TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ETHIOPIA

በሀገራችን #ኢትዮጵያ ልዩ ልዩ ሥፍራዎች ማለትም፦
- በሰሜን ኢትዮጵያ (ትግራይ፣ አማራ፣ አፋር)
- በአሮሚያ
- በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልሎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ በነበረው ጦርነት እና ግጭት ምክንያት ከ22 ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉዳት እና ውድመት መድረሱ ተገለጿል።

ይህ የተገለፀው ከቀናት በፊት የአምስት /5/ ዓመት የመልሶ ማቋቋም እና ግንባታ መርሐ ግብር ይፋ ሲደረግ ነው።

የጉዳት እና የመልሶ ማቋቋም ፍላጎት ዳሰሳ ከዓለም ባንክ እና ከሌሎችም ዓለም አቀፍ ተቋማት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ፣ በኢትዮጰያ መንግሥት የተደረገ ነው።

ይፋ በማድረጊያው ስነስርዓት ላይ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶች ተወካዮች የተገኙ ሲሆን የፌዴራል ባለስልጣናት፣ የክልሎች ርእሳነ መስተዳድሮች ተገኝተው የነበረ ሲሆን በመልሶ ማቋቋም እና ግንባታ መርሐ ግብሩ ላይ አስተየያየት ሰጥተዋል፡፡

ማን ምን አለ ?

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ፦

" የመልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ዕቅዱን ለማስፈጸም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል። "

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፦

" በትግራይ የደረሰው ጉዳትና ውድመት ግዙፍ ነው። ጦርነቱ ብዙ ሕይወትን ቀጥፏል፤ በመሠረተ ልማት ላይም መጠነ ሰፊ ውድመትን አስከትሏል፡፡ በትግራይ ግን ጉዳቱ ከዚያም በላይ ነው፡፡

በጦርነቱ የክልላዊ መንግሥቱ መዋቅር እንዳለ ነው የፈረሰው፡፡ በአብዛኛው የመንግሥት ተቋማት እንደ አዲስ ነው እየጀመሩ ያሉት፡፡

ያሉን የተፈናቃዮች ብዛት አስደንጋጭ ነው፡፡

ልጆቻችን ትምህርት ካቆሙ 4 ዓመታት ሆኗቸዋል፡፡ አርሶ አደሮቻችን የተለመደውን የእርሻ ሥራ ለመከወን የማይችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።

ለእኛ በዚህ ሰዓት ስለ መልሶ ግንባታ መናገር ቅንጦት ይሆንብናል፤ ምክንያቱም ከዚያ በፊት፣ በርካታ የማገገሚያ ሥራዎችን ማከናወን አለብን፡፡

ተፈናቃዮችን ወደ ቀዬአቸው መመለስ አለብን፡፡ አርሶ አደሮቻችን ማረስ እንዲጀምሩ ማስቻል አለብን፡፡ ተማሪዎቻችንን ወደ ትምህርት ቤት መመለስ አለብን፡፡ ቢያንስ እውነተኛውን ትምህርት እንዲያገኙ ሳይኾን፣ እንደው ለስሙ አእምሯቸው ከጦርነቱ ድባብ እንዲርቅ ያህል።

በትግራይ የደረሰው ጉዳትና ውድመት የተለየ ነው፤ በርካታ የቀድሞ ተዋጊዎች አሉን፡፡ እነርሱን በአግባቡ ማቋቋም ካልተቻለ፣ የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ማድረግ ያስቸግራል።

ያሉን የተረጂዎች ቁጥር ከስድስት ወራት በፊት ከነበረው ስድስት ሚሊዮን ያለምንም ሳይንሳዊ ጥናት ወደ ሦስት ሚሊዮን እንደወረደ ቢገለጽም፣ እነዚኽም ቢኾኑ በአሁኑ ጊዜ፣ ምንም ዓይነት ርዳታ እያገኙ አይደሉም።

ችግሮቹን ለመፍታት፣ በሚቀጥሉት ሦስት እና አራት ወራት፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት የቻሉትን ያህል ያግዙን፤ ከዚያ በኋላ ስለ መልሶ ግንባታ እንናገራለን። "

የአማራ ክልል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ፦

" በጦርነቱ በክልሉ የደረሰው ጉዳት እና ውድመት፣ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ተጠንቶ፤ ውጤቱም ታትሞ ተሰራጭቷል።

ክልሉ ከደረሰበት ጉዳትና ውድመት እንዲያገግምም፣ በመልሶ ማቋቋሙ እና ግንባታ ሒደቱ ተባብረን ልንሠራ ይገባል።

ስላጋጠመው ጉዳት በዝርዝር መናገር አልፈልግም ፤ ጦርነቱ ግን በሰላም ስምምነት ተቋጭቷል፡፡

የአማራ ክልልና በጥቅሉ ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነቱን ውጤት እያጣጣሙ ናቸው፡፡

አሁን ተፈናቃዮችን ወደ ቀዬአቸው የመመለስ ጥረት እያደረግን ነው። የቀውሱ ዳፋ ግን ቀጥሏል፡፡ መሠረተ ልማት ፈርሷል፤ የጤና እና የትምህርት ተቋማት ወድመዋል፡፡

ጦርነቱ የተካሔደባቸውን አካባቢዎች፣ ወደ ሰላማዊ ኑሮ ለመመለስ፣ የጋራ ትብብር እና ቅንጅታዊ አሠራር ይፈልጋል፡፡በርከት ያለ ገንዘብ ማውጣትን ይፈልጋል፡፡

ይህን ስናደርግ እነርሱም የሰላም ስምምነቱን ውጤት ማጣጣም ይጀምራሉ፡፡ የዘላቂ ሰላም ግንባታ ሒደት አካልም ይኾናሉ። "

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ ፦

" በደቡባዊ እና ምዕራባዊ የክልሉ አካባቢዎች ያለው ግጭት ከ5 ዓመታት በላይ አስቆጥሯል።

ግጭቱ በትምህርት፣ በጤናና በሌሎችም ማኅበራዊ መሠረተ ልማቶች ላይ ትልቅ ውድመት አድርሷል።

የመልሶ ማቋቋም እና የግንባታ ሥራን ለማከናወን በቅድሚያ በኦሮሚያ ክልል ከሚንቀሳቀሰው ሸማቂ ኃይል ጋራ የጀመርነውን የሰላም ጥረት በመቀጠል ከዳር ማድረስ አለብን።

በዚህ መልኩ ዘላቂ ሰላም ካልተረጋገጠ፣ የመልሶ ግንባታ ጥረቱ አይሳካም። "

Credit : VOA AMHARIC

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

(የገቢዎች ሚኒስቴር)

ክሊራንስ ለመስጠት ኦዲት #የማያስፈልጋቸው አገልግሎቶች ፦

ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት አገልግሎቶች ታክስ ከፋዩን ኦዲት ማድረግ ሳያስፈልግ የታክስ ክሊራንስ የምስክር ወረቀት ሊሰጥ ይችላል:-

- ንግድ ሥራ ፍቃድ ወይም የሙያ ፍቃድ ለማደስ፤
- ጨረታ ለመካፈል ወይም ለመሳተፍ፤
- ለተሽከርካሪዎች ወይም ለኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች ዓመታዊ ምዝገባና ምርመራ (ክላውዶ) ለማድረግ፤
- የባንክ ብድር ለማግኘት፤
- የመድን ካሳ ለማግኘትና የተሽከርካሪ ሰሌዳ ለውጥ ለማድረግ፤
- የድርጅት ስም ወይም አድራሻ ለመለወጥ፤
- የንግድ ሥራ ሀብት መቀነስን ሳይጨምር የንግድ ዘርፍ ቅነሳ ለማድረግ፤
- ድርጅቶች እንደገና ተደራጅተው ሲዋሀዱ የተዋሀደውን ድርጅት የታክስ ዕዳ አካቶ የሚዋሃዱ ስለመሆኑ የፀደቀ ሰነድ ለማቅረብ፤

1. የክሊራንስ ጥያቄ በቀረበበት ጊዜ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ የተሰጠው እና ያልተከፈለ የታክስ ዕዳ ያለበት ታክስ ከፋይ ኦዲት ሳይደረግ የባንክ ብድር እንዲወስድ ክሊራንስ የሚሰጠው ዕዳውን የከፈለ እንደሆነ ወይም ለመክፈል የባንክ ዋስትና ያቀረበ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡

2. ታክስ ከፋዩ የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ሊሰጠው የሚችለው:-
• ታክስ ከፋዩ ዓመታዊ የንግድ ትርፍ ግብር ማስታወቂያ እና መክፈያ የመጨረሻ ቀን ከመድረሱ በፊት የንግድ ሥራ ፍቃድ ለማደስ፣ በጨረታ ለመሳተፍ፣ የባንክ ብድር ለመውሰድ እና የጉዳት ካሳ ለማግኘት የሚቀርብ የታክስ ክራንስ ምስክር ወረቀት ጥያቄ ከሆነ ጥያቄው ከቀረበበት የግብር ዘመን በፊት ታክሱን አስታውቆ ግዴታውን የተወጣ ስለመሆኑ እና
• የታክስ ክራንስ ምስክር ወረቀት የተጠየቀበትን አገልግሎት ዓይነትና የተፈለገበትን ምክንያት የሚያስረዳ ማስረጃ ሲያቀርብ ብቻ ይሆናል፡፡

3.  የባንክ ብድር ለማግኘት የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት እንዲሰጠው ለጠየቀ ሰው የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት የሚሰጠው ጥያቄ አቅራቢው የንግድ ሥራ ያልሠራና በግብር ከፋይነት ያልተመዘገበ ከሆነ ከታክስ መስሪያ ቤቱ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ከመረጃ ቋት ተገቢውን ማጣራት አድርጎ ጠያቂው በንግድ ሥራ አለመሠማራቱን በማረጋገጥ ይሆናል፡፡

4.  የንግድ ሥራ ፍቃድ ለመመለስ ጥያቄ ሲያቀርቡ ከታክስ ሚኒስቴሩ የሥራ ክፍሎች እና ከሶስተኛ ወገን በማጣራት የታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት የሚሰጥ ይሆናል፡፡

Credit : የገቢዎች ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

" የፈተና ህትመት ደህንነቱን በጠበቀ መልኩ #ከፌደራል_ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር እየተሰራ ነው " - የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ ለሚሰጠው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና በቂ ዝግጅቶች መደረጋቸውን የከተማው ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

የፈተና ህትመት ደህንነቱን በጠበቀ መልኩ ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር እየተሰራ እንዳለ ተጠቁሟል።

በዘንድሮው ከተማ አቀፍ ፈተና በ8ኛ ክፍል 75‌100 ተማሪዎች በ766 ት/ቤቶች እንዲሁም በ6ኛ ክፍል 75‌090 ተማሪዎች በ788 ትምህርት ቤቶች በመደበኛ በማታና በግል ለመፈተን ምዝገባ ማካሔዳቸውን ተነግሯል።

ከተማ አቀፍ ፈተናውን በብቃት ለመስጠት ትምህርት ቢሮው በቂ ዝግጅት ማድረጉን ያሳወቀ ሲሆን የፈተና ጣቢያ ሃላፊዎች ሱፐርቫይዘሮችና ፈታኞችም ፈተናውን በስኬት ለማጠናቀቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

በቀጣይ በከተማዋ 53,535 የሚሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ለሀገር አቀፍ ፈተና እንደሚቀርቡ ከከተማው የትምህርት ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@tikvahethiopia
#Update

የትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል በጦርነቱ ምክንያት ሥራ አቁመው የነበሩ ዩኒቨርሲቲዎች ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ከአንድ ወር በኃላ ነባር ተማሪዎቻቸውን እንደሚቀበሉ ከመስከረም (2016) ጀምሮ ደግሞ #ሙሉ_ለሙሉ ሥራ እንደሚጀምሩ አስታውቋል።

የሚኒስቴሩ የአስተዳደርና ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሀ (ዶ/ር) ለኢፕድ የሰጡት ቃል ፦

" ከአክሱም ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ሦስቱ ዩኒቨርሲቲዎች በመጭው ወር ነባር ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራሉ።

በመጪው ዓመት በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችን ወደ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው።

ዩኒቨርሲቲዎቹን ወደ ሥራ ለማስገባት የትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርሲቲዎቹ ያሉበት ሁኔታ ከዩኒቨርሲቲዎቹ አመራሮች ጋር በመቐለ ተደጋጋሚ ውይይት አድርጓል።

ሥራ ለማስጀመር የሚያስችሉ ሥራዎችን ለመስራት ወደ ተግባር ተገብቷል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ የመማር ማስተማር ሂደት ከመጀመራቸው በፊት ፦
- የምግብ ፣
- የመኝታ፣
- የሕክምና አገልግሎቶች ቅድሚያ የሚያሟሉበት ሁኔታ እየተመቻቸ ነው።

ራያ ዩኒቨርሲቲም ይህንን አሟልቶ በትናንትናው ዕለት የተማሪዎች ምዝገባ ጀምሯል።

መቐለና ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ በቀጣይ ወር ትምህርት መጀመር የሚያስችላቸውን ተግባር ጨርሰው ተማሪዎችን መቀበል እንደሚጀምሩ ይጠበቃል።

አክሱም ዩኒቨርሲቲ ከሌሎቹ ዩኒቨርሲቲዎች በበለጠ በጦርነቱ ጉዳት በማስተናገዱ የተወሰነ ጊዜ ሊዘገይ ይችላል።

አራቱ ዩኒቨርሲቲዎች ከጦርነቱ በፊት 45 ሺሕ ተማሪዎችን ሲያስተምሩ ነበር። ከእነዚህ ውስጥም ባለፉት ዓመታት 22 ሺሕ የሚሆኑ ተማሪዎች እንዲወጡ ተደርጎ በጊዜያዊነት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ተደርጓል።

እነዚህ ዩኒቨርሲቲዎችም አሁን ላይ ቅበላ የሚያደርጉት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሳይመደቡ የቆዩ 20 ሺሕ የሚሆኑ ተማሪዎችን ነው።

በመጪው አገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው የሚያልፉ ተማሪዎችም የዩኒቨርሲቲዎቹ ዝግጁነት ተጠንቶና ታይቶ ተማሪዎች ሊመደቡባቸው ይችላል።

ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩና ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሄደው ያጠናቀቁ ተማሪዎች ውጤታቸውን የሚገልጽ የትምህርት ማስረጃ ሳያገኙ መቆየታቸውን ይታወሳል ፤ አሁን ላይ ከነበሩበት ዩኒቨርሲቲ ያገኙት ውጤት ወደ ትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲላክ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ዩኒቨርሲቲዎቹም ውጤቱ ሲደርሳቸው የነበራቸውን ውጤት ደምረው ጥቅል ውጤታቸውን የሚገልጽ ጊዜያዊ ዲግሪ ማግኘት ይችላሉ። "

Via EPA

@tikvahethiopia
Forwarded from JD
#ብርሃን_ባንክ
ዛሬ በጥቂት የተከማቸ ገንዘብ አድጎ ለቁም ነገር እንዲውል ጠቀም ያለ ወለድ የሚያስገኘው የህጻናት የቁጠባ ሂሳብ አገልግሎታችን ተጠቃሚ ይሁኑ!
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://publielectoral.lat/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ራያ ዩኒቨርሲቲ ነባር ተማሪዎችን ተቀብሎ ምዝገባ ማካሄድ ጀምሯል፣ መቐለ እና ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራሉ ፤ ኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎቹን ይቀበላል " - ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ (ለቲክቫህ ኢትዮጵያ)

ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች (መቐለ፣ ዓዲግራት፣ ራያ፣ ኣክሱም) ወደ መማር ማስተማር ስራቸው እንደሚመለሱ አሳወቀ።

የትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ሰለሞን አብርሃ ፤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት በክልሉ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ መማር ማስተማር ስራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም ራያ ዩኒቨርሲቲ ከትላንት ጀምሮ ነባር ተማሪዎችን በመቀበል ምዝገባ መጀመሩን አሳውቀውናል።

መቐለ እና ዓዲግራት ዩኒቨርሲቱ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ነባር ተማሪዎቻቸውን መቀበል እንደሚጀምሩ የገለፁልን ዶ/ር ሰለሞን፤ የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በሁለት ወር ጊዜ ውስጥ ተማሪዎቹን መቀበል እንደሚጀምር አሳውቀውናል።

የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በበለጠ በጦርነት መጎዳቱ የመዘግየቱ ምክንያት መሆኑን አስረድተውናል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ ቅበላ የሚያደርጉት ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ ሳይመደቡ የቆዩ ተማሪዎችን መሆኑን ዶ/ር ሰለሞን ገልጸውልናል።

በመጪው አገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስደው የሚያልፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲዎቹ ዝግጁነት ተጠንቶና ታይቶ ተማሪዎች ሊመደቡባቸው ይችላል ብለዋል።

በትግራይ ክልል ያሉ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ከመስከረም 2016 ዓ/ም ጀምሮ #ሙሉ_በሙሉ ወደ ስራ እንደሚገቡ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ በላኩልን መልዕክት አስረድተዋል።

@tikvahethiopia
ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ
=================
ደንበኞች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገራት ለሚያደርጉት ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ አስቀድመው መቆጠብ እንዲችሉ የተዘጋጀ የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡

ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ ከብር 1,000 ጀምሮ ይከፈታል፡፡

የቁጠባ ሂሳቡ የተለያዩ ጥቅሞች ያስገኛል፡፡

• ቆጣቢዎች በሀገር ወስጥ ጉዟቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ተጠቅመው ለአየር ትኬት፣ ለቱሪስት መዳረሻዎች መግቢያ፣ ለሆቴል አገልግሎት እና ለመሳሰሉት ክፍያ በሚፈፅሙበት ወቅት ተመላሽ ያገኛሉ፤

• ዳያስፖራ ወይም የውጭ ሀገር ዜጎች የሲቢኢ ቱሪስት ካርድን ሲጠቀሙ እስከ 7 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ ፤

• ለሀይማኖታዊ ጉዳይ ወደ ውጭ ሀገራት የሚጓዙ ደንበኞች ከአየር ትኬት ክፍያቸው እስከ 3 በመቶ የሚደርስ ተመላሽ ያገኛሉ፤

• ሌሎች ተጨማሪ ጥቅሞችንም ያስገኛል፡፡

ሂሳቡን በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ፤ ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ይደውሉ!
ይቆጥቡ፤ ይጓዙ!
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#forfreemarket

አስፈላጊ ምርቶች  ፤ ተመጣጣኝ_ዋጋ

ለተጨማሪ ማብራሪያ የቴሌግራም ገፃችን⤵️
https://publielectoral.lat/forfreemarket

አነስተኛ የልብስ እና ጫማ ማጠቢያ
👉ለጫማ ቢሉ ለልብስ ቦታ የማይዝ
👉 ለፓንት ቦክሰር እና ካልሲ
👉ለ ቲሸርት ሁነኛ ተመራጭ
 👉ለዳይፐር

🏢 አድራሻ 👉 ፒያሳ ጣይቱ ሆቴል ጊቢ ውስጥ
📲 0911255787
📲 0983360606
ጥራት መለያችን ነው
OnLineShopping
    
#Oromia

የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ቶላ በሪሶ የ8ኛ ክፍል እና የ12ኛ ክፍል ፈተናዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ መስጠታቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ አሳውቋል።

የ2015 የ8ኛ ክፍል ፈተና እንደ ክልል የሚካሄድ ሲሆን የ12ኛ ክፍል ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ እንደሚሰጥ ዶ/ር ቶላ በሪሰ ገልጸዋል

የ8ኛ ከፍል ፈተናን በተመለከተ 490,167 ተማሪዎች እንደሚወስዱ (ከዚህም ውስጥ ወንድ 260,807 እና ሴት 229,360 ናቸው) ገልጸው የ8ኛ ክፈል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ሰኔ 26 እና 27/2015 መሆኑን አሳውቀዋል።

የ12ኛ ክፈል ብሄራዊ ፈተናን አስመልክቶ በክልሉ 323,149 ተማሪዎች ለፈተናው እንደሚቀመጡ ገልጸው የፈተና ፕሮግራሙን እንደሚከተለው አብራርተዋል።

የፈተናው ፕሮግራም

👉 ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች

- ሐምሌ 16 -17 / 2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።

- ሐምሌ 18 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።

- ከሐምሌ ከ19 - 21/2015 ፈተናው ለ 3ት ቀናት ይሰጣል ።

- ሐምሌ 22-23/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።

👉 ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፦

- ሐምሌ 22 -23/2015 ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ።

- ሐምሌ 24/2015 የፈተና ኦረንቴሽን ይሰጣል።

- ከሐምሌ 25 -28/2015 ፈተናው ለአራት ቀናት ይሰጣል።

- ሐምሌ 29-30/2015 ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ይመለሳሉ።

ለ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ፈተናዎች ስኬት ሁሉም ማህበረሰብ የበኩሉን እንዲወጣ የኦሮሚያ ክልል ት/ቢሮው ሀላፊ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪም ተማሪዎች በፈተና ጥሩ ውጤት ለማስመዝገብ በሁሉም አቅጣጫ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

ምንጭ ፦ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ

More : @tikvahethafaanoromoo

@tikvahethiopia
#Update

የ2015 ዓ.ም ብሔራዊ የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለመውሰድ ከ869 ሺህ በላይ ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል፡፡

ለ2ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠውን አገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ 869 ሺህ 765 ተፈታኞች በኦንላይን መመዝገባቸውን በአገልግሎቱ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወንደወሰን ኢየሱስወርቅ ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

ከተመዘገቡት ውስጥ 503,812 ተማሪዎች የሶሻል ሳይንስ እና 365,954 የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።

የፈተና አስፈጻሚዎች፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ምልመላ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30/2015 ዓ.ም በሁለት ዙር እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ #ኢፕድ

More : @tikvahuniversity

@tikvahethiopia
#ቮልስዋገን

" ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር እንዳይገባ ታግዷል " - የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር

ወደ ኢትዮጵያ ከሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጲያ እየገባ የሚገኘው " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን የጀርመን ኩባንያ በኢንባሲው በኩል ለትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

ይህ ቻይና ሀገር የሚመረተው የ " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን ሚኒስቴሩ ዛሬ አሳውቋል።

ምንጭ፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

የቪዛ ካርድዎን ከአቢሲኒያ ባንክ በ72 ሰዓታት ውስጥ ይረከቡ! ልክ እንደጊዜው አገልግሎታችንም ፍጥነትን ከጥራት ያሟላ ነው!

መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #VISA #ATMcard #poweredbybankofabyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all