TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በአኩን ሰዓት #Facebook ኢትዮጵያ ውስጥ የስድብ እና የጥላቻ ንግግሮችን ማሰራጫ፣ የግጭት መጠንሰሻ፣ የጦርነት መቀስቀሻ፣ የሰላም ማደፍረሻ እየሆነ በመምጣቱ ለ1 ሳምንት እራሴን ከፌስቡክ አግልያለሁ!

ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነት!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፌስቡክ #የጥላቻ_ንግግርን በተመለከተ ያለውን ፖሊሲ እንደገና ሊከልስ ይገባል። #facebook🚫 #ፌስቡክ🚫

#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOIA
ለሽብር ያነሳሳል...

የአውሮፓ ሕብረት በሚያዚያ 2017 ባወጣው መረጃ ላይ #ስድብ አዘል የማሕበራዊ ድረገጽ አስተያየቶች ሰዎችን እንደሽብር ላሉ #መጥፎ ሀሳቦች የሚያነሳሳ እንደሆነ ይገልጽና፣ በማህበራዊ ድረገጾች ላይ #ክትትል ማድረግ ያስፈልጋል ሲል ይመክራል፡፡ የሕብረቱ ውሳኔ የተሳዳቢዎቹን ምክንያት አይገልጽም፡፡ ውጤቱ ወደ ሽብርተኝነት ያድጋል ሲል ማስጠንቀቁ ግን አልቀረም፡፡

#Facebook🚫

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምዕራፍ ሁለት!

ለ2 ሳምንት የሚቆይ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ #NoHateSpeechMovement /ETHIOPIA/ በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጩ ያሉ የጥላቻ ንግግሮችን የምንዋጋበት፤ የተለያዩ መልዕክቶችን ፖስት በማድረግ ጥላቻን የምናሸንፍበት ሳምንታት ይሆናሉ! #ቲክቫህኢትዮጵያ

ዘመቻው የሚካሄደው፦
#Facebook
#Telegram
#Twitter ላይ ይሆናል!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
🚫STOP HATE SPEECH🚫

#TikvahEthiopia #Facebook #Telegram #Twitter ሀገራችንን እናድን! የጥላቻ ንግግሮች ሀገራችንን ወደአስፈሪ ሁኔታ ውስጥ እየከተታት ይገኛል። ሁላችም ከጥላቻ ንግግሮች ራሳችንን በማራቅ ሀገራዊ ሀላፊነታችንን እንወጣ!

#ከጥላቻ_ንግግሮች_እንቆጠብ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FaceBook

ፌስ ቡክ #ከጥላቻ_ንግግር ፖሊሲው ጋር የሚጣረሱ መልዕክቶችን በቀጥታ በሚያሠራጩ ተጠቃሚዎች ላይ አዲስ የቁጥጥር ህግ ሊያስተዋውቅ ነው። በኒውዚላንድ ክሪስት ቸርች መስጊዶች ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ ለተወሰነ ጊዜ ተጠቃሚዎችን ከፌስቡክ ማገድ እንደ አንድ የመፍትሔ ሃሳብ ቀርቧል። በፓሪስ በሚካሄደውና በፈረንሳዩ ፕሬዚደንት ኢማኑኤል ማክሮንና በኒውዚላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ጃሲንዳ አርደርን በሚመራው ጉባዔ ላይም ፅንፈኛና ተንኳሽ የሆኑ ንግግሮችን ለመቀነስ የሚረዱ ሃሳቦች ይቀርቡበታል ተብሏል። በመስጊዶቹ ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ በስፋት ከተሠራጨው ተንቀሳቃሽ ምስል በኋለ ፌስቡክ ትችት አጋጥሞታል። በኒውዚላንድ ክሪስትቸርች ከተማ ሁለት መስኪዶች ላይ በተከፈተ ተኩስ 49 ሰዎች ሲገደሉ ብዙዎች መጎዳታቸው ይታወሳል።

Via #BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የጥላቻ_ንግግር #facebook የጀርመን ባለስልጣናት የማህበራዊ ትስስር ድረ ገጽ የሆነው ፌስቡክ የሀገሪቱን የጥላቻ ንግግር ህግ በመጣሱ በ2 ነጥብ 3 ሚሊየን የአሜሪካ እንዲቀጣ ውሳኔ ማሳለፋቸውን አስታውቀዋል።

ባለስልጣናቱ በፌስቡክ ላይ ቅጣቱን በትናንትናው እለት ያሳለፉ ሲሆን፥ ቅጣቱ የተላለፈውም ህጉን የጣሱ ይዘቶችን በፌስቡክ ገፅ ላይ ሲሰራጩ ምንም አይነት የማስተካከያ እርምጃ ባለመውሰዱ ነው ተብሏል። የጀርመን የፌደራል ፍትህ ቢሮ ባወጣው መግለጫ፥ ፌስቡክ የጥላቻ ንግግር ህግ የጣሱ ይዘቶች እና ህዝቡን የሚረብሹ ምስሎች ሲለቀቁ እርምጃ ባለመውሰዱ ውሳኔው እንደተላለፈበት አስታውቋል።

ፌስቡክ ህገ ወጥ የተባሉ ይዘቶች ላይ የወሰደውን እርምጃም ግልጽ አድርጎ በሪፖርት እንዳላቀረበም ነው ቢሮው ያስታወቀው። በጀርመን ህግ መሰረት ፌስቡክን ጨምሮ ሁሉም የማህበራዊ ትስስር ድረ ገፆች በበድረ ገፆቻቸው ላይ የሚያጋጥሙ ህገ ወጥ ይዘቶች ላይ የሚወስዷቸውን እርምጃዎች በየስድስት ወሩ በሪፖርት ማሳወቅ እንዳለባቸው ተደንግጓል።

ፌስቡክን ለቅጣት ከዳረጉት ምክንያቶች ውስጥም አንዱ የተሟላ ሪፖርት አለማቅረቡ አንደሆነም ነው እየተነገረ ያለው። የፌስቡክ ኩባንያ ግን በተላለፈበት የቅጣት ውሳኔ ላይ እስካሁን ምላሽ እንዳልሰጠ እና የይግባኝም አንዳልጠየቀ ነው መረጃዎች የሚያመላክቱት።

ምንጭ፦ www.cnet.com
🗞ቀን ሰኔ 26/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FaceBook

ፌስቡክ ከአፍሪካ ቼክ ጋር በመተባበር የሦስተኛ ወገን የእውነታ ማረጋገጫ ፕሮግራሙን ለማጠናከር በርካታ የአፍሪካ ቋንቋዎችን በፕሮግራሙ ውስጥ ማካተቱን ይፋ አደረገ።

እርምጃው በፌስቡክ ገጽ ላይ የሚሰራጩ ዜናዎችን እውነተኝነት ለማረጋገጥ እና የተሳሳቱ መረጃዎችን ለመቀነስ ያግዛል ተብሏል።

እ.አ.አ ከ2018 ጀምሮ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ናይጄሪያ፣ ሴኔጋል እና ካሜሩን ውስጥ የተጀመረው ፕሮግራሙ አሁን በእነዚህ ሀገራት ውስጥ ያሉ ተጨማሪ ቋንቋዎችን ማካተቱ ተነግሯል።

በተጨማሪነት ከተካተቱት ቋንቋዎች ውስጥም ከናይጄሪያ ዮሩባ እና ኢግቦ፣ ከኬንያ ስዋሂሊ፣ ከሴኔጋል ዎሎፍ፣ ከደቡብ አፍሪካ አፍሪካን፣ ዙሉ፣ ሴትስዋና፣ ሶቶ፣ ሰሜናዊ ሶቶ እና ደቡባዊ ንዴቤሌ ይገኙበታል።

በፌስቡክ የአፍሪካ የፐብሊክ ፖሊሲ ጉዳዮች ዋና ኃላፊ የሆኑት ኮጆ ቦክዬ የቋንቋዎቹን መካተት ምክንያት በማድረግ በሰጡት መግለጫ፣ "አጋዥ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ በመረጃ የበለጸገ እና አካታች የሆነ ማኅበረሰብ ለመገንባት ከምናደርገው ጥረት ጎን ለጎን በገጻችን ላይ የሚሰራጩ ሐሰተኛ ዜናዎችን በመታገሉ ረገድ አቅማችንን አጎልብተን መሥራቱን እንቀጥላለን" ብለዋል።

የሦስተኛ ወገን የእውነታ ማረጋገጫ ፕሮግራሙም የዚሁ ጥረት አካል መሆኑን ነው የገለጹት። የአፍሪካ ቼክ ዋና ዳይሬክተር ኖኮ ማክጋቶ በበኩላቸው፣ በፕሮግራሙ ውስጥ ተጨማሪ ቋንቋዎች መካተታቸው እንዳስደሰታቸው እና በርካታ ቋንቋዎች በሚነገርባቸው እንደ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ እና ሴኔጋል ውስጥ በተለያዩ የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች የእውነታ ማረጋገጫ መተግበሩ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ፌስቡክ/ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የታገቱ ተማሪዎችን አስመልክቶ የሶሻል ሚዲያው ንቅናቄ!

የሶሻል ሚዲያ ንቅናቄዎች ምን ይመስላሉ ብለን ቃኝተን ነበር ከደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ የተጠለፉ ተማሪዎችን አስመልክቶ በርካታ ሰዎች እነዚህን ፎቶዎች ተጠቅመው መንግስት እውነታውን እንዲገልጽ ሲጠይቁ አስተውለናል፡፡ አብዛኞቹ ልጄን መልሱልኝ የሚሉና #Bringbackourstudents የሚሉ ናቸው፡፡

#Facebook
#Tiwtter
#instagram

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#FACEBOOK

ፌስቡክ ከዘጠኝ አጋር አካላት ጋር በመተባበር ለአፍሪካ የኢንተርኔት  መረጃ ደህንነት እሰራለሁ ብሏል፡፡ ፌስቡክ ከሰሃራ በርሃ በታች ላሉ  አፍሪካ አገራት የኢንተርኔት መረጃ  አጠቃቀምንና አገልግሎቱን ለማሳደግ ከዘጠኝ መንግስታዊ እና  መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር  እንደሚሰራ አስታውቋል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FaceBook

ፌስቡክ ተጠቃሚዎቹ የተለያዩ ማኅበራዊና ፓለቲካዊ ቡድኖችን እንዲቀላቀሉ የሚጠቁም መልዕክት ማስተላለፍ እንደሚያቆም አስታወቀ።

ይህ ውሳኔ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች በገጻቸው ላይ የሚያዩትን ፓለቲካ ነክ ይዘት ከመቀነስ ጋር የተያያዘ ነው።

የአሜሪካ ምርጫ ሲካሄድ ፌስቡክ ለሳምንታት ያህል ፓለቲካዊ መልዕክቶችን ቀንሶ ነበር። አሁን ይህንን አሠራር በሌሎች አገራትም እንደሚተገብር ተገልጿል።

የፌስቡክ መስራች ማርክ ዙከርበርግ "ሰዎች ፓለቲካና ግጭት መመልከት አይፈልጉም" ሲል ተናግሯል።

ማርክ ዙከርበርግ እንደሚለውም፤ ሰዎች ፌስቡክ ላይ የሚቀላቀሏቸው ቡድኖች "ጤናማና ቀና" እንዲሆኑ ይፈለጋል።

"ከፖሊሲያችን ጋር ባይጻረሩም ሰዎች እንዳይገቡ የምንፈልጋቸው ቡድኖች አሉ" ብሏል።

ማኅበራዊ እንዲሁም ፓለቲካዊ ቡድኖችን የፌስቡክ ተጠቃሚዎች እንዲቀላቀሉ የሚላኩ ማስታወቂያዎችን ረዘም ላለ ጊዜ እንዳገዱም ገልጿል።

"ውጥረትን ለማርገብና በማኅበረሰቡ ዘንድ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ውይይት እንዲኖር የጀመርነው ሥራ አንድ አካል ነው" ሲል መስራቹ መናገሩን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#Facebook

ፌስቡክ የኮቪድ-19 ክትባት መርዛማ ነው ፣ አደገኛ ነው ፣ ኦቲዝም ያስከትላል በሚል ፖስት የሚደረጉ ፅሁፎችን እንደሚያነሳ በትላንትናው ዕለት አሳውቋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Facebook

ፌስቡክ ታሊባንን እንደ አሸባሪ ቡድን እንደሚመለከተውና ከቡድኑ ጋር የተያያዙ መልዕክቶችን እንደሚያቅብ አስታወቀ።

ፌስቡክ ታሊባንን የሚያደንቁ ይዘቶችን፣ የቡድኑን መልዕክቶችን አግዳለሁ ብሏል።

ይህን ሳንሱር እንዲሠሩለት አንድ ልዩ የአፍጋኒስታን ባለሙያዎች ቡድን ማዋቀሩን እና በእነዚህ ባለሙያዎች እየታገዘ የታሊባን ይዘቶችን ወዲያውኑ ከፌስቡክ ሰሌዳዎች ላይ እንደሚያጠፋ ፌስቡክ ዝቷል።

ታሊባን ለዓመታት መልዕክቶቹን በመላው ዓለም ለማድረስ ፌስቡክን እንደ አንድ መገናኛ ብዙኃን ሲጠቀምበት ቆይቷል።

ታሊባን አሁን የመንግሥትን መዋቅር መቆጣጠሩ ማኅበራዊ የትስስር መድረኮች ቡድኑን እንዴት ማስተናገድ እንዳለባቸው በድጋሚ እንዲያጤኑ እያደረጋቸው ነው።

የፌስ ቡክ ቃል አቀባይ ፥ "በአሜሪካ ሕግ ታሊባን አሸባሪ ቡድን ነው። ይህ ሕግ እኛም በዚያው ሁኔታ እንድናያቸው የሚያደርገን ነው። በመሆኑም ከታሊባን ጋር የሚያያዙ ማናቸውንም መልዕክቶች እናቅባለን" ብለዋል።

ፌስቡክ ዋንኛ የአፍጋኒስታን ቋንቋ የሆኑትን ዳሪ እና ፓሽቶን የሚናገሩ አፍጋኒስታዊያን ተወላጆችን ለዚሁ ተግባር ሲል መልምሎ፣ ቀጥሮ እያሠራ እንደሆነ ተናግሯል።

የፌስቡክ ኩባንያ እቀባውን ተግባራዊ የሚያደርገው በእህት ኩባንያዎቹ በኢንስታግራምና በዋትስአፕ የትስስር መድረኮች ጭምር ነው።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

@tikvahethiopia
#Facebook

ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ ፣ ኢንስታግራም መተግበሪያዎች መስራት አቁመዋል።

በፌስቡክ ስር የሚገኙት እኚህ መተግበሪያዎች በተለያዩ የዓለም ሀገራት ሙሉ ለሙሉ መስራት አቁመዋል።

እዚሁ ሀገራችን ላይም ከ25 ደቂቃዎች በፊት አገልግሎታቸው ተቋርጧል።

እስካሁን መተግበሪያዎቹ መስራት ያቆሙበት ምክንያት አልታወቀም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Facebook ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ ፣ ኢንስታግራም መተግበሪያዎች መስራት አቁመዋል። በፌስቡክ ስር የሚገኙት እኚህ መተግበሪያዎች በተለያዩ የዓለም ሀገራት ሙሉ ለሙሉ መስራት አቁመዋል። እዚሁ ሀገራችን ላይም ከ25 ደቂቃዎች በፊት አገልግሎታቸው ተቋርጧል። እስካሁን መተግበሪያዎቹ መስራት ያቆሙበት ምክንያት አልታወቀም። @tikvahethiopia
#Facebook

ፌስቡክ ፣ ዋትስአፕ ፣ ኢንስታግራም እና ሜሴንጀር በአሁኑ ወቅት በበርካታ አገሮች ውስጥ አገልግሎታቸው መቋረጡን ኔትብሎክስ አሳውቋል።

ክስተቱ በአገር ደረጃ ካለ የኢንተርኔት ግንኙነት ጋር ያልተገናኘ መሆኑንም ጠቁሟል።

እስካሁን በፌስቡክ በኩል ችግሩ በምን ምክንያት እንደተፈጠረ የተገለፀ ነገር የለም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ከ6 ሰዓታት በላይ ተቋርጠው የቆዩት ፌስቡክ ፣ ዋትስአፕ ፣ ኢንስታግራም እንዲሁም ሜሴንጀር ወደ አገልግሎት ተመልሰዋል። ፌስቡክ ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ ከመጠየቅ ውጭ እስካሁን ችግሩ በምን ምክንያት እንደተፈጠረ ማብራሪያ አልሰጠም። እንደብሉምበርግ ዘገባ ከሆነ በፌስቡክ መቋረጥ በ5 ሰዓታት ውስጥ ብቻ የማርክ ዙከርበርግ የግል ሃብት በ7 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ዝቅ ብሏል። @tikvahethiopia
#Facebook

ፌስቡክ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ትላንት ከ6 ሰዓታት በላይ አገልግሎቶቹ የተቋረጡበት ምክንያት ከተሳሳተ የአወቃቀር ለውጥ ጋር የተያያዘ ነው ብሏል።

የተሳሳተ የአወቃቀር ለውጥ መከሰቱን ተከትሎ በአጠቃላይ የኩባንያውን ውስጣዊ መሳሪያዎች እና ስርዓቶች ላይ ተፅእኖ በማሳደሩ ችግሩን ለመፍታት አዳጋች አድርጎታልም ሲል ገልጿል።

መግለጫው አክሎም "ተቋርጠው በነበሩበት ሰዓታት የተጠቃሚዎች ግላዊ መረጃ ተጥሷል የሚል ማስረጃ የለም" ብሏል።

የፌስቡክ መስራች ማርክ ዙከርበርግ አገልግሎቶቹ በመቋረጣቸው ምክንያት ለተጎዱ ሰዎች ይቅርታ መጠየቃቸውን #BBC / ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopia