TIKVAH-ETHIOPIA
#LIVE በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት ምርጫ ታዛቢዎች ቡድን ሪፖርቱን ከስካይ ላይት ሆቴል እያቀረበ ነው። ከላይ ያለውን Voice Chat 'Join' በማለት በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ። #TikvahFamily @tikvahethiopia
የAU የመጀመሪያ /ቀዳሚ የምርጫ 2013 ትዝብት ሪፖርት👆

በኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን የምርጫ 2013 የመጀመሪያ/ቀዳሚ ሪፖርት ዛሬ አቅርቧል።

ሪፖርቱን የቡድኑ መሪ ኦሊሰንገን ኦባሳንጆ በንባብ አሰምተዋል።

ቡድኑ በ5 ክልሎችና 2 ከተሞች የምርጫውን አባላቱን ልኮ ምርጫውን መታዘቡን አስታውቋል፡፡

በአንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች እንግልትና ወከባ ፤ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ስጋቶች ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎችን የማዋከብና የማንገላታት ችግሮች ፣ የቁሳቁስ እጥረት ችግር ምርጫው ላይ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አሳውቋል።

ከዚህ በተረፈ ግን ምርጫው ሰላማዊ ፣ ተአማኒ በሆነ ሁኔታ መከናወኑን ገልጿል።

የምርጫ ውጤት በሚመለከተው አካል ይፋ እስኪሆን ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲጠባበቅ ቡድኑ ጥሪ አቅርቧል።

ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia