TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወላይታ ሶዶ🔝

መንግስት በወላይታ ሶዶ ከተማ ዙሪያ ህገወጥ ናቸው #ባላቸው ግንባታዎች ላይ የማፍረስ #እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ የተፈጠረው አለመረጋጋት ረገብ ብሏል። ከተማዋም ወደቀደመ #ሰላማዊ እንቅስቃሴዋ እየተመለሰች ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኒውዚላንድ🔝

በኒውዚላንድ #ክሪስትቸርች ከተማ ሁለት መስጊዶች ላይ ጥቃት በመፈፀም 49 #ሰላማዊ ዜጎችን ህይዎት በማጥፋት ከተጠረጠሩ ግለሰቦች ውስጥ አንደኛው በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት ቀርቧል።

ድርጊቱን የፈፀመው ተጠርጣሪ ብሬንቶን ታራንት የሚባል ሲሆን፥ በዜግነትም አውስትራሊያዊ መሆኑ ነው የተገለፀው።

የ28 ዓመቱ ብሬንቶን ታራንት በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት የቀረበውም በነፍስ ግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ነው ተብሏል።

ፅንፈኛ #ቀኝ_ዘመም_አሸባሪ የተባለው ተጠርጣሪ #ብሬንቶን_ታራንት ፍርድ ቤቱ ያቀረበበትን ክስ በዝምታና በአርምሞ አድምጧል ነው የተባለው ።

ፍርድ ቤቱ የተጠርጣሪውን የይግባኝ መብት በመከልከል ጉዳዩን በድጋሜ ለመመልከት ለፊታችን ሚያዝያ 5 ቀጠሮ ይዟል።

በሽብር ጥቃቱ የተጠረጠሩ ሁለት ተጨማሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ፥ ሁለቱም ከዚህ በፊት በምን አይነት የወንጀል ተጠርጥረው  ፍርድ ቤት ቀርበው የማያውቁ መሆኑ ተገልጿል።

የኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር #ጃሲንዳ አርደርን ድርጊቱን የሽብር ጥቃት በማለት ያወገዙ ሲሆን፥ በጥቃቱ የተጎዱ ዜጎችን ማንነት  የመለየት ስራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጠርጣሪዎች  ድርጊቱን ለመፈፀም የተጠቀሙበት #መሳሪያ ዘመናዊና የተሻሻለ መሆኑን በመጥቀስ፥ የፀጥታ አካላት ባደረጉት #እርብርብ በፍጥነት በቁጥጥር ስር በማዋል የሚደርሰውን እልቂት ለመታደግ ተችሏል ብለዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዛሬው ውሎ...

የዛሬው #የሀረማያ_ዩኒቨርሲቲ ውሎ #ሰላማዊ እንደነበር የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ተናግረዋል። በግቢው ውስጥ መከላከያ ሰራዊት፣ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሀይል እና ፌደራል ፖሊስ ጥበቃ እያደረጉ እንደሚገኙ ጨምረው ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰላም እና መረጋጋት እየታየ ነው...

በአማራ ክልል የፀጥታ ችግር ተፈጥሮባቸው የነበሩ የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች #መረጋጋትና #ሰላማዊ ሁኔታ እንደሚታይ ተገለፀ።

የአማራ ክልል ሰላም እና ደህንነት ግንባታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኮሎኔል አለበል አማረ እንደተናገሩት፥ የፀጥታ ችግሩ ተከስቶባቸው በነበሩ በሁሉም አካባቢዎች መረጋጋት እና ሰላማዊ ሁኔታ ታይቶባቸዋል።

የአካባቢውን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት ለመመለስ የፀጥታ አካላት ከህብረተሰቡ ጋር እየሠሩ እንደሚገኙ የገለፁት ኮሎኔል አለበል፥ አጥፊዎችን በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተነግሯል።

አሁንም ቢሆን ግጭቱን ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማዛመት እና ችግሩን ለማባባስ የተለያዩ ያልተጣሩ መረጃዎችን የሚያሰራጩ ግለሰቦች በመኖራቸው ህዝቡ ከወዲሁ መጠንቀቅ እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ግጭቶቹ የተከሰቱባቸው አካባቢ ነዋሪዎች በበኩላቸው፥ ችግር ተፈጥሮባቸው የነበሩ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች የተሻለ መረጋጋት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

እንደ አስተያት ሰጭዎቹ፥ ተፈጥሮ በነበረው ችግር ምክንያት ተደናግጠው አካባቢያቸውን ለቀው ወደ ፈረዶ ውኃ እና መሀል ሜዳ ሸሽተው የነበሩ የአጣየ ከተማ ቀበሌ 01፣ 02 እና 03 ነዋሪዎች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ነው፡፡

በማጀቴም ከትናንት የተሻለ ሰላማዊ ሁኔታ እንደሚታይ ተጠቁሟል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከጅማ🔝

"የጅማ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ተማሪዎች በድጋሜ #ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ነን፡፡ ጥያቄአችን #ሳይመለስ አናቆምም!!" YZ ke JU(ጅማ ዩኒቨርሲቲ)

@tsegabwolde @tikvahethioia
የፊታችን ሀሙስ ሰልፍ ሊደረግ ነው...

#ጌታቸው_አሰፋ ሽልማት እንጅ #እስር አይገባውም' በሚል መሪ ቃል የፊታችን ሀሙስ በመቐለ ከተማ #ሰላማዊ_ሰልፍ እንደሚያደርግ የትግራይ ወጣቶች ማህበር አስታውቋል።

Via ELU/ድምጺ ወያነ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፊታችን አርብ ሰልፍ ሊደረግ ነው...

/Wolaita zone administration public relation office/

በወላይታ ዞን የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች #ሰላማዊ_ሰልፍ ለማድረግ ሲያቀርቡት የነበረው ጥያቄ ይሁንታ አግኝቷል።

ከዚህ ቀደም የህብረተሰቡን ሠላምና ፀጥታ ለማስጠበቅ ሲባል ሰልፉ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ ይታወሳል።

የወላይታ ሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን፣ ዬላጋ አደረጃጀት፣ የክብር ተሰናባች የሠራዊተ አባላት እና የንግድ ማህበራት ምክር ቤቶች ሠላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ በግንቦት 5/2011 ዓ ም በጠየቁት መሠረት ሰላማዊ ሰልፉ መፈቀዱ ታውቋል።

ሰልፉ በግንቦት 9/2011 ዓም ከጧቱ 12:00 ሰዓት እስከ 4:00 ሰዓት ድረስ የሚካሄድ መነሻው አዲሱ የወላይታ ዞን አስተዳደር ሆኖ በፍሬው አልታዬ ጎዳና የወላይታ ጉታራ አዳራሽን አቋርጦ በወላይታ ሶዶ ሁለገብ ስታዲየም የሚዘልቅ መሆኑ ታውቋል።

ከነዚህ ከተፈቀዱ ቦታዎች ውጪ ሰላማዊ ሰልፍ ባለማድረግ እና ከፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ የዞኑ አስተዳደሩ አሳስቧል።

/Wolaita zone administration public relation office/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ👆በዛሬው ዕለት በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች መምህራን #ሰላማዊ_ሰልፍ ሲያካሂዱ ውለዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጎንደር #Gondar

ጎንደር ከተማ #ሰላማዊ መሆንዋን ምክትል ከንቲባ በሪሁን ካሣዉ ገልፀዋል። ትላንት አነስተኛ ውዝግብ ከተማ ውስጥ መፈጠሩን ያነሱት ምክትል ከንቲባው የነበረውን አነስተኛ ዉዝግብ ተጠቅመዉ ረብሻ ለማስነሳት የሞከሩ እና አንዳንድ ያልተገባ ነገር ለመፈፀም የሞከሩ፤ ድርጊታቸዉን ሳይፈፅሙ በቁጥጥር ስር አውለናቸዋል፤ #ከጀርባቸዉ ማን እንዳለም እያጣራን ነዉ ሲሉ ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል።

Via #DW
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADDISABEBA

በአዲስ አበባ ከተማ የአዲስ ዓመት በዓል የድንገተኛ አደጋና ከወንጀል ድርጊቶች ነጻ በሆነ መልኩ በሰላማዊ መንገድ መከበሩን የከተማዋ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የኮሚሽኑ የኢንዶክትሪኔሽንና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ፋሲካ ፈንታው ለኢዜአ  እንደገለጹት፤ የአዲስ ዓመት በዓል ከዋዜማው ጀምሮ እጅጉን #ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሯል። ይህ ዜና እስከተዘገበበት ድረስ “በትራፊክ አደጋ ሰው አልሞተም፤ ከባድ የአካል ጉዳት አልደረሰም፤ ከጸጥታና ከወንጀል ጉዳይ ጋር በተያያዘም ምንም የተከሰሰተ ነገር የለም” ብለዋል።

Via ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸በጅማ ከተማ የደመራ በዓል ስነ ስርዓት #ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል። በስፍራው የሚገኙ የበዓሉ ተሳታፊዎች ያለውን ድባብ በፎቶ አስደግፈው ልከውልናል።

PHOTO: MILVER/TIKVAH-ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Election2013

የሀገር መከላከያ ሰራዊት 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አሳውቋል።

6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ይካሄዳል።

የመከላከያ ሚኒስቴር ምርጫው #ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ ገልጸዋል፡፡

ከምርጫው በተጨማሪም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር ውሃ ሙሌት እንዲከናወን እና በመላው ሀገሪቱ ወንጀለኛን አድኖ ለመያዝ የመከላከያ ሰራዊቱ ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ምርጫው በሰላማዊና በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲጠናቀቀቅ ሁሉም የበኩሉን ሃላፊነት እንዲወጣ ጥሪ መቅርረቡን አሐዱ ኤፍ ኤም 94.3 ዘግቧል።

PHOTO : FILE
@tikvahethiopia
በፎቶሾፕ ከሚቀናበሩ የምርጫ ውጤቶች ተጠንቀቁ !

የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት እያሳወቁ ይገኛሉ።

በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት ናቸው የተባሉ ወረቀቶች እየተለጠፉ ነው።

ነገር ግን ወረቀቶቹ ላይ ያሉትን ቁጥሮች በፎቶሾፕ የመነካካት፣ የማስተካከል ምልክቶችን ታዝበናል።

በተለይ የቲክቫህ አባላት በሙሉ ፦

1ኛ. ዘመኑ የረቀቀ ነውና የምርጫ ውጤትን በተመለከተ ትክክለኛው ሪፖርት እስኪላክላችሁ ታገሱ

2ኛ. ድምፅ የሰጣችሁበት የምርጫ ጣቢያ #በአካል ተገኝታችሁ የተለጠፈውን ውጤት እንድትመለከቱ እናበረታታለን።

የውጤት ጉዳይ በጥንቃቄ ካልተያዘ እስካሁን የተመጣበትን #ሰላማዊ ሂደትን ሊያበላሽ ስለሚችል ከሀሰተኛ መረጃዎች/በይፋ በምርጫ ቦርድ ካልተረጋገጡ ሪፖርቶች ሁሉ እንድትርቁ አደራ እንላለን።

@tikvahethiopia
" አዲስ አበባ #ሰላማዊ የአፍሪካ ከተማ ናት " - አውሪሊያ ካላብሮ

በኢትዮጵያ የተመድ (UN) የኢንዱስትሪ ልማት ቀጠናዊ ቢሮ ዳይሬክተሯ ሚስ አውሪሊያ ካላብሮ አዲስ አበባ እጅግ ሰላማዊዋ የአፍሪካ ከተማ ናት ብለዋል።

ዳይሬክተሯ ይህንን የተናገሩት በአፍሪካ ሌዘር ፣ ጨርቃ ጨርቅ ፣ ፋሽን እና የዘርፉ ቴክኖሎጂዎች ኤግዚቢሽን መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።

አውሪሊያ ካላብሮ ፥ " አዲስ አበባ ከተማ ከሚወራው እጅግ ተቃራኒ በሆነ ሁኔታ በአፍሪካ እጅግ ሰላማዊ ከሆኑ ከተሞች አንዷ ናት " ሲሉ ተናግረዋል።

በዚህም ዓለም አቀፍ የቆዳና የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪና የዘርፉ ነጋዴዎች እዚህ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን ላይ መገኘታቸውን ገልፀዋል።

ኤግዚቢሽኑ ባለፉት 3 ዓመታት የኮቪድ 19 ካደረሰው ጫና በኋላ አዲስ የንግድ ስልቶችን በመማር የተዘጋጀ ነውም ብለዋል።

ምንጭ፦ አሻም ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #USA

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ዴቪድ ሳተርፊልድ ዛሬ እና ነገ በኢትዮጵየ፣ አዲስ አበባ ቆይታ እንደሚኖራቸው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት መረጃ ያሳያል።

ልዩ መልዕክተኛ ሳተርፊልድ ከኢትዮጵያ መንግስት፣ ከአፍሪካ ህብረት እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣናት እንዲሁም ከሰብአዊ ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ተገናኝተው ይመክራሉ።

አሜሪካ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት #ሰላማዊ መቋጫ እንዲያገኝ ጥረት እያደረገች መሆኑ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
" የክልል እንሁን ጥያቄዎች ዘላቂ ሰላምን በሚያመጣ መልኩ ሊፈቱ ይገባል " - እናት ፓርቲ

እናት ፓርቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ የ " ክልል እንሁን " ጥያቄዎች ዘላቂ ሰላምን በሚያመጣ መልኩ ሊፈቱ እንደሚገባ አሳስቧል።

ፓርቲው የክልልነት ጥያቄን በተመለከተ የሀገሪቱን ተጨባጭ ኹኔታና የሕዝቡን ጥያቄ ከግምት ውስጥ በማስገባት የሚከተሉትን የመፍትሔ ሀሳቦች ጠቁሟል።

የመፍትሄ ሀሳቦች ፦

1. የሀገሪቱ አብዛኛው ችግር የሚመነጨው ከሕገ መንግሥቱ " የክልል አወቃቀር " ጋር በተያያዘ መሆኑ ታውቆ ከጊዜያዊ መፍትሔ ይልቅ ዘለቄታዊ መፍትሔና የችግሩ ምንጭ ላይ ያተኮረ አፋጣኝ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዲጀመር ጠይቋል።

2. በአሁኑ ሰዐት የክልልነት ጥያቄ እየጠየቁ ላሉ የማኅበረሰባችን ክፍሎች መንግሥት የኃይል አማራጭን ከመከተል ይልቅ ከሕዝቡ ጋር በቅርበት በመነጋገርና በመግባባት ብቻ ችግሩን ለመፍታት ጥረት እንዲያደርግ አሳስቧል።

3. ሰላም ወዳድ የሆነው ሕዝብ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች እጅግ #ሰላማዊ በሆነ መንገድ ውጤት ላይ መድረስ እንጂ አላስፈላጊ መሥዋዕትነት ከሚያመጡ ድርጊቶች እንዲቆጠብ ጥሪ አስተላልፏል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ደሴ ! ከደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የከተማው ሰላም እና ደህንነት ላይ መክሮ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም ፦ - የምግብ ቤቶች ፣ የምሽት መጠጥ ቤቶች/ግሮሰሪዎች/ ከምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በማንኛውም ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ ተከልክሏል። - ማንኛውም ምርት ላይ የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል። - በመፈናቀል…
#Update

የደሴ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በንቃት በመጠበቅ የከተማዋን ሰላም ሊያስጠብቁ እንደሚገባ የደሴ ከተማ አስተዳደር ገልጿል።

ነዋሪዎች በሚነዙ ሀሰተኛ ወሬዎች፣ መረጃዎችና አሉባልታ አትደናገሩ ብሏል።

ማንኛውም የተለየና አጠራጣሪ ነገር ሲመለከቱ ነዋሪዎች ለጸጥታ ኃይል በማሳወቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ተጠይቋል።

ከተለያዩ አከባቢዎች ለመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ነገር ግን በዚህም መሃል ሰርገው ሊገቡ የሚችሉ የጥፋት ኃይሎች ካሉ በመከታተል ለሚመለከተው የጸጥታ ኃይል መጠቆም እንደሚገባ አስተዳደሩ ገልጿል።

የባንክና መሰረታዊ አገልግሎቶች ክፍት ሆነው እየተሰጡ መቀጠል እንዳለባቸው አፅንኦት የተሰጠ ሲሆን አገልግሎት በሚያቋርጡና ዋጋ አላግባብ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ ማስጠንቀቂያ ተላልፏል።

በከተማው የታወጀውን አሰገዳጅ ህግ ሁሉም ሊያከብረው የሚገባ ሲሆን ጥሰት የሚታይ ከሆነ አስተዳደሩ ትእግስት እንደማያደርግና እርምጃ እንደሚወስድ አጥብቆ አስጠንቅቋል።

በሌላ በኩል ፤ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በየመዝናኛ ቤቶችና ህዝብ በሚሰበሰብበት ቦታዎች ላይ አሉባልታ ወሬ በማናፈስ ህብረተሰቡ እንዳይረጋጋ በማድረግ ኗሪው በፍርሃት ከተማውን ለቆ እንዲወጣ ተልዕኮ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች እንዳሉ ገልጿል።

ህብረተሰቡ ይህንን በማወቅ በአሉባልታ ሳይደናገር የራሱን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክት አስተላልፏል።

የከተማው ጸጥታ ማዋቅር የከተማውን ሰላም ለማስጠበቅ እየሰራ መሆኑንም የገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ተደራጅቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል።

ወልድያን በተመለከተም ዛሬም #ሰላማዊ ሁኔታ የቀጠለ ሲሆን ነዋሪዎች ከአሉባልታ በመራቅ አካባቢያቸውን በንቃት እንዲጠብቁና ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update | #Pretoria

የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ዛሬ ከሰዓት በአፍሪካ ህብረት መሪነት በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ስላለው " የሰላም ንግግር " ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ እንደሚሰጡ ተነግሯል።

ኦባሳንጆ ፤ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት #ሰላማዊ መፍትሄ ያገኝ ዘንድ በአፍሪካ ህብረት መሪነት እየተካሄደ ስላለው የሰላም ንግግር በተመለከተ በፕሪቶሪያ ሆነው ነው መግለጫውን የሚሰጡት።

ባለፈው ጥቅምት 15 ቀን 2015 ዓ/ም በደቡብ አፍሪካ የጀመረው የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት የሰላም ንግግር እሁድ እንደሚጠናቀቅ ቢገለፅም ለተጨማሪ ቀናት ተራዝሞ የሰላም ንግግሩ እንዲቀጥል ተደርጓል።

በዚህ ሁሉ ጊዜ የሰላም ንግግሩ ይዘት ፣ አጀንዳ እና የደረሰበት ደረጃ በተመለከተ ምንም መረጃ ሳይወጣና የንግግሩ አመቻቾች አጠቃላይ ሂደቱ ከሚዲያዎች በራቀ ሁኔታ እንዲሄድ አድርገዋል። ዛሬ ከሰዓት ግን ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ የሰላም ንግግሩን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን ይፋዊ መግለጫ ይሰጣሉ።

ውድ ቤተሰቦቻችን ፤ የዛሬውን የሰዓት መግለጫ በተመለከተ ይህን መረጃ ያገኘነው ከDICRO South Africa ነው።

@tikvahethiopia