TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#LIVE በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ሪፖርቱን ከስካይ ላይት ሆቴል እያቀረበ ነው። ከላይ ያለውን Voice Chat 'Join' በማለት በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ። #TikvahFamily @tikvahethiopia
የAU የመጀመሪያ /ቀዳሚ የምርጫ 2013 ትዝብት ሪፖርት👆

በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን የምርጫ 2013 የመጀመሪያ/ቀዳሚ ሪፖርት ዛሬ አቅርቧል።

ሪፖርቱን የቡድኑ መሪ ኦሊሰንገን ኦባሳንጆ በንባብ አሰምተዋል።

ቡድኑ በ5 ክልሎችና 2 ከተሞች የምርጫውን አባላቱን ልኮ ምርጫውን መታዘቡን አስታውቋል፡፡

በአንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች እንግልትና ወከባ ፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ስጋቶች ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችን የማዋከብና የማንገላታት ችግሮች ፣ የቁሳቁስ እጥረት ችግር ምርጫው ላይ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አሳውቋል።

ከዚህ በተረፈ ግን ምርጫው ሰላማዊ ፣ ተአማኒ በሆነ ሁኔታ መከናወኑን ገልጿል።

የምርጫ ውጤት በሚመለከተው አካል ይፋ እስኪሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲጠባበቅ ቡድኑ ጥሪ አቅርቧል።

ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
የ40/60  መቶ በመቶ ከፋዮች ተፈረደላቸው።

40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መቶ በመቶ የከፈሉ ከ700 በላይ ተመዝጋቢዎች ተወሰነላቸው።

በቀድሞ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም እጣ የወጣባቸው የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ፣ መቶ በመቶ ክፍያ የፈጸሙ ቅድሚያ ለነሱ ሳይሰጥ እጣ መውጣቱን በመቃወም በፍርድ ቤት አሳግደው ነበር።

ሲከራከሩ ከርመው ዛሬ ሰኔ 16 ቀን 2013 ዓ.ም የታገደው ቤት እንዲሰጣቸው ፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጥቷል።

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tikvahethiopia
#ሪፖርት

የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን በተመለከተ ቃላቸውን ሰጥተውናል።

በአጠቅላይ ምርጫው ሰላማዊ መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ፣ የተለያየ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውድድሩን ህግ በማክበር ፍፁም ነው ባይባልም የተሻለ ውድድር ስሜት የተፈጠረበት እና የህዝብ መነሳሳት የታየበት አበረታች የሚባል ሂደት ነበር ብለዋል።

ነገር ግን ምርጫው እንከን አልባ እና ፍፁም ነበር ማለት እንዳልሆነ ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ አሳውቀውናል።

ምርጫው ላይ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ እንደሆነም አንስተዋል።

ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ ፥ "የትኛውም ምርጫ ፍፁም ሆኖም አያውቅም፣ ሊሆንም አይችልም፤ ምርጫ ሂደት ነው የምንማርበት ነው ከዚህ ምርጫ የተሻለ አፈፃፀም ደግሞ በሚቀጥለው ይታያል ብዬ አስባለሁ" ብለዋል።

* የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
Audio
AudioLab
#ምርጫ2013

ምርጫውን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የሰጡን አጭር ገለፃ።

@tikvahethiopia
#EthiopianAirlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ' ሙሉ በሙሉ ' የኮቪድ-19 ክትባት በወሰዱ ሰራተኞች በረራ ማድረግ መጀመሩን ዛሬ አሳውቋል።

የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ተወልደ ገብረማርያም ፥ በረራዎችን ሙሉ በሙሉ ክትባት በወሰዱ ሠራተኞች በማድረጋችን ተደስተናል ብለዋል።

አክለውም ፥ "ይህንን ማድረጋችን የሰራተኞቻችንን እና የደንበኞቻችንን የጤና ደህንነት በመጠበቅ ረገድ ትልቅ እርምጃ ነው" ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ተወልደ፥ በመላው ዓለም በኮቪድ-19 ክትባት በመተማመን ለንግድ ፣ ለቪኤፍአር እና ለቱሪዝም የሚጓዙ መንገደኞች ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ ተበረታተናል ብለዋል።

አየር መንገዱ ለሰራተኞቹ እንዲሁም ለባለድርሻ አካላቱ ከ37,000 በላይ የክትባቶችን ገዝቶ ማስገባቱን አቶ ተወልደ አሳውቀዋል።

በሌላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ መረጃ ፦ ወደ ኤርትራ #አስመራ ተቋርጦ የነበረው የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት ከዛሬ ሰኔ 16 ቀን 2013 ጀምሮ የሚቀጥል መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

በዘንድሮ ምርጫ የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች ተሳትፎ ምን ይመስላል ?

በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ተሳትፎና የሚዲያዎች ሚና ምን እንደሚመስል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ማህበር ሥራ አስፈጻሚዎች ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በቀጥታ በVoice Chat አጭር ገለፃ ያደርጋሉ።

ገለፃ የሚያደርጉት ፡
- ጋዜጠኛ ሲሳይ ሳህሉ
- ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ
- ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ናቸው።

(ከምሽት 2:10 - 2:40 ድረስ)

@tikvahethiopia