TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በታላቁ አንዋር መስጂድ በሰላማዊ ምእመናን ላይ የደረሰውን ጉዳት ተከትሎ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ ከሚመለከተው የፌደራል ፓሊስ ኮሚሽን ጋር የተፈጠረውን ቀውስ ለማረጋጋት እና ባስቸኳይ የተጎዱትን ለማትረፍ በሚቻልበት መንገድ ላይ እየተነጋገሩ መቆየታቸው ተሰምቷል። በተፈፀመው ጥቃት ጉዳት የደረሰባቸው ምዕመናን የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ ወደ…
#Update

" በአንዋር መስጂድ የነበሩ በቁጥር እጅግ በርካታ ሰዎች በሰላም እንዲወጡ ተደርጓል " - የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሱልጣን አማን ኤባ እና የበላይ አመራሮች በአንዋር መስጂድ ከደረሱበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ የማረጋጋት ስራ በመስራት አንድ ሸሂድ (መስዋእት) የሆነ ሙስሊም እና ጉዳት የደረሰባቸውን ወደ ሆስፒታል እንዲሄዱ ማድረጋቸውን ም/ቤቱ አሳውቋል።

የጁመዓ ሰላት ለመስገድ በአንዋር መስጂድ የተገኙና በተፈጠረው ችግር ምክንያት በመስጂዱ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ታግተው የቆዩ ምእመናንም ወደየቤታቸው #በሰላም ሸኝተዋል።

አንድም ሰው እንዳልቀረ ካረጋገጡ በኃላ አመራሮቹ የመስጂዱን ቅጥር ጊቢ ለቀው መውጣታቸው ተገልጿል።

ከፍተኛ ም/ቤቱ ፤ " ለሞቱት ጀነት እንዲወፍቃቸው፣ ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ ለተጎዱትም ቶሎ ማገገምን ይቸር ዘንድ አላህን እንጠይቃለን " ብሏል።

በቀጣይ ህዝበ ሙስሊሙ እየተፈፀሙበት ያለውን አላግባብ የመብት ጥሰቶች በተገቢው መልኩ መፍትሄ ያገኝ ዘንድ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ጠቅላላ ጉበኤ ውሳኔ መሰረት የተቋቋመውን ዘጠኝ አባላት ያሉት ኮሚቴን እና የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የሚሰጠውን አቅጣጫ እንደ መሪ ተቋም በማክበር ተግባራዊ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

መረጃው የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amahara በአማራ ክልል ከሚገኙ ከተሞች አንፃራዊ የሚባል ሰላም እና መረጋጋት የነበራት ባህር ዳር ዛሬ በተለያዩ አካባቢዎች በተኩስ ስትናጥ መዋሏን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ከስፍራው ዘግቧል። ምንም እንኳን ስለደረሰው ጉዳት የሚታወቅ ነገር ባይኖርም ትላንት ማታ ቦምብ የፈነዳ ሲሆን ዛሬ ቅዳሜ ከጥዋት ጀምሮ በተለይ  " ቀበሌ 14 " በሚባለው አካባቢ ላይ መንገዶች ተዘግተው ፤ የንግድና ትራንስፖርት እንቅስቃሴ…
#Amhara

በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች ያለው ውጥረት አሁንም የቀጠለ ሲሆን በተለያዩ ቀጠናዎች ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ስለመኖራቸው ለማወቅ ተችሏል።

በክልሉ ባለው ግጭት እና ፍጥጫ የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት ተስተጓጉሏል ፣ የኢንትርኔት አገለግሎት ተቋርጧል፣ አንዳንድ አካባቢዎች በታጣቂዎች ቁጥጥር ስር ናቸው።

" የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ " ዋና ሰብሳቢ እና የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አግልግሎት ዳይሬክትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ትላንት እሁድ በሰጡት ማብራሪያ፤ በአማራ ክልል የተጣለውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚያስፈጽመው ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ ሕግ የማስከበር ሥራውን በማከናወን ክልሉን ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው በአጭር ጊዜ እንዲመለስ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።

አቶ ተመስገን ፤ አማራ ክልል የተከሰተው በትጥቅ የታገዘው እንቅስቃሴ " የክልሉን መንግሥት በማፍረስ ወደ ፌደራል መንግሥቱ የሚዞር ግብ ያለው " ነው ብለዋል።

በክልሉ የተለያዩ ክፍሎች ሕገወጥነት ተከስቷል ያሉት ሰብሳቢው ፤ " የተደራጁ ዘራፊ ቡድኖች " ሲሉ የጠሯቸው አካላት በክልሉ ውስጥ የዞን እና የወረዳ ከተሞችን #ተቆጣጥረው የፍትሕ እና የሕዝብ ተቋማት አገልግሎት እንዳይሰጡ ከማስተጓጎል ባሻገር " በአንዳንድ አካባቢዎች ማረሚያ ቤቶችን ሰብረው ወንጀለኞችን እንዲያመልጡ እስከማድረግ የደረሰ ውንብድና ፈጽመዋል " ብለዋል።

በክልሉ ሕግ እና ሥርዓትን ለማስከበር እንዲሁም የመንግሥት እና የፓርቲ መዋቅርን የማጠናከር ሥራዎችን ለማከናወን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዙ ክልሉን በአራት ኮማንድ ፖስቶች ማዋቀሩን አስታውቀዋል።

• የመጀመሪያው የምዕራብ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ምሥራቅ እና ምዕራብ ጎጃም
- ደብረ ማርቆስ ከተማ፣
- የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን
- ባሕር ዳር ከተማ ያሉበት ነው።

• ሁለተኛው የሰሜን ምዕራብ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ሰሜን፣ ምዕራብ፣ ማዕከላዊ እና ደቡብ ጎንደር
- ጎንደር ከተማ
- ደብረታቦር ከተማ የሚገኙበት ነው።

• ሦስተኛው ኮማንድ ፖስት ማዕከላዊ ሸዋ ፦
-  ሰሜን ሸዋ፣
- የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን
- ደብረ ብርሃን ከተማን ያካተተ ነው።

• አራተኛ የምሥራቅ አማራ ኮማንድ ፖስት ፦
- ኮምቦልቻ እና ወልዲያ ከተሞች - ሰሜን እና ደቡብ ወሎ
- ዋግ ኽምራን ያካተተ መሆኑን የዕዙ ሰብሳቢ ገልጸዋል።

አቶ ተመስገን ፤ በክልሉ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር እና የሚነሳ የትኛውንም ጥያቄ መንግሥት #በሰላም_ምላሽ_ማግኘት_አለበት ብሎ በጽኑ እንደሚያምን የገለፁ ሲሆን ሕግ እና ሥርዓት የማስከበሩ ሥራም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በአማራ ክልል ፤ ባለፉት ጥቂት ወራት ተቃውሞና ግጭቶች የነበሩ ሲሆን ከሰሞኑን ግን ግጭቶቹ ተስፋፍተው ወደ ትልልቅ ከተሞች ደርሰዋል።

ከመንግሥት ፀጥታ ኃይል ጋር ግጭት ውስጥ የገቡት የፋኖ ታጣቂዎች ፤ በተለይ " ከአማራ ልዩ ኃይል መፍረስ ጋር በተያያዘ የ #አማራ_ህዝብ እና #ክልልን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥል ውሳኔ ነው የተወስነው ፤ ሌሎችም የህልውና ጥያቄዎች አሉብን " በማለት ወደ ግጭት መግባታቸው ይነገራል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ይጎብኙ 🖼  . . .  #ይምረጡ

በ13 ቡድን የተከፈሉና 80 ወጣቶች #በሰላም ዙሪያ ያላቸውን ሀሳብ ክህሎታቸውን ተጠቅመው የገለጹበት የስዕል ኤግዚቢሽን ለተመልካቾች ክፍት ተደርጓል።

ጎብኚዎች የስዕል ሥራዎቹን፣ የተወዳዳሪዎቹን ሀሳብ እንዲሁም የወደዱትን ሥራ ላይ ድምጽ የሚሰጡበት የዲጂታል ኤግዚቢሽን ሲሆን በተመልካች እና በዳኞች በሚሰጥ ድምጽ አሸናፊዎች የሚለዩ ይሆናሉ።

ሪድም ዘ ጀኔሬሽን ባዘጋጀው በዚህ የስዕል ውድድር ፦
- አንደኛ ለሚወጣው ቡድን የ60,000 ብር፤
- ሁለተኛ ለሚወጣው ቡድን የ40,000 ብር፤
- ሦስተኛ የሚወጣው ቡድን ደግሞ የ25,000 ብር 
- በማኅበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ላገኘው የሥዕል ሥራ የ10,000 ብር ሽልማት ያገኛሉ።

የሥዕል ስራውን ይጎብኙ፤ ለወደዱት ሥዕል ድምጽ ይስጡ 👉 https://redeem.tikvahethiopia.net/
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በዓሉ #በሰላም ተጠናቋል " - ግብረ ኃይሉ

የ2016 የሆራ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርአቱን በጠበቀ መልኩ #በሰላም መከበሩን የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታውቋል።

ግብረ ኃይሉ ፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተሳታፊዎች ተገኝተውበታል ያለድ የዘንድሮው የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በሰላም ተከብሮ #መጠናቀቁን ገልጿል።

የነገው የሆራ አርሰዴ ኢሬቻ በዓለም በተመሳሳይ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ህብረተሰብ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ እና ለፀጥታ ኃይሉ እገዛውን እንዲያጠናክር ተጠይቋል።

@tikvahethiopia
ቪድዮ፦ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን በረራ ላይ ሳለ #መስኮቱ_መገንጠሉን ተከትሎ አንድ የአሜሪካ አየር መንገድ አውሮፕላኑን ከበረራ አግዶታል።

የአሜሪካው አላስካ አየር መንገድ በቁጥር 65 የሆኑ 737 ማክስ 9 አውሮፕላኖቹን አግዷል።

እገዳው በበረራ ወቅት የአንደኛው አውሮፕላን መስኮት ተገንጥሎ አውሮፕላኑ በአስቸኳይ ለማረፍ ከተገደደ በኋላ ነው።

አርብ ዕለት በኦሬጎን ግዛት ከፖርትላንድ ከተማ ተነስቶ ወደ ካሊፎርኒያ ሲበር የነበረው አውሮፕላን የገጠመውን አደጋ ተከትሎ ከ35 ደቂቃዎች በረራ በኋላ በመነሻው ለማረፍ ተገዷል።

አየር መንገዱ በአውሮፕላኑ ተሳፍረው የነበሩት 177 ተሳፋሪዎች እና ሠራተኞች ምንም ጉዳት ሳይደርስባቸው አውሮፕላኑ #በሰላም አርፏል ብሏል።

የአደጋው መንስዔ እስኪጣራ ድረስ ሁሉንም 737 ማክስ 9 አውሮፕላኖች በጊዜያዊነት ከበረራ እንዳገደ አየር መንገዱ አስታውቋል።

ይህ ቦይንግ ሰራሹ አውሮፕላን ባለፉት ዓመታት መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል።

ከአምስት ዓመት በፊት #በኢትዮጵያ እና #ኢንዶኔዢያ ባጋጠመ አደጋ ምክንያት ከበረራ ታግዶ የነበረው ይህ ማክስ 737 ዝርያ መሆኑ ይታወቃል። #BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት የሆኑት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ፥ " በወረራ " ተይዘዋል ያሏቸውን የትግራይ ክልል ግዛቶችን በሰላም ስምምነቱ መሰረት ነጻ እንዲወጡ እና የአካባቢዎቹ ሰላምና ደህንነት ተረጋግጦ ተፈናቃዮች ወደ ቀድሞ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ኃላፊነት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት…
" ስጋት ፈጥሮብናል " - ኤምባሲዎቹ

ሰሞነኛውን የሰሜን ኢትዮጵያን ጉዳይ አስመልክቶ በአዲስ አበባ የሚገኙት ፦
- የካናዳ፣
- የፈረንሳይ፣
- የጀርመን፣
- የጣሊያን፣
- የጃፓን፣
- የእንግሊዝ እና የአሜሪካ ኤምባሲዎች የጋራ አጭር መግለጫ አውጥተዋል።

በዚህም ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ " #አወዛጋቢ " በሆኑት አካባቢዎች ከሰሞኑን የተፈጠረው ግጭት " ስጋት ፈጥሮብናል " ብለዋል።

ሁሉም ወገኖች የታጣቂ ኃይሎች ትጥቅ ማስፈታት ፣ ብተና እና መልሶ ማቋቋም /#DDR / እንዲሁም ተፈናቃዮችን #በሰላም ወደ ነበሩበት መመለስ ላይ አበክረው መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

" ውጥረቱ እንዲረግብ እና #ሰላማዊ_ሰዎች ጥበቃ እንዲደረግላቸው እናሳስባለን " ብለዋል።

በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ እና የተወሳሰቡ የፖለቲካና የጸጥታ ቀውሶችን ለመፍታት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ውይይት ማድረግ ብቸኛው መንገድ ነው ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #EOTC " የቤተ ክርስቲያን መከራ ከውጭ ብቻ አይደለም ከውስጥም እንጂ፤ ከባዕድ ብቻም አይደለም ከወዳጅም እንጂ ፤ የወዳጅ ፈታኝ እንደሚብስም ታውቆ ያደረ ነገር ነው " - ቅዱስነታቸው ግንቦት ወር ላይ የሚካሄደው ዓመታዊው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ተጀመረ።   የጉባኤውን መጀመር አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ…
#EOTC #ETHIOPIA

ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፦

" የማኅበረሰባችን ችግር በቤተ ክርስቲያን ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ በሀገር ደረጃ እየቀጠለ ያለው አለመግባባትም ለጠቅላላ ማኅበረ ሰባችን ፈተና ከሆነ ውሎ አድሮአል፤ የቤተ ክርስቲያናችን ፈተና ምንጭ ከሆኑትም አንዱና ዕድል ሰጩ ይህ ሀገራዊ አለመግባባት ነው።

በዚህ አለመግባባት ምክንያት ገዳማውያን መነኮሳት፤ መምህራን ካህናት ምእመናን አብያተ ክርስቲያናት ከባድ የሆነ ጉዳት ደርሶባቸዋል ፤ #በሰላም_ወጥቶ_መግባትም_አጠራጣሪ_ሆኖአል ፤ ይህንን ችግር ለመፍታት የሚደረግ ጥረትም ጎልቶ አይታይም፡፡

በመሆኑም ይህ ክሥተት እውን ኢትዮጵያውያን የራሳችንን ችግር በራሳችን መፍታት የማንችል ሰዎች ነን ወይ ? ለኛስ ከኛ የበለጠ ማን ይመጣልናል ? የሚለውን ጥያቄ ልናነሣ ግድ ነው። ስለዚህ ለሀገር ህልውናና ድኅነት የሚበጅ ነገር እንዲመጣ ቤተ ክርስቲያን ባላት ሃይማኖታዊና ሰብአዊ ኃላፊነት ጠንክራ መስራት ይጠበቅባታል። "

#ኦርቶዶክስተዋሕዶ #ኢትዮጵያ
#የግንቦት_ርክበ_ካህናት_ቅዱስ_ሲኖዶስ_ምልአተ_ጉባኤ

@tikvahethiopia
#OROMIA #PEACE

" የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ... ለሰላም ክፍት ነን ድርድሮችም እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " - የኦሮሚያ ክልል መንግሥት

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አሁንም ቢሆን ያሉ ችግሮች #በሰላም እንዲፈቱ መንግሥት #ለድርድር ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል።

የክልሉ መንግሥት አመራሮች ከኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር በአዲስ አበባ እንደመከሩ ተነግሯል።

በምክክሩ ላይ የተገኙት የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኦሮሚያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ታፈሰ ውይይቱ ልማትና ጸጥታ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ሲሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

በውይይቱ ፦

- የልማት ስራ ያለ ሰላም ውጤት አልባ እንደሆነ / ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት እንደሆነ ፤

- ሰው ሰርቶ የሚበላው ፣ ወልዶ የሚስመው ሰላም ሲኖር እንደሆነ አጽንኦተ ተሰጥቶበታል ብለዋል።

" ሰላም ለመንግሥት ብቻ የተተወ ስላልሆነ እንዴት ነው አብሮ መስራት የሚቻለው ? " የሚለውም መነሳቱን አስረድተዋል።

" መንግሥት እና ሸኔ የጀመሩት ድርድር ፤ በተለያየ ምክንያት አኩርፈው ጫካ የገቡ ነፍጥ ያነገቡ ጓዶች አሉ ፤ መንግሥት በሆደ ሰፊነት ዛሬ ነገ ሳይል እነዚህን አካላት ጠርቶ በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር አለበት ይህ ሲደረግ ደግሞ ለሰዎቹ እውቅና ተሰጥቶ የህግ ከለላ ተሰጥቶ ነው ውይይት መደረግ ያለበት " የሚለውም መነሳቱን ገልጸዋል።

" በመንግሥት በኩል ' ዛሬም ቢሆን ክፍት ነው እንነጋገራለን ፣ ችግሮችን በጋራ ተነጋግረን እንፈታለን ' የሚል ምላሽ ነው የተሰጠን " ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አሁንም ቢሆን የክልሉ መንግሥት በውይይት ያምናል ብለዋል።

" የመንግሥት ወታደሮች ፣ ሌላም ፣ ንጹሃንም ዋጋ መክፈል የለባቸውም፤ ሙሉ ትኩረታችን ወደ ሰላም ማምጣት ነው ያለብን። የፈለግነውን ነገር በአዳራሽ መወያይት ይቻላል። ጥረቶች ብዙ ነው ያደረግነው አሁንም ለሰላም ክፍት ነን እኛ 3ኛ ዙር ይሁን፣ 5ኛ ዙር ይሁን ፣ 10ኛ ዙር ድርድሮች እንዲቀጥሉ እንፈልጋለን " ብለዋል።

#Ethiopia
#Oromia #VOA

@tikvahethiopia