#ETHIOPIA #USA

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ዴቪድ ሳተርፊልድ ዛሬ እና ነገ በኢትዮጵየ፣ አዲስ አበባ ቆይታ እንደሚኖራቸው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት መረጃ ያሳያል።

ልዩ መልዕክተኛ ሳተርፊልድ ከኢትዮጵያ መንግስት፣ ከአፍሪካ ህብረት እና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣናት እንዲሁም ከሰብአዊ ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ተገናኝተው ይመክራሉ።

አሜሪካ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት #ሰላማዊ መቋጫ እንዲያገኝ ጥረት እያደረገች መሆኑ ይታወቃል።

@tikvahethiopia