#ቮልስዋገን

" ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር እንዳይገባ ታግዷል " - የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር

ወደ ኢትዮጵያ ከሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጲያ እየገባ የሚገኘው " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን የጀርመን ኩባንያ በኢንባሲው በኩል ለትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

ይህ ቻይና ሀገር የሚመረተው የ " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን ሚኒስቴሩ ዛሬ አሳውቋል።

ምንጭ፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia