TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ነእፓ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ የተናገሩትን ንግግር አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።

ዛሬ በተካሄደው 6ኛው የህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት 1ኛ አመት የስራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ ላይ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አብዱልቃድርን ለአዲስ አበባ ም/ቤት የካቢኔ አባልነት ተጠይቀው ፓርቲያቸው እንዳልፈቀደ ተናግረው ነበር።

ይህን ተከትሎ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ብልፅግና ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በጋራ ለመስራት ያለውን ፍላጎት አድንቆ ለሀገሪቱ ፖለቲካ ጠቃሚ በመሆኑ ደግፋለሁኝ ብሏል።

ፓርቲው በአዲስ አበባ ካቢኔ ውስጥ ለመሳተፍ ስምምነቱን የገለፀ ሲሆን ከአፈፃፀም ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ከብልፅግና ጋር ውይይት ማድረጉን አሳውቋል።

በተደረገው ውይይትም በአ/አ ካቢኔ ውስጥ እንዲሳተፉ የተጠየቁት የፓርቲው ሊቀመንበር ምትክ ሌላ የፓርቲው ከፍተኛ አመራር እንዲሳተፉ ከብልፅግና ጋር ስምምነት መደረሱን አስታውሶ ፓርቲውን ወክለው በአ/አ ካቢኔ አባል እንዲሆኑ የተመረጡት የነእፓ አመራር ለብልፅግና እንዳሳወቀ በመገለጫው ጠቅሷል።

ይሁን እንጂ ነእፓ መርጦ የላካቸው የፓርቲው ተወካይ በካቢኔው ሳይካተቱ መቅረታቸውን ገልጿል፤ይህንንም በተመለከተ ከብልፅግና የተሰጠው ማብራሪያ እንደሌለም አሳውቋል።

ፓርቲው ሀገርን በጋራ ለማገልገል ተፎካካሪዎች በመንግስት ስልጣን እንዲሳተፉ በብልፅግና የተሰጠው እድልን አድንቆ በሀገሪቱ የመንግስት ታሪክ አዲስ አሰራር በመሆኑ ከገዢው ፓርቲ ጋር አብሮ ለመስራት ያለውን ዝግጁነት አረጋግጧል።

ነገር ይህ አዲስ አሰራር ተግባራዊ ሲደረግ ተፎካካሪ ፓርቲዎች በሂደቱ በግልፅ እንዲሳተፉ ማድረግ በሀገር ደረጃ ለታሰበው አዲስ የፖለቲካ ባህል ውጤታማነት አስፈላጊ ነው ብሏል።

@tikvahethiopia
#ነእፓ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን መጋቢት 18 እንደሚያካሂድ አሳውቋል።

የጉባኤው ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጿል።

1ኛ መደበኛ ጉባኤ ፓርቲውን ወደአዲስ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነእፓ አሳውቋል።

የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያከናውኑ እና አስፈላጊ የሆኑ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያስገቡ ማሳሰቢያ ከሰጣቸው 13 ሀገራዊ እና 13 ክልላዊ ፓርቲዎች መካከል አንዱ ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ አንዱ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነእፓ ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን መጋቢት 18 እንደሚያካሂድ አሳውቋል። የጉባኤው ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑንም ገልጿል። 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ፓርቲውን ወደአዲስ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነእፓ አሳውቋል። የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያከናውኑ እና አስፈላጊ የሆኑ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያስገቡ ማሳሰቢያ ከሰጣቸው…
#ነእፓ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ አንደኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ መጋቢት 18 /2014 በአዲስ አበባ ማካሄድ ጀምሯል።

ይህ የፓርቲው አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ፓርቲውን ወደአዲስ ምዕራፍ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ጉባኤው በተለያዩ የፓርቲው ውስጣዊ ጉዳዮችና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል።

በአሁን ሰዓት እየተካሄደ በሚገኘው የማስጀመሪያ ስነስርዓት የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣አባላት፣ የሌሎች የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየታደሙ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በሰሜን ኢትዮጵያ ሌላ ዙር ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ከፍተኛ ስጋት አድሮብኛል " - ነእፓ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ሌላ ዙር ጦርነት እንይቀሰቀስ ከፍተኛ ስጋት ያደረበት መሆኑን ገለፀ። ነእፓ ያንዣበበው የጦርነት አደጋ ተቀርፎ በሰሜኑ የሀራችን ክፍል አስተማማኝ እና ዘላቂ ሰላም ይረጋጥ ዘንድ ለሚለከታቸው አካላት ሁሉ ጥሪውን አስተላልፏል። ፓርቲው የተፈጠረውን የጦርነት…
ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ፦

(ለሚመለከተው ሁሉ የቀረበ ሀሳብ)

ነእፓ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ክልሎች አንዱ ትግራይ መሆኑና በጦርነቱ የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት እንደደረሰበት ገልጿል። በክልሉ እና በህዝቡ ላይ የደረሰው ከፍተኛ ጉዳት ዘላቂ ሰላም በመፍጠር በአፋጣኝ ሊቀየር ይገባል ብሏል። በመሆኑም ትግራይን በማስተዳደር ላይ ያሉ ኃይሎች በትግራይ ህዝብ ላይ የደረሰውን ከፍተኛ ጉዳት ለመቀነስ እና በክልሉ ላይ ያንዣበበውን የጦርነት ስጋት ለመግታት ዳግም ወደ ጦርነት ከሚያመሩ ወታደራዊ ፣ ፖለቲካዊ እና የሚዲያ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠቡ፣ በአንጻሩ ለሰላም መረጋገጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።

➢ በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ ከልል የተፈጠረውን ከፍተኛ የምግብ፣ የመድሀኒት እና ሌሎች ቁሳቁሶች ችግር ለመቅረፍ የፌዴራል መንግስት አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ ወደ ክልሉ አንዲገባ መፍቀዱን አስታውሷል፤ በዚሁ መሰረት የፌዴራል መንግስቱ ምግብ፣ መድሀኒት እና ሌሎች ሰብአዊ ድጋፎች በበቂ ሁኔታ ወደ ክልሉ እንዲደርስ አስፈላጊውን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።

➢ የፌዴራሉ መንግስት ፤ እንዲሁም የአማራ እና የአፋር ክልላዊ መስተዳድሮች እና የትግራይ ኃይሎች የተፈጠረውን ዳግም ወደ ጦርነት የመመለስ አደጋ ለማስወገድ እና ችግሩን በሰላማዊ መንድ ለመፍታት የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ጠይቋል። የፌደራል መንግስት ጦርነቱ በሰላማዊ መንገድ እና በድርድር አንዲያልቅ የድርድር ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ በአስቸኳይ ወደ ተግባራዊ እርምጃ አንዲገባም ጠይቋል።

➢ የሀገር ሸማግሌዎች ፤ የፖለቲካ ፓቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ በውጭ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፤ ባለሃብቶች፣ የተፈጠረውን የግጭት ስጋት ለማስወድ የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ፤ የሚዲያ ተቋማት እና አክቲቪሰቶች ካለፈው ትምህት በመውሰድ ግጭት ቀስቃሸ የሆኑ መልእከቶችን ከማሰራጨት በመቆጠብ እና ሰላምን በማቀቀን ሀገራችን ዳግም ወደ ጦርነት እንዳትግባ ሙያዊ ግዴታቸውን ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ እንዲወጡ ጠይቋል።

➢ በማንኛውም ሁኔታ ለሚቀሰቀስ የእርስ በእርስ ጦርነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ትልቅ ዋጋ የሚከፍሉት ዜጎች ናቸው - ከአንድ አመት በላይ በሰሜኑ የሀገራችን ከፍል በተካሄደው ጦርነት ትልቅ ዋጋ የከፈሉትም መላው የሀገራችን ህዝቦች ናቸው። በመሆኑም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ያንዣበበው የጦርነት ስጋት ተወግዶ ሰላም እንዲረገጥ መላው የሀገራችን ህዝቦች ጦርነትን በማውገዝ እና የሰላምን አርማ ከፍ አድርጎ በማውለብለብ ሰላም እንዲሰፍን የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።

#ነእፓ #ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#ነእፓ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ፤ ዛሬ በላከልን መግለጫ መንግስት ከጁመዓ ሰላት በኃላ በምዕመናን ላይ እርምጃ መውሰዱንና ይህንንም በፅኑ እንደሚያወግዝ ገልጿል።

ፓርቲው ፤ " ባለፉት ጥቂት ወራት በ ' ሸገር ከተማ ' እየተካሄደ ያለውን ' ህገወጥ ' መስጂዶችን የማፍረስ እርምጃ በሰላማዊ መንገድ በመቃወም በአዲስ አበባ በተለይ በአንዋር መስጂድ ከጁምአ ሰላት በኃላ ድምጻቸውን ባሰሙ ሙስሊሞች ላይ በተወሰደው እርምጃ የሰው ህይወት አልፏል ፣ በርካታ ምዕመናን ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል " ያለ ሲሆን " የተወሰደው የእብሪት እርምጃ ነው ፤ ይሄንንም በፅኑ እናወግዛለን " ሲል አሳውቋል።

መንግስት ከሀይማኖት ተቋማት ላይ እጁን እንዲያነሳ ፣ የሀይማኖት እና የመንግስትን ህገመንግስታዊ ልዩነት እንዲያከብር ፓርቲው በላከልን መግለጫው ጠይቋል። 

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ፦

- መንግስት የጀመረው መስጊዶችን የማፍረስ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ተባባሶ ወደ ከፋ ሀገራዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ችግር ከመቀየሩ አስቀድሞ እርምጃውን በአስቸኳይ እንዲያቆም፣ እስከ አሁን ለደረሱ የህይወት፣ የንብረት እና የስነ ልቦና ጉዳቶች ህዝብን በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ፤

- ዜጎች የመንግስትን የተሳሳቱና ብልሹ አሰራሮችን የመቃወም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን እንዲያከብር፣

- መንግስት በሀይማኖት ተቋማት ላይ በሚወስደው ኢ -ህገ መንግስታዊና ኢ-ዴሞክራሲያዊ ጣልቃ ገብነት ሀገራችን ወዳልተፈለገ የፖለቲካ ቀውስ መግባቷን ከቅርብ የሀገራችን ታሪክ ትምህርት በመውስድ ራሱን እና ሀገራችንን ከቀውስ እንዲታደግ፣

- መንግስት ራሱ ከፈጠረው ተምኔታዊ የብልጽግና እና ልዕልና ትርክት በተቃራኒ ሀገራችን በተጨባጭ ያላችበትን ጥልቅ እና አሳሳቢ የደህንነት፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ቀውሶችን ከግምት ያስገባ፣ ዜጎች ያሉበትን የከፋ ድህነት እና ስራ አጥነት፣ አድሏዊ እና ብልሹ አሰራር፣ ሙስና፣ በሰላም ወጥቶ የመግባት ስጋት፣ . . . ችግሮችን ያገናዘበ ፈጣን እና ስር ነቀል የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ ሀገሪቱን ከከፋ የፖለቲካ ቀውስ እንዲታደግ አሳስቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ነእፓ

የነእፓ ሊቀመንበር ለጠ/ሚኒስትሩ ደብዳቤ ፃፉ።

የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ሊቀመንበር ዶ/ር አብዱልቃድር አደም የአዲሱን ዓመት 2016 ተንተርሶ ለጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ግልፅ ደብዳቤ ፃፉ።

በዚህ ደብዳቤያቸው እየተጠናቀቀ ባለው 2015 ዓመት እንዲሁም ባለፉት ዓመታት በሀገራችን ስለነበሩ የሰላም እና ጸጥታ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ችግሮች በወፍ በረር በመዳሰስ ችግሮቹ ወደ አዲሱ አመት እንዳይሸጋገሩ  አሉኝ ያሉትን የመፍትሄ ሀሳቦች እና ጥያቄዎች ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅፈውላቸዋል።

ከደብዳቤያቸው የወሰድነው ፦

" ለአብዛኛው የሀገራችን ህዝብ ኑሮ እጅግ ከብዷል።

ሰፊው ህዝባችን ጦም እያደረ የፖለቲካ ስልጣን የያዙ እና በነሱ ጉያ ስር የተወሸቁ ጥቂቶች እጅግ የተንደላቀቀ ህይወት የሚኖሩበት አስጊ ሁኔታ ተፈጥሯል።

የሀገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ፓርቲዎ እና መንግስትዎ እናሳካለን ብለው ለህዝብ ከሚነግሩት እውነተኛ የብልጽግና ጉዞ እየተለየ መጥቷል። 

ለም መሬት እና ለሌሎች የሚተርፍ ወንዞች ያላት ሀገራችን ለበርካታ ልጆቿ የቀን ጉርስ ማቅረብ ተስኗታል።

በቅዱሳን መጽሀፍት የሰላም እና የፍትህ ምድር በመባል የምትታወቀው ሀገር ሰላም እና ፍትህ ርቋታል።

ለዓለም ተምሳሌት የሚሆን የአብሮነት እና የመተሳሰብ ባህል የነበራቸው ባለ ብዙ ቀለም ህዝቦች በመካከላቸው መተማመን ቀንሶ እርስ በርስ እየተጠራጠሩ መኖር ጀምረዋል።

በዜጎች ፊት ደስታ እና ተስፋ እየራቀ መጥቷል፣ ስጋት በኢትዮጵያ ሰማይ ነግሷል። ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮቻችን ልንሸፋፍናቸው ከማንችልበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። 

እንደ ሀገር የገጠሙንን ችግሮች በቅንነት፣ ከፖለቲካ ርእዮት እና ወገንተኝነት ወጥተን በሀገር ልጅነት ስሜት ተወያይተን እና ተጋግዘን ለመፍታት ጊዜ እና ታሪክ አንድ ተጨማሪ እድል ሰጥቶናል።

2015 ተገባዶ አዲስ አመት ለመቀበል ቀናት በቀሩበት ወቅት፣ ሁላችንም ያለፉ ስኬቶቻችንን እና ስህተቶቻችንን ቆም ብለን ልናስተውል ይገባል።

2015ን አገባደን አዲስ ዘመን ለመቀበል እየተሰናዳን ባለንበት ወቅት፣ በተለይም ባለፉት አምስት አመታት በሀገራችን የተከሰቱ እጅግ አውዳሚ ጦርነቶች እና ግጭቶች ቆመው ሰላም የሰፈነባት ሀገር ለመፍጠር ሁላችንም ቃል ልንገባ ይገባል። ይህን አለማድረግ ሁላችንንም በታሪክ ተጠያቂ ያደርገናል። 

ሀገራችን ካለችበት ውስብስብ ቀውስ እንድትላቀቅ፣ ህዝባችንም ሰቅፎ ከያዘው ዘርፈ ብዙ ችግር እንዲላቀቅ ማድረግ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ቢሆንም፣ #የመንግስት ድርሻ ከፍተኛ ነው።

በየደረጃው ያሉ የመንግስት አካላት ሀገራችን ካለችበት ችግር እንድትላቀቅ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት ያለባቸው ሲሆን፣ የመንግስት የአስፈጻሚ አካል መሪ በመሆን የእርስዎ የግል ኃላፊነት እና ተነሳሽነት እጅግ ከፍተኛ እንደሆነ በታላቅ ትህትና እና ወንድማዊ ስሜት ላስታውሶት እወዳለሁ። "

(ሙሉ የደብዳቤያቸው ቃል ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ነእፓ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ለኢፌዴሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ደብዳቤ ፃፈ።

ፓርቲው በዚህ ደብዳቤው ፤ " የፓርቲ አባል ያልሆኑ የመንግሥት ሰራተኞች በብልፅግና ፓርቲ ስልጠና እንዲሳተፉ የሚደረግበት አሰራር እንዲቆም " ሲል ጠይቋል።

ነእፓ#የመንግስት እና #የፓርቲ መደበላለቅ በለውጡ ማግስት መጠነኛ መሻሻል አሳይቶ እንደነበር አስታውሷል።

ነገር ግን በተለይ ከ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት ጀምሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቷል ብሏል።

ከቅርብ ወራት ጀምሮ ገዢው ፓርቲ እያካሄደ ባለው የአባላት ስልጠና፣ የፓርቲው አባል ያልሆኑ የፌዴራል እና የክልል የመንግስት ሰራተኞች (Public servants) የገዢውን ፓርቲ ድርጅታዊ ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑ ለዚህ አንድ ማሳያ ነው ሲል አስረድቷል።

ፓርቲው አለኝ ባለው መረጃ የገዢው ፓርቲ አባላት ያልሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ስልጠናውን እንዲወስዱ በተለያየ መንገድ ጫና እየተደረገባቸው መሆኑን ገልጿል።

ይባስ ብሎ በየአካባቢው እየተካሄዱ ያሉ ስልጠናዎች ፦
- አበል፣
- ትራንስፖርት፣
- ሆቴል እና ሌሎች የስልጠና ወጪዎች የሚሸፈኑት #በመንግስት_በጀት መሆኑ ችግሩን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል ብሏል።

በመሆኑም የፓርቲ አባል ያልሆኑ የፌዴራል እና የክልል የመንግስት ሰራተኞች የገዢውን ፓርቲ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ ህገ መንግስቱን እና የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነ ስርአት አዋጃ ቁጥር 1162/2011 የሚቃረን በመሆኑ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ድርጊቱ ይቆም ዘንድ የሚጠበቅበትን እንዲያደርግ ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል።

በቀጣይ ተመሳሳይ የህግ ጥሰቶች እንዳይፈጠሩ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወሰድም አሳስቧል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት፤ ገዢው ፓርቲ የስልጠናና ሌሎች ድርጅታዊ እንቅስቃሴውን በመንግስት ሀብት የሚሸፍንበት አሰራር ህግ እና ስርአትን ያልተከተለ ከመሆኑም ባሻገር የፖለቲካ ሜዳውን የሚያዛንፍ በመሆኑ፣ ድርጊቱ ይታረም ዘንድ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።

በተለይም ፦
- የምርጫ ቦርድ፣
- የገንዘብ ሚንስቴር
- የክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ቢሮዎች፣
- በየደረጃው ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምከር ቤቶች አዋጁን በማስከበር ገዢው ፓርቲ ድርጅታዊ መዋቅሩን ከመንግስት መዋቅር ለይቶ እንዲሰራ ኋላፈነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።

(ፓርቲው የላከው መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ነእፓ

በሀገሪቱ ያሉ የእርስ በርስ ግጭቶችን ለማስቆም “ ኢትዮጵያ በልጆቿ ትታረቅ ! ” በሚል የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ የእርቅ እና የሰላም ሀሳብ ይዞ መቅረቡን አሳውቋል።

ፓርቲው በላከልን መግለጫ ፤ ሀገራችን በታሪኳ በርካታ በእርስ በእርስ ግጭቶችን ማስተናጓን ገልጿን።

ለ2 አመታት በትግራይ፣ በአማራ እና አፋር ክልሎች የተካሄደው ጦርነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን ህይወት መቅጠፉን አመልክቷል።

አሁንም በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች የቀጠለው የወንድማማቾች ጦርነት የወገኖቻችንን ህይወት እየቀጠፈ እንደሚገኝ ገልጿል።

በየአካባቢው በተለኮሱ ጦርነቶች ሳቢያ ፦

- በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ውድ ህይወታቸውን እንዳጡ፣ አካላቸው እንደጎደለ፤

- እድሜ ልካቸውን ያፈሩት ንብረት እና የሀገራችን ኢትዮጵያ አንጡራ ሀብትም እንደወደመና እየወደመም እንደሚገኝ ገልጿል።

በእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ህጻናት ያለ አሳዳጊ፣ አረጋውያን ያለ ጧሪ ፣ አያሌ ኢትዮጵያውያን ለርሀብ፣ ለእንግልት፣ ለስደት እና ለሞት መዳረጋቸውን ገልጿል።

በየአካባቢው የተከሰቱ ግጭቶች ማህበራዊ ግንኙነታች እንዲበጣጠስ፣ በዜጎች መካከል ጥርጣሬ እንዲነግስ፣ ማህበራዊ ትስስራችን እንዲላላ፣ ጥላቻ፣ እልህ፣ በቀል እንዲስፋፋ፣ ስጋት እና ጭንቀት በዜጎች ልቦና እንዲሰፍን ማድረጋቸውንም አመልክቷል።

ነእፓ፤ ጦርነት መቼም ቢሆን የፖለቲካ ልዩነቶችን ለመፍታት የተሻለ አማራጭ አይሆንም ፤ የእርስ በእርስ ጦርነት አሸናፊና ተሸናፊ የሌለው የመጨረሻ ውጤቱ ሞት፣ ስደት፣ ስቃይ፣ ሀዘን ፣ የሀገር ድቀትና መፍረስ ነው ብሏል።

ላለፉት ዓመታት ሰላም እንዲሰፍን በተለያዩ መንገዶች ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን የሚገልጸው ነእፓ ሀገራችንን ለክፉ ችግር፣ ህዝባችንን ማባሪያ ለሌለው ሰቆቃ የዳረጉ ጦርነቶች እንዲቆሙ “ #ኢትዮጵያ_በልጆቿ_ትታረቅ ” በሚል ስያሜ አዲስ የእርቅ እና የሰላም ሀሳብ መንደፉን ይፋ አድርጓል።

ዋናው ዓላማ በመንግስት እና ከመንግስት ጋር ነፍጥ አንግበው በሚፋለሙ ማናቸውም ኃይሎች መካከል በሀገር ሽማግሌዎች፣ በኃይማኖት አባቶች እና በሌሎች ታዋቂ ስብእናዎች አማካኝነት እርቅ ማውረድ እንደሆነ ገልጿል።

በቀጣይ ሂደቱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎች ይሰጣሉ ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 “ ... ያለፉትን ዘመናት እኮ #እንደ_ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው ” - ጎጎት ፓርቲ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' #የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ ? ' በሚል በህጋዊ መንገድ ተመዝገበው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እያቀረበ ያለውን ወቅታዊ ሀገራዊ ጥያቄዎች በመቀጠል ጎጎት ፓርቲን አነጋግሯል። የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ጀሚል ሳኒ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ…
🇪🇹 የፓለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

“ መንግስት እንደ መንግስት ሥራውን እየሰራ አይደለም ” ሲል ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ተቸ።

የፓርቲው ሊቀመንበር ፤ ዶክተር አብዱልቃድር አደም ስለወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮች የፓርቲያቸውን ምልከታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርተዋል።

ሊቀመንበሩ በነበራቸው ቆይታ  ፦
- የዝቅተኛ ደመወዝ ወለል ጉዳይ
- የኑሮ ውድነት
- የሰላም እና ጸጥታ ጉዳይ
- ከሰሞኑን እየወጡ ስላሉ አዳዲስ አዋጆች
- ስለ ፖለቲካ ህዳሩ
- የመልካም አስተዳደር እጦት
- የኢኮኖሚ ጉዳይ ... ሌሎችም ተነስተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም " መፍትሄው ምንድነው ? " ሲል ላቀረበው ጥያቄ ፓርቲው ምላሽ ሰጥቷል።

ምጣኔ ሀብትን በተመለከተ ዶክተር አብዱልቃድር አደም ምን አሉ ?

“ የMacro Economy መናጋት አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ የከፋ ሁኔታ ላይ ደርሷል።

የኢትዮጵያ የልማት ስትራቴጂ ሁኔታዎችን ያላገናዘበ ነው።

ይልቁንም ትኩረት የሚሹት ፦
➡️ ኢንፍራስትራክቸር፣
➡️ መብራት፣
➡️ ጤና፣
➡️ ውሃ መሠረታዊ ችግሮች ናቸው፤ ዜጎች በእነዚህ ነገሮች ተቸግረዋል።

ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ በሚል የሚሰራቸው ፕሮጀክቶች መቃኘት አለባቸው።

ከፍተኛ የሆነ የንግድ ጉድለት አለ። የምንሸጠው እና የምንገዛው ልዩነቱ የሰፋ ነው። የበጀት Deficit አለ።

መንግስት የሚሰበስበውና የሚያወጣውን ገንዘብ ለዚያውም አስፈላጊነታቸው አጠራጣሪ ፕሮጀክቶች ላይ ገንዘቡ ወጪ ይሆናል።

ይሄ ኢኮኖሚው እንዲናጋ አድርጓል ብለን እናምናለን።”

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-24

#ነእፓ #ኢትዮጵያ #የፖለቲካፓርቲዎችምንይላሉ?