TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
🔈#የነዋሪዎችድምጽ

ሰሞኑን " ዶላር በጣም ጨምሯል " በሚል የዋጋ ጭማሪ እያደረጉ የሚገኙ የንግዱ አካላት እጅግ እያማረሯቸዉ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቤት ብለዋል።

" አሁን ላይ ነጋዴው እቃውን በሌሎች ነጋዴዎች ሱቅና በራሱ መጋዘን ሲያስቀምጥ አይናችን እያዬ እቃዉ የለም በሚል ዋጋ ሊጨምር ሲሞክር ማየት ያማል " ሲሉ ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ ፥ " እስከ 1,080 ብር የነበረዉ ዘይት 1380 ብር ሲገባ ዶላር ነው " አሉን " እሺ የቲማቲምና ሽንኩርቱስ ዋጋ መናር ከየት መጣ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

1 ኪሎ ሽንኩርት ከ40 ብር ተነስቶ 90 ብር ቲማቲም 20 ብር የነበረው 40 እና 45 መግባቱን ጤፍም በኪሎ ከ10 ብር በላይ እንደጨመረ ጠቁመዋል።

ስሚንቶ ላለፉት ወራት ጥሩ ቢሆንም አሁን ላይ " የለም " እየተባለ እንደሆነ ገልጸዋል።

የነዳጅ ጉዳይ ግን በፊትም አንስቶ ፈተና ነበር አሁን ብሶበት ራስ ምታት ሆኖ ቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

ሀዋሳ ላይ የገበያውን ሁኔታ ስርአት ለማስያዝ የተቋቋመ ግብረሀይል መኖሩን በመስማታችን  የነዋሪዎችን ቅሬታ ይዘን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዡ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለን አነጋግረናል።

እሳቸውም ፥  " አሁን ላይ እቃ በሚደብቁ እና አላግባብ ዋጋ በሚጨምሩ ህገወጥ ነጋዴዎች ላይ ግብረሀይሉ  ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው " ብለዋል

ግብረሀይሉ  በሰራዉ ስራ ሁለት ማደያዎች እና 62 የሸቀጣሸቀጥ ሱቆች የምግብ ግብአትና የብረታብረት አቅራቢዎች በ8ቱ ክፍለ ከተሞች  መታሸጋቸዉንና እቃዎችም ተወርሰዉ ህገወጦቹ ግለሰቦች  በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ገልጸዋል።

ክትትሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሚገልጹት አዛዡ ማህበረሰቡም ህገወጦችን በመጠቆም የፖሊስን ስራ እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🔈#የመምህራንድምጽ

° " ግንባታው እንዲቆም ተደርጎብናል " - መምህራን

° " ጉዳዩን የጸረሙስና አካላት ወደ ፍርድ ቤት ወስደውታል፤ ምርመራ ተጀምሯል " - የሀዋሳ ፖሊስ

ከሰሞኑን " በማህበር ተደራጅተን የምንገነባውን የመኖሪያ ቤት ግንባታ በማስቆም እንዲገነባልን ውል የገባውን ተቋራጭ አሰሩብን " ያሉ የሀዋሳ ከተማ መምህራን ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

መምህራኑ " አመራሩ ሊደግፈን ሲገባ እየገፋን ነው " ብለዋል።

" በሀገሪቱ ጠ/ ሚኒስትር ሳይቀር ለመምህራን ድጋፍ ተደርጎ የቤት ባለቤት የምንሆንበት መንገድ ይመቻች በተባለበት በዚህ ወቅት መምህራን የሚገነቡትን ቤት አስቁሞ ተቋራጭን ማሰር መንግስትና መምህራንን ለማጋጨት የታሰበ ሴራ እንጅ ሌላ ምንም አይደለም " ብለዋል።

" ድርጊቱ አሳፋሪ ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

መምህራኑ፤ ከሳምንት በፊት አመራሩ በመምጣት " በርቱ " እንዳላቸውና ከፌደራል ሳይቀር እንግዳ ጋብዞ ፣ እገዛ ልናደርግ ዝግጁ ነን " እንዳላቸው ተናግረዋል።

በድንገት ግን ተገልብጦ ስራው ህጋዊ አይደለም ማለቱን ጠቁመዋል።

" ችግሮች ቢኖሩ እንኳን በውይይት ማስተካከል ይቻላል " የሚሉት መምህራኑ ለ9 አመታት የቆመ ቤት ድንገት መሰራት ሲጀምር ለማስቆም መሯሯጥ ከጀርባው ሌላ ዓላማ ያነገበ እንዳይሆን ስጋታቸውን ገልጸዋል።

መምህራኑ ህጋዊ በሆነ መንገድ የሚያሰሩትን የህንጻ ዲዛይን ከG+3 ወደ G+4 መቀየራቸውን የከተማው ማዘጋጃ ቤት የማህበራት ማደራጃ እና የከንቲባ ጽህፈት ቤት የሚያውቀው እንደሆነ ጠቁመዋል።

ይህ ሆኖ እያለ ግንባታው #እንዲቆም መታዘዙን ገልጸው ፤ " ወቅቱ መምህራን የሚደገፉበት እንጅ ጥሪታቸውን ያፈሰሱበትን የሚቀሙበት አይደለምና እንቅፋት የሆኑብን አካላት ሊተዉን ይገባል " ብለዋል።

" በህግ አምላክ እጃችሁን ከድሀው መምህራን ላይ አንሱልን ፤ ይህ ባይሆን ግን አደባባይ በመውጣት ጩኸታችንን ለማሰማት ዝግጁ ነን " ሲሉም ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የከተማው አስተዳደር ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ በአጠቃላይ ለስድስት የመምህራን መ/ቤቶች ህብረት ስራ ማህበራት የጻፈውን ደብዳቤ ደርሶት ተመልክቷል።

በዚህም ደብዳቤው ፦

- የነበረው ዲዛይን ከG+3 ወደ G+4 ማስተካከያ እንዲደረግ ተጠይቆ የG+4 ዲዛይን መሰጠቱ ፤

- ነገር ግን ይህ ዲዛይን የመምህራን መ/ቤቶች ማህበራት ከተደራጁበት አላማ አንጻር ተጻራሪ ዓላማ እንዳለው ስለተደረሰበት የG+4 ዲዛይን መሰረዙን ሌላ ደብዳቤ እስኪላክላቸው ድረስ ቀድሞ በነበረውም G+3 ዲዛይን ግንባታ ማካሄድ እንደማይችሉ ያዛል።

የመምህራኑን ጥያቄ ይዘን ጥያቄ ያቀረብንለት የከተማው ፖሊስ ጉዳዩን የጸረሙስና አካላት ወደ ፍርድ ቤት ወስደዉ ምርመራ እንደጀመሩበት በመግለጽ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#Gamo : ሰሞኑን ለሶስት ተከታታይ ቀናት በጣለ ከባድ ዝናብ በተፈጠረ የመሬት መንሸራተት በጋሞ ዞን በገረሴ ዙሪያ ወረዳ ካምአለ ባርኤ ኦሮ ቀበሌ የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል። መረጃው  የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ጉ/ጽ/ቤት ነው። @tikvahethiopia
#Update

" አራቱ ሟቾች የአንድ ቤተሰብ አባል ናቸው " - በጋሞ ዞን የገረሴ ወረዳ አስተዳዳሪ

በጋሞ ዞን፣ ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ካማአለ ባርኤ ኦሮ ቀበሌ በደረሰ የናዳ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉ ይወቃል።

ከዚህ ባለፈ ደግሞ ከሰላሳ ሰባት በላይ የቤት እንስሳት ላይ ጉዳት ደርሷል ፤ 15 ቤቶችም መፍረሳቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተረድቷል።

የገረሴ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ካሳሁን ካማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " የሟቾችን ቀብር ከአካባቢዉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን በክብር አስፈጽመናል " ብለዋል።

በአካባቢዉ ችግር ይከሰታል የሚል ቅድመ ትንበያም ይሁን ግምት ፈጽሞ እንዳልነበር ይልቁኑ በቀርከሀ የተሞላ ደን እያለ አደጋዉ መከሰቱ ሁኔታዉን አስደንጋጭ አድርጎታል ሲሉ ገልጸዋል።

አራቱ ሟቾች የአንድ ቤተሰብ አባል መሆናቸዉን የገለጹት አስተዳዳሪው በአንድ ቤት ዉስጥ ከነበሩት ሰባት ሰዎች ውስጥ በጓዳ የነበሩት አራቱ ሞተው ሶስቱ ከጓዳ ወጭ የነበሩት መትረፋቸውን ነግረውናል።

የሟቾች ስርዓተ ቀብር ከተፈፀመ በኃላ ወደ ቀጣይ ተግባር ተገብቷል ሲሉም ገልጸዋል።

አሁን ላይ የዝናቡ መጠን ከፍ እንደሚል መረጃ ማግኘታቸውን ተከትሎ ሌላ አደጋ እንዳይከሰት እንቅስቃሴ መጀመሩንና የአካባቢውን ሰው በማሸሽ በአጎራባች ቀበሌዎች ውስጥ ባሉ ትምህርት ቤቶች የጤና ኬላዎችና የእምነት ቦታዎች ማሳረፍ መጀመሩን አመልክተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ወንድም እና እህቱን በቁጥጥር ስር አድርገን ምርመራ እያካሄድን ነው " - የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንና የባህር ዳር ከተማ የመሀል ሜዳው ተጫዋች አለልኝ አዘነ ለህልፈት መዳረጉን ተከትሎ ቤተሰቦቹ  በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል። የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፥ " አሟሟቱ ድንገተኛና አሰቃቂ መሆኑን ተከትሎ የቅርብ ግንኙነት…
የእግር ኳስ ተጫዋቹ አለልኝ አዘነ ጉዳይ የት ደረሰ ?

የባህር ዳር ከነማው የመሀል ሜዳ ተጫዋች አለልኝ አዘነ ከወራት በፊት አሟሟቱ ድንገተኛና አሰቃቂ መሆኑን ተከትሎ " የቅርብ ግንኙነት ያላቸውን አካላት ይዤ ምርመራ ጀምሪያለሁ " ያለው የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ " ጉዳዩን በፍጥነት በማጣራት በቅርብ ለኢትዮጵያ ህዝብ የደረስኩበትን አደርሳለሁ " በማለት ቃል ገብቶ ነበር።

ይሁንና በጉዳዩ ላይ ሀምሌ ወር ውስጥ መግለጫ ይሰጣል መባሉ በተጨማሪ ለእስር የተዳረጉት የተጫዋቹ የቅርብ ሰዎች መሆናቸውን ተከትሎ ጉዳዩ የት ደረሰ ? የሚለው ትልቅ ጥያቄ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ጉዳይ ላይ ጥያቄ ያቀረበለት የጋሞ ዞን ፍ/ቤት ጉዳዩ ወደ ፍ/ቤት አለመመራቱንና ክስ ባልተከፈተበት በጉዳዩ ላይ መረጃ መስጠት እንደማይችል ገልጾልናል።

ይህንንም ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወቅቱ ጉዳዩን እንደያዙትና ከምርመራ በኋላ የተደረሠበትን ጉዳይ ለህዝብ እንደሚያደርሱ ቃል የገቡልን በወቅቱ የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የነበሩትን ኢንስፔክተር አብርሀምን አነጋግረናቸው ነበር።

አዛዡ በወቅቱ የሟችን ቤተሰቦች በቁጥጥር ስር አድርገው ምርመራ እያካሄዱ እንደነበር አስታውሰው አሁንም ጉዳዩ ምርመራ ላይ እንደሆነ በመግለጽ ከቦታው በመነሳታቸው እንዲሁም የፖሊስ አሰራር በዚህ ሰአት መረጃ መስጠትን ስለሚከለክል ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን አሁንም ይከታተላል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
🔈 #የመምህራንድምጽ

" መምህራን እየተራቡ ስለትምህርት ጥራት ማዉራት አግባብ አይደለም " - የደቡብ ኦሞ ዞን መምህራን

" በዚህ ደረጃ ክፍያ ይዘገያል ብለን ባናስብም ችግሩ ካለ በቅርብ ይፈታል " - የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊ

ከሰሞኑ በተደጋጋሚ በደረሰን የቅሬታ መልእክት በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ክልል የደቡብ ኦሞ ዞን መምህራን ላለፉት ሁለት ወራት ደሞዝ እንዳልተከፈላቸዉ በመግለጽ በተለያዩ ፕሮግራሞች ውስጥ መሳተፍ እንዳልቻሉ ነግረዉናል።

መምህራኑ እንደሚሉት አሁን ላይ ከፊሉ በመንግስት አቅም ማሻሻያ ፕሮግራሞች ግማሹ ደግሞ በራሱ ፍላጎት ወደተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ቢያቀናም ደሞዝ አለመለቀቁን ተከትሎ ግን ችግር ላይ ወድቀዋል።

አሁን ላይ በገቡባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች ዉስጥ አላማቸዉን ካለማሳካታቸዉ ባለፈ ጥለዋቸዉ የመጡ ቤተሰቦቻቼዉ ረሀብ ላይ መዉደቃቸዉን ተከትሎ የሄዱበትን የትምህርትና ስልጠና ፕሮግራሞች ጥለዉ ለቀን ስራ መዳረጋቸዉን ይገልጻሉ።

ከዚህ በተጨማሪ በትራንስፖርት ችግር ምክኒያት ብዙ መምህራን በሚያስተምርበት አካባቢ ቢቀሩም በእንቅርት ላይ እንዲሉ ባሉበት አካባቢም የወባ ወረሽኝ አስቸጋሪ ሆኖባቸዋል።

ችግሩን የመንግስት አካላት ያዉቁታል የሚሉት የጎሪጌሻ የሜኒት ማጅና ቱም የጎልዲያና ሻሻ እንዲሁም የጋቺት እና ሱርማ ወረዳ  ቅሬታ አቅራቢዎች " መምህራን እየተራቡ ስለትምህርት ጥራት ማዉራት አግባብ አይደለም " ብለዋል።

በጉዳዩ ላይ ከቀናት በፊት ያነጋገርናቸዉ የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፊዉ አቶ  በበኩላቸዉ በዚህ ደረጃ ክፍያ ይዘገያል ብለን ባናስብም ችግሩ ካለ በቅርብ ይፈታል ብለዋል።

ሀላፊዉ አክለዉም ምናልባትም ችግሩ የበጀት ከሆነ አሁን ላይ በየወረዳዉ ግብር እየተሰበሰበ በመሆኑ በተቻለ ፍጥነት ችግሩ  ይፈታል በማለት የደሞዝ ችግሮ በቅርቡ እንደሚፈታ ገልጸዉልናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈 #የአርሶአደሮችድምጽ ° " ' እኛ ያቀረብነውን ዘር ካልገዛችሁ ማዳበሪያ አትወስዱም ' በመባላችን የእርሻ ወቅት እንዳያልፍብን እስከ 8 ሺህ ብር ማዳበሪያ ለመግዛት ተገደናል " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ሻመና ከተማና አካባቢው አርሶአደሮች ° " ያቀረብነውን ምርጥ ዘር ካልወሰዳችሁ ብሎ ያስገደደ የለም ማዳበሪያ ብቻ የሚፈልግ መውሰድ ይችላል " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ አስተዳዳሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ…
🔈 #የአርሶአደሮችድምጽ

ሲዳማ !

" የማዳበሪያ ችግር የለም ተብሎ በሚዲያ ቢነገርም በቂ ማዳበሪያ እየደረሰን አይደለም " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ አርሶ አደሮች

ከሰሞኑ " ዘር ካልገዛችሁ ማዳበሪያ አይሰጣችሁም ተባልን " ያሉ የሀዋሳ ዙሪያ አርሶ አደሮች ቅሬታ ማቅረባቸዉን ዘግበን ነበር።

በወቅቱ  የማዳበሪያ ችግር እንደሌለና ወደግብርና ቢሮ በመምጣት መዉሰድ እንደሚቻል ከምርጥ ዘር ጋር በተያያዘ አርሶአደሩን የሚጠቅም አካሄድ መሆኑን ይሁንና ገበሬዉ የራሱ ዘር ካለዉ እንደማይገደደ ተገልጾም ነበር።

ይሁንና ከመረጃዉ በኋላ " የማዳበሪያ ችግር የለም " ተብሎ በሚዲያ ምላሽ ከመሰጠቱ በላይ በስብሰባ ወቅት " መጋዝናችን ሙሉ ነዉ " ብንባልም በአግባቡ እየተሰጠን አይደለም ሲሉ በድጋሜ የአካባቢዉ አርሶአደሮች ቅሬታ አቅርበዉልናል።

" አሁን ላይ የዘር ወቅት እያለፈ በመሆኑ ከፍተኛ ስጋት ዉስጥ ገብተናል " የሚሉት አርሶ አደሮቹ " አራትና አምስት  ኩንታል ለሚያስፈልገዉ አምስት ሄክታር የለሰለሰ ማሳ አንድ ኩንታል ብቻ ስለምን እንደሚሰጠን አይገባንም " በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል።

" ማዳበሪያዉ በቂ አለመሆኑን የአካባቢዉ የግብርና ባለሙያዎች ያውቃሉ። እንደኛ ከማዘን ዉጭ መፍትሄ መስጠት አልቻሉም " ሲሉ ገልጸዉ ጉዳዩ በአመራሩ እጅ መያዙን አስረድተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ፥ " ቀኑን ሙሉ ስራ በመፍታት መጋዝን በር ላይ የሚዉለዉ አርሶ አደር ሀያ ሰላሳ ሰዎች ከተስተናገዱ በኋላ ወደቤታችሁ ሂዱ ይባላል በማለት መጋዝኑን የሞላዉ ማዳበሪያ ለማን ነዉ ? " በማለት ጠይቀዋል።

ከሳምንት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " የማዳበሪያ ችግር የለም ከአካባቢዉ አርሶ አደር ጋርም የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል " ያሉት የወረዳዉ አስተዳዳሪ  " መሬቱን ያዘጋጀ ገበሬ የፈለገዉን ያክል ማዳበሪያ መዉስድ ይችላል " በማለት አንዳች ቅሬታ ያለበት አርሶ አደር ካለ ሊያናግረን ይችላል ማለታቸዉ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🔈#Konso

" ታጣቂዎቹ ተመልሰው ይመጣሉ በሚል አሁንም በፍርሀት ውስጥ ነን " - የሰገን ዙሪያ ወረዳ ነዋሪዎች

ከሰሞኑ በወረዳው ዋና ከተማ ሰገን በድንገት ከወደደራሼ አቅጣጫ ተነስተው መጥተዋል ከባሉ ታጣቂዎች በፖሊስ ፣ በከተማው አስተዳደርና ፣ በንጹሀን ዜጎች ላይ በከፈቱት ጥቃት ከ10 በላይ ሰዎች ሲገደሉ በርካቶች መቁሰላቸዉን ተሰምቷል።

ቅዳሜ አመሻሽ ጀምሮ ጥቃቱ መከፈቱን የገለጹት ነዋሪዎች በከተማዉ ውስጥ የነበሩ ፖሊሶችና የአስተዳደር ቢሮ የጥቃቱ ኢላማና ቀዳሚ ሰለባ ከመሆናቸው በላይ የመጀመሪያ ዙር ጥቃት እንደተፈጸመ ድጋፍ የሚሰጥ ሀይል ከተለያዬ ቦታ ወደስፍራዉ በፍጥነት አለመላኩን ተከትሎ ሁለተኛ ዙር ጥቃት በበነጋታዉ ጠዋት መከፈቱን አስረድተዋል።

የወረዳው ነዋሪዎች " የሰው ነፍስና በርካታ ንብረት መዳን ሲችል ጉዳት ደርሷል " ሲሉ ገልጸዋል።

እስከእሁድ ጠዋት በቀጠለዉ ተኩስ ሱቆች መዘረፋቸውን ፣ ቤቶች መቃጠላቸዉና አካባቢው አስፈሪ መልክ መያዙን ተከትሎ አሁን ላይ በርካታ ሴቶችና ህጻናት ወደአጎራባች መንደሮች እየተሰደዱ መሆናቸውን ተናግረዋል።

" ከሀይቤና ቀበሌ በመነሳት የተለመደ የከብት ዘረፋና የነብስ ማጥፋት ወንጀሎች ነበሩ " ያሉት ነዋሪዎቹ " ካሁን በፊት ሁኔታውን መንግስት ይቆጣጠረዉ ዘንድ ጥያቄ ማንሳታቸውን ለአብነት እንኳን ከሳምንት በፊት በወረዳው አስተዳደር ከማህበረሰቡ ጋር በነበረው ስብሰባ መነሳቱን " ገልጸዋል።

አሁንም ቢሆን ድንገት በመምጣት ጥቃት ያደርሳሉ የሚል ግምት እንዳላቸው ተናግረዋል።

" ሁኔታዉ ከቁጥጥር ዉጭ ከመሆኑ በፊት ከወረዳው ባለፈ የዞንና የክልል አመራሮች ጣልቃ መግባት አለባቸው " በማለት " ቤታቸዉ ለተቃጠለባቸውና ንብረታችዉ ለወደመባቸው ግለሰቦች ዝናብ ላይ በመሆናቸው አፋጣኝ ድጋፍ እንፈልጋለን " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

" ነዋሪዎቹ የመንግስት ኃይሎች ለእርምጃ መዘግየት ዋጋ አስከፈለን ሲሉም " አክለዋል።

ግጭቱን አስመልክተዉ የሰገን ዙሪያ አስተዳዳሪ አቶ ኡርማሌ ኡጋንዴ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድረገጅ በሰጡት ቃል አስራ አንድ ሰው መሞቱን ጠቁመዋል።

ነዋሪዎቹ ግን የሟቾቹን ቁጥር አስራ ሶስት በማድረስ ስምንቱን ነዋሪ አምስቱ ደግሞ ፖሊስ መሆናቸዉን ገልጸዉ ከዚህም ሊያልፍ ይችላል ብለዋል።

አሁን ላይ ከወረዳዉ ባለፈ በዞኑ ደረጃ የኮንሶ ዞን የሀዘን መግለጫ በማዉጣት ሁኔታዉን ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ ላይ መሆኑን የገለጸ ሲሆን የዞኑን ህዝብ ግንኙነት ቢሮና የፖሊስ መምሪያ ለማነጋገር ያደረግነዉ ጥረት አልተሳካም።

ዞኑ " ጽንፈኛ እና አሸባሪ " ያላቸው ኃይሎች በኮንሶ ዞን የሰገን ዙሪያ ወረዳ በፈጸሙት ጥቃት ንጹሃን ሰዎችና የፖሊስ አባላት መገደላቸውን አረጋግጧል።

ምን ያህል ሰው እንደተገደለ የሰጠው ቃል የለም።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Omo

የኦሞ ወንዝ ሙላት ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው አርሶአደር በ4ቱም አቅጣጫ ንብረቱን ጥሎ መሸሽ ላይ ነው።

ችግሩ እንደሚከሰት ታውቆ በርካታ ስራ ሲሰራ ቢቆይም የኦሞ ወንዝ መጠን ከተለመደውና ከታሰበው ውጭ መሆኑን ተከትሎ ግን ለዞኑ መንግስትም ሆነ ለግብረሰናይ ድርጅቶች ሁኔታው ከባድ ሆኖባቸዋል።

የወንዙ ሙላት ከባድ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ አርብቶ አደሩን በአራት ጊዜያዊ መጠለያ እንዳስቀመጡትና ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚያሻዉ የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማዕከል ማልኮ ገልጸው " በአሁኑ ወቅት የውሃው መጠን ከተለመደው ውጪ እየጨመረና ሰፊ ቦታ እየያዘ ከመምጣቱ የተነሳ ለኦሞራቴ ከተማ ማህበረሰብ እንደሚያሰጋ " ተናግረዋል ።

ችግሩ እየባሰ የመጣው የውሃውን አቅጣጫ የማስቀየርና የማፍሰስ ስራዎች በኢንቨስተሮች እርሻ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እያስከተለ ነው በሚል በጅምር በመቆሙ መሆኑን የሚያነሱት የአካባቢዉ ነዋሪዎች በበኩላቸው ችግሩ በየአመቱ የሚፈጠር በመሆኑ ኑሯቸውን አስቸጋሪ እንዳደረገዉ ይገልጻሉ።

በመሆኑም አሁን ላይ ማህበረሰቡ ቤቱ እየተዋጠበት ከብቱ እየሞተበትና የሚቀምሰውም በመጥፋቱ ተስፋ በመቁረጥ አካባቢውን ጥሎ መሸሽ መጀመሩ ተሰምቷል።

ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ከኦሞ ወንዝ ሙላት ጋር ተያይዞ በአከባቢው በተደጋጋሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ ሲከሰት እንደነበር የገለጹት የዳሰነች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ በበኩላቸው አምና ከ79 ሺህ በላይ አርብቶ አደሮች በወንዙ ሙላት መጥለቅለቅ ከመኖሪያ ቀዬአቸው መፈናቀላቸውን ይናገራሉ።

እነዚህ አርብቶ አደሮች እስከ ዛሬ በጊዜያዊ ማቆያ ስፍራ እንዲቆዩ የተደረገ መሆኑን የሚገልጹት አቶ ታደለ ለእርሻ ስራ በሚል ወደ ቀድሞ ቀያቸው በተመለሱት ላይ አሁንም ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል ።

አሁን ላይ ወንዙ መደበኛ የፍሰት አቅጣጫውን በመልቀቅ የጉዳት መጠኑን አስፍቶና አርብቶ አደሩን አፈናቅሎ ለማህበራዊ ችግር እየዳረገ ሲሆን በኢፌዴሪ ውሃና ኢነሪጂ ሚኒስቴር አማካኝነት ችግሩን ለመቅረፍ የተጀመረው የመከላከያ ፕሮጀክት መፍትሄ ያመጣል ቢባልም ሊጠናቀቅ አልቻለም።

በዚህ ምክኒያትም አሁን ላይ በ33 ቀበሌዎች የነበሩ መሠረተ ልማቶች ትምህርት ቤቶች ጤና ኬላዎችና መኖሪያ ቤቶች በውሃ ሊከበቡና ነዋሪው ለከፋ ችግር ይጋለጥ ዘንድ ምክኒያት ሆኗል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Omo የኦሞ ወንዝ ሙላት ከቁጥጥር ውጭ መሆኑን ተከትሎ የአካባቢው አርሶአደር በ4ቱም አቅጣጫ ንብረቱን ጥሎ መሸሽ ላይ ነው። ችግሩ እንደሚከሰት ታውቆ በርካታ ስራ ሲሰራ ቢቆይም የኦሞ ወንዝ መጠን ከተለመደውና ከታሰበው ውጭ መሆኑን ተከትሎ ግን ለዞኑ መንግስትም ሆነ ለግብረሰናይ ድርጅቶች ሁኔታው ከባድ ሆኖባቸዋል። የወንዙ ሙላት ከባድ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ አርብቶ አደሩን በአራት ጊዜያዊ…
#ALERT🚨

⚠️ " በውሀ ተውጠን ከማለቃችን በፊት ድረሱልን " - የኦሞራቴ ከተማ ነዋሪዎች

🔴 " የውሀው አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው ፤ የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ነው " - የአካባቢዉ አስተዳደር

የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ ሀብት ንብረቴ የሚላቸዉ ከብቶች ማለቁን ያየዉ የደቡብ ኦሞ አርብቶ አደር በአራቱም አቅጣጫ እየተሰደደ መሆኑን ጠቅሰን አካባቢው ትኩረት ይሻል ስንል ከቀናት በፊት መዘገባችን ይታወሳል።

ይሁንና አሁን ላይ የኦሞ ወንዝ ከአቅም በላይ በመሙላቱና የአካባቢዉ መሬት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ መተኛቱን ተከትሎ የወረዳዉ ዋና ከተማ የሆነችዉን ኦሞራቴን ደሴት ሲያደርጋት ህዝቡም መዉጫ በማጣት ጭንቀት ውስጦ መግባቱን ሰምተናል።

የድረሱልን ጥሪያቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያደረሱት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ለአመታት በወንዙ ሙላት ሲቸገሩ መቆየታቸውንና አሁን ግን ከርቀት ወደምትገኘው ኦሞራቴ ከተማ በእጅጉ መጠጋቱ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ ከመዋጣቸው በፊት የሚመለከተዉ አካል እንዲደርስላቸው ተማጽነዋል።
 
በአካባቢው የነበሩት አርብቶ አደሮች በበኩላቸው ሙሉ በሙሉ የግጦሽ መሬቶች በወንዙ ተቆርሶ መወሰዱንና ከብቶቻቸው ማለቃቸውን ገልጸዉ አሁን ላይ የተጠለሉባቸው ጊዜያዊ መጠለያዎች በውሀው እየተጥለቀለቁ በመሆኑ ህይወታቸዉ አደጋ ላይ መውደቁን አስተድተዋል።

ስለሁኔታዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ " የዉሀዉ አመጣጥ እጅግ አስፈሪ ነው " ብለዋል።

ማህበረሰቡ አፈር በማዳበሪያ እየቋጠረ ግድብ መስራቱ ውሀውን ስላላስቆመው የፌደራል መንግስት ማሽነሪዎች ቶሎ እንዲያቀርብልን እየጠየቅን ብለዋል።

" አሁን ላይ የኦሞራቴ ከተማ ከጊዜያዊ መጠለያዎችም ሆነ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ለመገናኘትም ሆነ ለመሸሽ ቱርሚን የሚያገናኘዉ ድልድይ በመሰበሩና ወደኬኒያ የሚወስደዉ ዋና መንገድ በውሀው ክራክ በማድረጉ ደሴት ሆናል " ሲሉ ገልጸዋል።

በመሆኑም " የኦሞራቴ ህዝብ የከፋ ችግር ላይ በመሆኑ የሚመለከተው አካል አፋጣኝ ድጋፍ ሊያደርግለት ይገባል ሲሉ " ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🔈#የመምህራንድምጽ

ድምጻቸውን ለማሰማት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ተሰባስበው በመመካከር ላይ የነበሩ መምህራን በፖሊስ ተበተኑ።

በወላይታ ዞን ስር ያሉ መምህራን " ሀሳባችን እንዳንገልጽ ፖሊስ አደናቀፈን " ሲሉ ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

" ወደመንግስት አካላት በመሄድ ረሀባችን እወቁልንና ደሞዛችን በወቅቱ ክፈሉን በማለት  ልናሳዉቅ እንጅ ረብሻ ለመፍጠር አልነበረም ተሰባስበን ስንመካከር የነበረው " የሚሉት መምህራኑ " ከረሀባችን በላይ ተሰባስበን በመመካከር ድምጻችን እንዳናሰማ መደረጉ አሳዝኖናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ላለፉት 3 ወራት ያለደሞዝ ቆይተን የሰኔን ብቻ ሰጥተውናል ይሄ ለመምህራን ችግር ግድ የለሽ መሆናቸውን " አሳይቶናል ብለዋል።

አሁን ላይ በዱቤ ይሰጡን የነበሩ ነጋዴዎችም መከልከል በመጀመራቸዉ ተቸግረናል ሲሉ ለቲክቫህ አስረድተዋል።

" ስራቸውን ለመስራትና የባለስልጣናቱን ትእዛዝ ለመፈጸም የመጡ ፖሊሶች  እንኳን ረሀባችሁን እኛም እናውቀዋለን " በማለት እያዘኑ በተኑን በማለት ሀዘናቸውን የገለጹት መምህራኑ " ከዚህ በላይ ሞት እንጅ ሌላ ተስፋ እየታየን አይደለም "  ሲሉ ያሉበትን ሁኔታ ገልጸዋል።

" በመሆኑም አሁን ላይ በፖሊስ በመገፋታችንና ባለስልጣናቱም ስብሰባ ገቡ በመባላቸዉ  ወደመጣንባቸው አካባቢዎች ብንመለስም ረሀባችን የከፋ መሆኑን ለመግለጽ  ተጠናክረን መጮሀችን ይቀጥላል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቀናት በፊት በክልሉ ስላለዉ የመምህራን ደሞዝ መዘግየትና መቆራሪጥ ላነሳንለት ጥያቄ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ወረዳዎች ከገቢያቸዉ ክፍያ የሚፈጽሙበት አስራር መዘርጋቱንና ችግሮች ከተፈጠሩ ጣልቃ በመግባት እርማት እንደሚደረግ መግለጹ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈 #Silte ስልጤ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ በመከሰቱ በርካታ ወገኖቻችን ለመፈናቀል መገደዳቸውን ነዋሪዎችና ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተለይ በዞኑ የስልጢ ወረዳ ጎፍለላ ቀበሌ በጎርፍ አደጋ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል። ወገኖቻችን ሕይወታቸውን ለማትረፍ ሲሉ ቤት ንብረታቸውን ትተው ወደ ተለያዩ ስፍራዎች ተፈናቅለዋል። አደጋው እንስሳትን ጨምሮ በንብረት ላይ ውድመት አስከትሏል…
#ATTENTION🚨

ከ6 ሽህ በላይ ወገኖቻችን ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።

በስልጤ ዞን ባሉ 2 ወረዳዎችና 8 ቀበሌዎች ከአንድ ሺህ በላይ አባዉራ ቤትና ማሳዉ በውሀ መዋጡን ተከትሎ ከአካባቢዉ መነሳታቸው ተሰምቷል።

እስካሁን ባለዉ መረጃ ከ6 ሺህ በላይ ሰዎች ድጋፍ እንደሚሹ የዞኑ የአደጋ ስጋት ኃላፊ ወሲላ አሰፋ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ጎርፉ የፈጠረዉን ሀይቅ በዚህ ወቅት ማፋሰስ አሰቸጋሪ መሆኑን ያነለከቱት ኃላፊዋ " የሁለቱን ወረዳ ነዋሪዎች በክልሉና በዞኑ ድጋፍና ትብብር አውጥተን በትምህርት ቤቶችና በአርሶ አደሩ የስልጠና መዕከላት አስፍረን ስላልበቃን ትርፍ ቤት ያለዉ ሁሉ ትርፍ ቤቱን በመስጠት በጊዜያዊነት ለማስጠለል ተሞክሯል " ብለዋል።

" የመሬቱ አቀማመጥና የጎርፉ ብዛት የፈጠረዉ የዉሀ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ዝናቡ እስኪቆም ዘላቂ መፍትሄ መስጠት አንችልም ፤ ይሁንና አንዳንድ ቦታ ላይ ቋሚ ሰብሎች እንዳይጎዱና ቤቶች እንዳይበሰብሱ አንዳንድ ስራዎች እየሰራን ነው " ሲሉ አክለዋል።

አሁን ላይ ለተጎጂዎች እየቀረበ ያለው የምግብ እና አልባሳት ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ የዞኑ አደጋ ስጋት ምክር ቤት ተቋቁሞ ድጋፍ የሚሰበሰብበት መንገድ መመቻቹትን አመልክተዋል።

የስልጤ ዞን የጎርድ ድጋፍ ማሰባሰቢያ አካዉንት 1000647585535 (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) መሆኑ ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 ኦሞ ወንዝ በከፍተኛ ሁኔታ በመሙላቱ የወንዙ ውሃ እና የቱርካና ሀይቅ ይዞታውን እያሰፋ በመሆኑ በኦሞራቴ ከተማ በ1.9 ኪ/ሜ ርቀት አከባቢ በተለያዩ ቦታዎች የመሬት መሰንጠቅ እዲሁም ውሃው ውስጥ ለውስጥ እየሄደ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል። @tikvahethiopia
#ትኩረት🚨

ኦሞራቴ ዙሪያ 500 ሜትር እርዝመትና ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለዉ የመሬት መሰንጠቅ ተከስቷል።

የከተማዉ ነዋሪዎች " የመሬት መሰንጠቁ ውሀዉ መድረሱን ያሳያልና ድረሱልን " እያሉ ነው።

ከሰሞኑን የኦሞ ወንዝ መሙላቱን ተከትሎ በርካታ አርብቶ አደሮች መፈናቀላቸውንና አካባቢው በውሀው ከመጥለቅለቁ ባለፈ የወረዳው ዋና ከተማ ኦሞራቴ መቅረቡ የከተማውን ማህበረሰብ ስጋት ውስጥ እንዳስገባው ነግረናችሁ ነበር።

አሁን ደግሞ የተፈጠረዉ የመሬት መሰንጠቅ ሌላ የድንጋጤ ምክኒያት ሆኗል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች " ውሀው ከመቅረቡ ባለፈ በአካባቢው የመሬት መሰንጠቅ መፈጠሩ በነዋሪው ላይ ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሯል " ብለዋል።

ውሀው ወደ ከተማው መጠጋቱን ለመከላከል እና አቅጣጫውን ለማስቀየር በሰው ሀይል ጥረት ቢደረግም ውሀው ውስጥ ለውስጥ መጠጋቱን የፈጠረዉ የመሬት መሰንጠቅ ይጠቁማል ብለዋል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸዉን የሰጡን የወረዳዉ አስተዳዳሪ አሁን ላይ ህዝቡን ያሰጋዉ አምስት መቶ ሜትር ርዝመትና ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው የመሬት መሰንጠቅ በመፈጠሩ ነው ብለዋል።

አንድ ዶዘር መድረሱንና ስካቫተር እየመጣ መሆኑን ጠቁመው ይህም የውሀዉን አቅጣጫ ለመቀየርና ለማፍሰስ ይረዳል በማለት ይህም እየተከሰተ ያለውን የመሬት መሰንጠቅ አስቁሞ ማህበረሰቡን ያረጋጋል ብለዋል።

አሁን ላይ ምንም እንኳን ዶዘር መድረሱና ስካቫተር እየመጣ መሆኑ ተስፋ ቢሰጠንም የነዳጅ የሰዉ ሀይልና አጠቃላይ ኦፕሬሽን ኮስት ስለሚያስፈልገን የክልሉና የፌደራሉ መንግስት ሊያግዘን ይገባል ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
#ትኩረት🚨

ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል።

" ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል።

ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች የ9 ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ የአካባቢዉ ባለስልጣናት መታሰራቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

ባለፉት ጊዜያት የነበረዉ የንጹሀን ግድያ  ለተወሰነ ጊዜ ረገብ ቢልም ከሰሞኑ እንደገና ባገረሸ ግጭት የ9 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 4 ሰዎች ደግም ቆስለዋል።

ይህን ተከትሎ አካባቢዉ ውጥረት ዉስጥ በመግባቱ አሁን ላይ በአካባቢዉ የሚኖሩ ንጹሀን በፍርሀት ውስጥ ናቸው።

" ኢንሴኖ ከተማና አካባቢው በየጊዜው በሚነሳው ግጭት ገጠራማው ቀበሌ የሚኖረው ምስኪን ግድያ ሲፈጸምበት ቆይቷል " የሚሉት ነዋሪዎቹ " በአካባቢው ሲስተዋል የነበረዉ የበቀል መጠፋፋት አሁንም በከፋ ሁኔታ ተመልሶ ይመጣል በሚል ተጨንቀናል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከሰሞኑ በማረቆ ልዩ ወረዳ በሌሊት በተፈጸመ ጥቃት የ7 ሰዎች ህይወት (4ቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት) እንዲሁም በመስቃን ደግሞ 2 ሰዎች ህይወታቸው መቀጠፉን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ሁኔታውን የመንግስት አካላት ቶሎ ካልተቆጣጠሩት ግጭቱ ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ፍርሀታቸውን አስረድተዋል።

ስለሁኔታዉ የጠየቅናቸዉ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ ተካልኝ ንጉሴ ስለሁኔታው መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ይሁንና በልዩ ወረዳዎቹ ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ አካባቢውን ለማረጋጋት ወደቦታው ያቀናው የጸጥታ ኃይል ጥቂት የአካባቢው ግለሰቦችን ጨምሮ ግጭት በተፈጠረባቸዉ አካባቢዎች ለጊዜዉ ስማቸዉ አይጠቀስ የተባሉ የወረዳ ከፍተኛ ባለስልጣናትን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

አሁን ላይ ኢንሴኖን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የፌደራልና የክልል የጸጥታ አካላት ተሰማርተው ህዝቡን እያረጋጉ ሲሆን የህዝቡ እንቅስቃሴ ግን በጅጉ መቀዛቀዝ ይስተዋልበታል።

ይህ አካባቢ በተደጋጋሚ የሰዎች ህይወት የሚቀጠፍበት ፣ ዜጎች የሚፈናቀሉበት ሲሆን ዘላቂና አስተማማኝ መፍትሄ ሳይገኘ ዛሬም በዛው ቀጥሏል።

#Update : ከመሸ ስልክ ያነሱልን የምስራቅ ጉራጌ ወንጀል መከላከል ዲቪዥን ኃላፊ ኮማንደር መሀመድ ሀሰን " አሁን ላይ ሁሉም አካባቢ ሰላም " መሆኑን ጠቅሰው ስለሁኔታው አሁን ላይ መረጃ መስጠት ከባድ መሆኑን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
🔈 #የነዋሪዎድምጽ

• " ቤንዝል ሙሉ በሙሉ  ከጠፋ 4 ቀናት መሆኑን ተከትሎ ከስራ ውጭ ሆነናል " - በሀዋሳ ከተማና አካባቢዉ የሚገኙ አሽከርካሪዎች

• " ከጅቡቲ የተነሱ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች እስኪደርሱ በትእግስት ጠብቁ " - የሀዋሳ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ

ከሰሞኑ በነዳጅ እጥረት ምክኒያት አልፎ አልፎ የነዳጅ ፕሮግራም ሲወጣ ቢቆይም ካለፉት አራት ቀናት ጀምሮ ግን ሙሉ በሙሉ ድልድል ባለመውጣቱና በከተማው ውስጥ ያሉ ሁሉም ማደያዎች " ቤንዝል  የለም " በማለታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ችግር ውስጥ ገብተናል ያሉ የሀዋሳና አካባቢው አሽከርካሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

አሁን ላይ በህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ አሽከርካሪዎች ስራ መፍታታቸዉን ሲገልጹ አንዳንዶች ደግሞ እጅን አጣጥፎ ላለመቀመጥ ከህገወጥ ቤንዝል ሻጮች አንድን ሊትር እስከ ከመቶ ሀምሳ ብር በላይ እየገዙ መሆኑን ይናገራሉ።

በዚህ ደረጃ ቤንዝል መጥፋቱ ግራ አጋብቶናል የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ አሁን ላይ አሽከርካሪዉም ማህበረሰቡም ችግር ላይ ነው ብለዋል።

የአሽከርካሪዎቹን ቅሬታ ይዘን ያነጋገርናቸው የሀዋሳ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ኃላፊዉ አቶ ተመስገን ችሎት " ላለፉት ሶስት ቀናት ድልድል ያልነበረው ከተማ ውስጥ የሚገኙ ማደያዎች ቤንዝል በመጨረሳቸዉ ነው " ብለዋል።

በዚህ ሰአት መንገድ የጀመሩ ነዳጅ ጫኝ ቦቴዎች ከጅቡቲ መነሳታቸውን የሚገልጽ መረጃ አለን የሚሉት ኃላፊዉ እነዚህ ቦቴዎች እስኪደርሱ  ሁለት ሶስት ቀናት መታገስ ይኖርብናል ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🔈 #የሰራተኞችድምጽ

" ክፍያችን ከኑሮ ውድነት አንጻር በጣም የወረደ በመሆኑ ህይወት አስቸጋሪ ሆኖብናል " - በሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ ሰራተኞች

" በ1000 ብር ደሞዝ ኑሮን መቋቋም አቃተን "  ያሉ የሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክ ሰራተኞች የሚከፈለን ገንዘብ ከቤት ኪራይ የማያልፍ በመሆኑ በረሀብ እየተሰቃየን ነው በማለት ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰጥተዋል።

የረከሰ ቤት ፍለጋ ከከተማ ወጣ ያሉ ሰፈሮች በመምረጥ ሶስት አራት ሆነዉ እንደሚከራዩና ጠዋት አንድ ሰአት ለመድረስ ከአስራ ሁለት ሰአት በፊት ተነስተዉ ያውም በባዶ ሆድና በእግር እንደሚመጡ የሚናገሩት ሰራተኞቹ " አሁን ግን ኑሮ ጣሪያ በመንካቱ በዚህ መልክ እንኳን መቀጠል አልቻልንም " ብለዋል።

" ምንም እንኳን የምሳ ድጋፍ ቢደረግልንም በአንድ ከተማ በአንድ የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ያለዉ ልዩነት ያሳዝናል " በማለት በፓርኩ ውስጥ እንኳን ልዩነት መኖሩን ይገልጻሉ።

አንዳንድ ሼዶች የትራንስፖርት አገልግሎትን ጨምሮ የትርፍ ሰአት ስራ የሚያመቻቹ ቢሆንም ሌሎች ደግሞ ከአንድ ሽህ ብር ደሞዝ ውጭ ምንም ትርፍ ነገር አይሰጡም።

" በዚህም ኑሮን መግፋት ተራራ ሆኖብናል " በማለት ያሉበትን የስቃይ ህይወት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።

ሰራተኞቹ " በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አይደለም የቤት ኪራይ ከፍለንና የምግብ ወጭ ሸፍነን ለመኖር ይቅርና ሰርተዉ ይረዱናል ብለዉ በማሰብ ወደላኩን  ቤተሰቦቻችን ለመመለስ እንኳን አስቸጋሪ ሆኖብናል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህን የሰራተኞች እሮሮ ይዞ ምላሽ ለማግኘት የሀዋሳ ኢንደስትሪ ፓርክን ደጋግሞ ቢያናንኳኳም ለጊዜዉ ምላሽ ማግኘት አልቻልንም።

ይሁንና በቅርቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ስራ አስፈጻሚው አቶ ዘመን ጁነዲን " የሰራተኛውን ምቹ ከባቢ መፍጠር የኛም ፕራይወሪቲ ነው " ብለው ነበር።

አሁን ላይ ከሚመለከታቸዉ አካላት በተለይም ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር እየተነጋገርሩ መሆኑን የገለጹት አቶ ዘመን ከክፍያ በተጨማሪ ትራንስፖርት ምግብና መሰል ድጎማዎች እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Sidama

" በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰና እያስመረረ የሚቀጥል አመራር አይኖርም " - አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ

በሲዳማ ክልል የጸጥታ አካላት ግምገማ መደረጉን ተከትሎ በርካታ የፖሊስ አዛዥች ከስልጣን ሲነሱ በጥቂቶች  ላይ ከህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ምርመራ እንደተጀመረባቸው ተሰምቷል።

ከሰሞኑ በክልሉ ሲካሄድ የሰነበተውን የግምገማና የውይይት መድረክ አሰመልክተው ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ኃላፊዉ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ " በህዝብ ላይ ጉዳት እያደረሰና እያስመረረ የሚቀጥል አመራር አይኖርም " ብለዋል።

" በዚህ መሰረት በተደረገ ግምገማ በክልሉ በተለያዩ ዞን ወረዳና ከተማ አስተዳደር ውስጥ
ባሉ መዋቅር ይሰሩ ከነበሩ አመራሮች ውስጥ ሰባት የፖሊስ አዛዦችና ሙሉ የአንድ ክፍለ ከተማ የማኔጅመንት አባላት ላይ ከህገወጥ ንግድና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ምርመራ እንዲጀመር ታዟል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ከተደረጉ አመራሮች መካከል ፦
- የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ፣
- የሆኮ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ
- የጨቤ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ይገኙበታል።

የዳዬ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ከኃላፊነታቸው ታግደው ከመልካም አስተዳደር ችግሮችና ከህገወጥ ንግድ ጋር ተያይዞ የተጠረጠሩባቸው ጉዳዮች እንዲጣራ ታዟል።

በተጨማሪም ደቡባዊ ሲዳማ ዞን ፖሊስ መምሪያ ዋና አዛዥ በዞኑ ህገ-ወጥ ንግድና የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ እየተበራከተ በመምጣቱና መቆጣጠር ባለመቻላቸው ከኃላፊነታቸው ሊነሱ ችለዋል።

በወረዳ ደረጃ ደግሞ የሁላ ወረዳ፣ የአለታ ጩኮ ወረዳ፣ የቡርሳ ወረዳና የጠጢቻ ወረዳ ፖሊስ አዛዦች የተነሳባቸው ጉዳዮች ተጣርቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት አቅጣጫ ተቀምጧል።

በሀዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ ያሉ ጠቅላላ ማኔጅመንቱ ከኃላፊነት እንዲነሱ መደረጋቸው ተነግሯል።

በመድረኩ በርካታ ችግሮች የተነሱ ሲሆን ለአብነትም ኪራይ ሰብሳቢነትና ባለጉዳይን ማማረር ጎልተዉ የተነሱ ክፍተቶች ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia