የAU የመጀመሪያ /ቀዳሚ የምርጫ 2013 ትዝብት ሪፖርት
👆በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን የምርጫ 2013 የመጀመሪያ/ቀዳሚ ሪፖርት ዛሬ አቅርቧል።
ሪፖርቱን የቡድኑ መሪ ኦሊሰንገን ኦባሳንጆ በንባብ አሰምተዋል።
ቡድኑ በ5 ክልሎችና 2 ከተሞች የምርጫውን አባላቱን ልኮ ምርጫውን መታዘቡን አስታውቋል፡፡
በአንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች እንግልትና ወከባ ፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ስጋቶች ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችን የማዋከብና የማንገላታት ችግሮች ፣ የቁሳቁስ እጥረት ችግር ምርጫው ላይ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አሳውቋል።
ከዚህ በተረፈ ግን ምርጫው ሰላማዊ ፣ ተአማኒ በሆነ ሁኔታ መከናወኑን ገልጿል።
የምርጫ ውጤት በሚመለከተው አካል ይፋ እስኪሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲጠባበቅ ቡድኑ ጥሪ አቅርቧል።
ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia