፈተና ለመፈተን ወደ አማራ ክልል በሄዱበት በተባባሰው ግጭት ምክንያት ከክልሉ መውጣት ባለመቻላቸው ችግር ላይ መሆናቸውን እየገለፁ ናቸው።

መምህራኖቹ አማራ ክልል ከሚገኙ ተቋማት አንዱ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን ፤ መምህራኑን በተመለከተ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንት ዶ/ር ፋሪስ ደሊል ለቪኦኤ በሰጡት ቃል ፤ ባለፈው ሳምንት በጎንደር የተገደለው መምህር የተቋማቸው ባልደረባ መሆኑን ገልጸው እስካሁን እስክሬኑ ከከተማው እንዳልወጣ ጠቁመዋል።

ሌሎችም መምህራን ጎንደር እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ዶ/ር ፋሪስ ፤ " ለመፈተን ከሄዱ መምህራን አንዱ መምህር ታደሰ አበበ አስክሬኑን ማምጣት አልቻልንም እዛው ነው ያለው ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ውስጥ " ያሉ ሲሆን " ሌሎች ለመፈተን የሄዱ መምህራንም አሉ እነሱን በስልክ እያገኘናቸው ነው መመልስ አልቻሉም " ብለዋል።

ካሉበት ወጥተው ለመምጣት ደህንነት የለም ያሉት ፕሬዜዳንቱ " የጥይት ድምፅ በተለያየ ቦታ ይሰማል ዩኒቨርሲቲው ባላችሁበት ቆዩ ነው ያላቸው። " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመምህራኑ ጉዳይ እየተነጋገርን ነው ያሉት ዶ/ር ፋሪስ " መንገዱ ሰላም ሆኖ መውጣት የሚችሉበት ሰዓት ደርሶ እስኪመጡ በትግዕስት መጠበቅ እንዳለብን ነው የምንነጋገረው ፤ እዛው ከለው የዩኒቨርሲቲ አመራር ፣ ፕሬዜዳንቱም ጋር እየተደዋወልን ነው በትዕግስት ጠብቀን መንቀሳቀስ ሲችሉ መምህራኖቻችን እና የባልደረባችንን አስክሬን እንደምናገኝ ነው የምንነጋገርው " ብለዋል

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ፤ 53 መምህራን በጎንደር ፣ ደባርቅ እና ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲዎች እንደተመደቡና ሁኔታቸውን በቅርበት እየተከታተልን ነው ብለዋል።

ደህንነታቸው ተጠብቆ በሚወጡበት ሁኔታ ላይ ከትምህርት ሚኒስቴር እና ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ጋር እየተነጋገርን ነው ሲሉ አሳውቀዋል።

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፤ ፈታኝ መምህራንን ቀደሞ ወደመጡበት መሸኘቱን ተፈታኝ ተማሪዎች ግን በመንገድ መዘጋት ምክንያት ከግቢ መውጣት አልቻሉም ብሏል። ተቋሙ ባህር ዳር ነዋሪ የሆኑትን እና ቤተሰብ ያላቸውን የሸኘ ሲሆን ወደ ወረዳ እና ዞን መመለስ የነበረባቸውን በመንገድ መዘጋት መሄድ ስላልቻሉ ግቢ ውስጥ እንዲቆዩ መደረጉን ለሬድዮ ጣቢያው (ቪኦኤ) ገልጿል።

የአውሮፕላን በረራ በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የፈተና አስፈጻሚዎች / መምህራን " ያለው ሁኔታ እስከሚረጋጋ ድረስ ትንሽ ቀን " መጠበቅ እንደሚኖርባቸው የትምህርት ሚኒስትሩ ባለፈው አርብ በሰጡት መግለጫ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

@tikvahethiopia
Visa Everywhere Initiative (VEI) ልዩ የኢትዮጵያ ውድድር: ቢዝነሳችሁን ወደ ላቀ ደረጃ ለመውሰድ ዝግጁ ናችሁ?

ለVisa Everywhere Initiative 2015/16 በመመዝገብ እውቅና ማግኘት፣ የቬንቸር ካፒታሊስቶችን ዐይን መሳብ ፣ ኢንቬስትመንት እና አጋሮችን ማግኘት ይቻላል።

የVEI ልዩ የኢትዮጵያ ውድድር ምዝገባ እስከ ነሐሴ 14 ድረስ ክፍት ነው። https://africa.visa.com/visa-everywhere/everywhere-initiative/initiative.html

#EverywhereInitiative8
#ሰከላ_ስኩል_ሲስተም

የግልና የመንግስት የትምህርት ተቋማትን ሁለንተናዊ ክንውን የሚያዘምነውን የሰከላ ሲስተምን (SIMS) በአዲሱ የት/ት ዘመን ይተግብሩ!

ክፍያዎችን በኦንላይን ለመፈፀም፣ መረጃ አያያዝና አስተዳደርን ዲጂታል ለማድርግ ሁሉን በአንድ የያዘ አስተማማኝ መተግበርያ!

ይህንን https://sekela.app ወይንም https://sekela.app/school-registration ሊንክ በመከተልና በመመዝገብ ያለምንም ኢንስታሌሽንና ቅድመ ክፍያ ካሉበት ይጠቀሙ