TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UNSC : ትላንት ለሊት የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።

በዚህ ስብሰባድ በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ጦርነት እየተባባሰ መሄዱ በጽኑ እንዳሳሰበውና በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ አቀረበ።

ከስብሰባው በኋላ በ15ቱም አባላት #ተቀባይነት_አግኝቶ በወጣ መግለጫ ሁሉም በግጭቱ ተሳታፊ የሆኑ ወገኖች ጦርነቱን በማቆም "ዘላቂ ሰላም የሚያመጣ የተኩስ አቁም ለማድረግ" ውይይት እንዲጀምሩ ጥሪ አቀርቧል።

መግለጫው ለተፈጠረው ቀውስ መፍትሔ ለማግኘት እንዲቻል እና ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ ውይይት ለማካሄድ አመቺ ሁኔታ እንዲፈጠር ጠይቋል።

የምክር ቤቱ አባላት ችግሩን ለመፍታት #የአፍሪካ_ሕብረትን በመሰሉ አካባቢያዊ ድርጅቶች በኩል የሚደረገውን ጥረት እንደሚደግፉና የሕብረቱ ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ተኩስ እንዲቆምና ጦርነቱ ሰለማዊ መቋጫ እንዲያገኝ የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚደግፍ ገልጿል።

በተጨማሪ ሁሉም ወገኖች "ከአደገኛ ጥላቻ ከሚያስፋፉ፣ ግጭትንና መከፋፈልን ከሚያነሳሱ ንግግሮች" እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AU2022Summit ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በ35ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር አፍሪካ በተመድ ፀጥታ ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት የሚሠራበት ጊዜ መሆኑን ገለፁ። ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፥ " አሁን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሚሻሻልበት እና አፍሪካም በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት የሚሠራበት ጊዜ ነው " ሲሉ ተናግረዋል። ከዚህ…
#UNGA  

አሜሪካ የተመድ የፀጥታ ም/ቤት ሁሉን አካታች እንዲሆን ለማድረግ #ሪፎርም እንዲደረግበት ጥሪ አቀረበች።

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በኒውዮርክ እየተካሄደ ባለው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 77ኛ ጠቅላላ ጉባዔ ባደረጉት ንግግር ፦
- #የአፍሪካ
- ላቲን አሜሪካ
- ካሪቢያን ሀገራት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

የፀጥታው ምክር ቤት ለዓለም አቀፍ ተግዳሮቶች ምላሽ ለመስጠት የተሻለ ብቃት እንዲኖረውና ሁሉንም አካታች እንዲሆን ለማድረግ ሪፎርም እንዲደረግበትም ባይደን ጥሪ አቅርበዋል።

ምክር ቤቱ አሁን ላይ 5 ቋሚ እና 10 ተለዋዋጭ በድምሩ 15 መቀመጫዎቸ ያሉት ሲሆን ይህ የመቀመጫ ቁጥር እንዲጨምር ጠይቀዋል።

በአፍሪካ፣ ላቲን አሜሪካና ካሪቢያን ውስጥ የሚገኙ ሀገራት በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲያገኙ የጠየቁት ባይደን አሜሪካ ይህንን አቋም ለረጅም ጊዜ ስትደግፍ ቆይታለች ብለዋል።

በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ያላቸው ሀገራት በእነሱ ላይ ወይም በአጋሮቻቸው ላይ የሚተላለፉ ውሳኔዎችን የመሻር መብት አላቸው።

ባይደን አሜሪካን ጨምሮ በፀጥታው ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ ያላቸው ሀገራት ምክር ቤቱ ተዓማኒነት ያለውና ውጤታማ ሆኖ እንዲቀጥል ከአቅም በላይ ከሆኑ ያልተለመዱ ሁኔታዎች ውጪ ድምጽን በድምጽ መሻር መብታቸውን ከመጠቀም እንዲቆጠቡም አሳስበዋል።

አፍሪካ በፀጥታው ም/ ቤት ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራት ለማስቻል የተለያዩ ዘመቻዎች ሲካሄዱ እንደነበር ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከዚህ ቀደም ይህንን የአፍሪካ ሀገራት በተመድ የጸጥታው ጥበቃ ም/ቤት ቋሚ መቀመጫ ማግኘት አለባት የሚለውን ሃሳብ መቀላቀላቸውን ይፋ ማድረጋቸው አይዘነጋም።

#አልዓይን

@tikvahethiopia
#SPORT : ኢትዮጵያ በጊኒ ተሸነፈች።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድናችን #የአፍሪካ_ዋንጫ ማጣርያ የምድብ ሶስተኛ ጨዋታውን ከጊኒ አቻው ጋር አድርጓል።

ጨዋታውን ያደረገው በሞሮኮ " ሞሀመድ አምስተኛ " ስታዲየም ነው።

በዚህም ጨዋታ ብሔራዊ ቡድናችን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።

ውጤቱን ተከትሎ አሁን ያለው የምድቡ ደረጃ ፦

1ኛ. ግብፅ 6 ነጥብ
2ኛ. ጊኒ 6 ነጥብ
3ኛ. ማለዊ 3 ነጥብ
4ኛ. ኢትዮጵያ 3 ነጥብ

ብሔራዊ ቡድናችን ከቀናት በኋላ የምድብ አራተኛ ጨዋታቸውን #ከጊኒ ጋር ያደርጋል።

More : @tikvahethsport    

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት አንደኛ ዓመት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል። በዚህም መግለጫ የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ እንዲከበር ቁርጠኛ መሆኑን አሳውቋል። በአከራካሪ ቦታዎች ተፈናቃዮች እንዲመለሱና በህገመንግቱ መሰረት ህዝበ ውሳኔ እንዲደረግ አቋም ይዞ ተግባር ላይ እንዳለ አመልክቷል። የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ፤ መንግሥት በጦርነቱ የመጨረሻ…
" ለትግራይ ህዝብ ደህንነት የሚያሰጋ ነገር ከሌለ #ከመከላከያ_ሃይል ውጪ ያሉት የታጠቁ ሃይሎች ከትግራይ መሬት ከወጡ ትጥቅ ተሸክመን የምንኖርበት ምክንያት የለም  " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አንደኛ አመት በማስመልከት ከ " ትግራይ ቴሌቪዥን " ጋር ሰፊ ቃለመጠይቅ አድረገዋል።

በዚህም ቃለመጠይቃቸው ፥ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የትግራይ ግዛትን የተቆጣጠሩት ኃይሎችን ማስወጣትና ፣ በትግራይ ግዛት በአማራ ሃይሎች የተመሰረቱት አስተዳደሮች የማፍረስ ጉዳይ የፌደራል መንግስት ግዴታዎች ናቸው ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ " የፕሪቶሪያ ውል የቶክስ ድምፅ የማቆም ስምምነት ነው " ያሉ ሲሆን  ከዚህ አኳያ ስኬታማ ውልና ስምምነት ነው ብለውታል።

በቃለመጠይቁ ላይ  ' ስለመሬት ይገባኛል ' ጉዳይም አንስተው የተናገሩት አቶ ጌታቸው " በአማራ ክልል በኩል ሃቅ የሚመስል የመሬት ይገባኛል ጥያቄ እንዳለ አስመስሎ የሚቀርብ አለ። በኔ አረዳድ እንደዛ አይነት ጥያቄ የለም ነው የምለው " ሲሉ ተደምጠዋል።

በኢትዮጵያ #የፌዴራል_መንግስት_ተደራዳሪዎች በኩል የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አጨቃቂዎቹን የምእራብ ፣ ሰሜን ምእራብን ደቡብ ትግራይ ማስተዳደር የለበትም የሚሉ እንደነበሩ የክልሉ አስተዳዳሪ አንስተዋል።

አቶ ጌታቸው " ለትግራይ ህዝብ ደህንነት የሚያሰጋ ነገር ከሌለ #ከመከላከያ_ሃይል ውጪ ያሉት የታጠቁ ሃይሎች ከትግራይ መሬት ከወጡ ትጥቅ ተሸክመን የምንኖርበት ምክንያት የለም " ያሉ ሲሆን " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የፈረምነው የትግራይ መሬት ቆርሰን ለመስጠት ሳይሆን ፤ በህገ-መንግስት መሰረት ይፈታ ስለተባለ ነው " ብለዋል። 

ከተፈናቃዮች መመለስ ጋር በተያያዘም የትግራይ ምእራባዊና ደቡባዊ አከባቢዎች እንዲሁም ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የመመለስ ጉዳይ ቀደም ብሎ መፈፀም የነበረበት ተግባር እንደነበር ገልጸዋል።

" ይሁን እንጂ የፌደራል መንግስት ተፈናቃዮች እስከ ሰኔ 21/2015 ዓ.ም ወደ ቄያቸው ይመለሳሉ ብሎ የገባውን ቃል አልፈፀመም " ብለዋል።

የሰላም ስምምነት ትግበራው እንዲፋጠን ከአማራ ክልል አመራሮች ለመስራት ጥረት መደረጉን ያነሱት አቶ ጌታቸው " በፕሪቶሪያ ውል ላይ መደራደርና መገምገም ስለጀመሩ ዉይይቱ ተቋረጠ " ሲሉ ገልጸዋል።

ከዚህ ባለፈ በቃለመጠይቁ የሪፈረንደም ጉዳይም ተነስቶ ነበር።

አቶ ጌታቸው ሪፈረንደም ለማካሄድ የትግራይ ክልል ተወካዮች ምክር ቤት የግድ መቋቋም እንዳለበት ተናግረዋል።

" ከዚህ ውጭ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሪፈረንደም የማካሄድ ህገ-መንግስታዊ ስልጣን የለውም " ሲሉ አሳውቀዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ " የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሪቶሪያ ውል እንዳይፈፀም እግር እየጎተተ ነው የሚለው ንግግር የተጋነነ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ፤ #የአፍሪካ_ህብረት ግጭት ዳግም እንዳይነሳ በማረጋገጥና ውሉ በተማሏ መንገድ እንዲፈፀም ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት አስገንዝበው " ሁሉም ልዩነቶች ሰላም ብቻ ነው መፈታት ያለባቸው ፣ ከጥይት ቶክስ #ለውይይት ቦታ መስጠት አለብን። ትግራይ የአውዳሚ ጦርነት መነሃሪያ እንድትሆን አንፈቅድም። " ብለዋል። 

አቶ ጌታቸው የጊዜያዊ አስተዳደራቸው ዋና ትኩረት የትግራይ ህዝብ #ደህንነት_ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸው ፤ " የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ለማደናቀፍ የሚንቀሳቀስ ማኛውም አካል ወይም ሃይል ተቀባይነት የለውም እንታገለዋለን። " ብለዋል።

በትላንትናው ዕለት የፌዴራል መንግሥት ባወጣው መግለጫ ፦

-  የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በአንዳንድ ነገሮች ወደኋላ እየቀረና የሰላም ስምምነቱን በተሟላ ሁኔታ ሳይፈፅም እያነከሰ ነው ሲል መተቸቱ ፤

- አከራካሪ የሚባሉ አካባቢዎችን በተመለከተ አቋም ወስዶ እንደሰራ እንደሆነ ፤ ክረምት ደርሶ የእርሻ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ተፈናቃዮች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ፣ የአካባቢ ነዋሪዎች በመረጧቸው አካላት እንዲተዳደሩ፣ በመጨረሻም ደረጃ በደረጃ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ አቅጣጫ መቀመጡን እና ይሄንንም ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ ማስታወቁ ፤

- የሰላም ስምምነቱ #በተሟላ_ሁኔታ_እንዲፈፀም ማድረግ ያለበትን ሁሉ ቢደረግም በዚያኛው ወገን እግር የመጎተት አዝማሚያ እንደሚታይ መግለፁ አይዘነጋም።
  
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
EU_Cotonou and Samoa Agreement_merged.pdf
#SamoaAgreement

ከወር በፊት ሀገራችን #ኢትዮጵያን ጨምሮ አጠቃላይ 79 የአፍሪካ እና የካረቢያንና ፓስፊክ ሀገራት / 48 ከአፍሪካ፣ 16 ከካረቢያን፣ 15 ከፓስፊክ / ሳሞአ ላይ አንድ ስምምነት ተፈራርመዋል።

የተፈረመው ስምምነት " #የአፍሪካ#የካረቢያን እና #የፓስፊክ ሀገራት ከአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ጋር የሚያደርጉት የንግድ እና ኢኮኖሚ ትብብር " የሚል ነው።

ስምምነቱ 22 ዓመታትን የዘለቀው " የኮቶኑ ስምምነት " ቀጣይ እንደሆነ ተነግሯል።

ይህ ስምምነት ግን ብዙ ጥያቄ ተነስቶበታል። 

በቅድሚያ ስምምነቱ ላይ ጥያቄ እና ከፍተኛ ጥርጣሬ የተነሳው #ካረቢያን አካባቢ ነው። 

ስምምነቱ ፤ በካሪቢያን አካባቢ ከባህል እና ከእሴቶች ጋር የማይጣጣሙ ህጎችን በካሪቢያን ህዝብ ላይ ይጭናል በሚል ከፍተኛ ስጋት እንዳላቸው በቅድሚያ የገለፁት ፦
- በትሪንዳድ እና ቶቤጎ የሚገኘው የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን 
- የጃማይካ ጥምረት ለጤናማ ማህበረሰብ (JCHS) ናቸው።

በትሪኒዳድ የሚኖሩ አንድ #የሃይማኖት_አባት በሀገር ውስጥ በሚገኝ መገናኛ ብዙሃን ላይ ቃለ ምልልስ ካደረጉ በኃላ ነው ስምምነቱ ላይ #ህዝባዊ_ትችት የመጣው።

የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን አባት የስምምነት ሰነዱ ' የአውሮፓ ህብረት ' " የእኛ ያልሆነን ርዕዮተ ዓለም " በአስገዳጅነት እንዲጭን የሚያደርግ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የጃማይካ ጥምረት ለጤናማ ማህበረሰብ (JCHS) ደግሞ " ተቀባይነት የሌለውን / ውድቅ የተደረገውን አጠቃላይ የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ትምህርተ ሥርዓተ ወደ ጃማይካ የመማሪያ ክፍሎች እንደሚመልስ እና የጃማይካውያንን መሠረታዊ መብቶች እና ነጻነቶች ይጎዳል ፤ ከሀገሪቱ ባህልም ያፈነገጠ ነው " በሚል ጠንካራ ተቃውሞ አስምቷል።

እንዚህ አካላት፤ " በማዕቀብ ሰበብ እና ውል በማሰር " ህዝብ የማይቀበለውን #ከባህል_ያፈነገጠ ተግባር ያለማምዳል ፤ ይጭናል በሚለው ነው የተቃወሙት።

በ ' ሴንት ቪንሰንት እና ግሬናዲንስ ' ከዚህ ከባለ 400 ገፆች የሳሞአ ስምምነት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ስጋት ተሰቅስቅሶ ነበር። እሱም ስምምነቱ ፦
- ሀገሪቱ በፅንስ ማቋረጥ ፣
- በተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ 
- በLGBTQ መብቶች ላይ ሀገሪቱ ህጎቿን ለማሻሻል #ትገደዳለች የሚል ነው።

ይህ ጉዳይ እና ስጋት በካረቢያን አካባቢ ከተነሳ በኃላ ጉዳዩ በማህበራዊ ሚዲያ ሰፊ መናጋገሪያ ሆኖ ወደ አንዳንድ #የአፍሪካ_ሀገራት ተሰራጭቷል።

በተለይ ደግሞ በናይጄሪያ፣ በናሚቢያ፣  በታንዛኒያ ... የመሳሰሉ ሀገራት ውስጥ ያሉ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በስምምነቱ ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ሲገልጹ ነበር።

ምንም እንኳን በርካታ ሀገራት ስምምነቱን #በሰዓቱ ቢፈርሙም አንዳንድ ሀገራት ግን ሰነዱ ላይ ዘግይተው ነው የፈረሙት።

ለአብነት ሰነዱን ዘግይተው ከፈረሙት ውስጥ በሰነዱ ላይ በቅድሚያ ከዜጎቿ ጥያቄ የተነሳባት #ጃማይካ አንዷ እና ዋነኛዋ ስትሆን እነ ፦
* ቦትስዋና፣
* ናሚቢያ፣
* ሰኔጋል፣
* ታንዛኒያ፣
* ሶማሊያ፣
* ሩዋንዳ ዘግይተው ከፈረሙት ውስጥ ይጠቀሳሉ።

➡️ ጥያቄ እና ስጋት በተነሳባቸው ሀገራት ምን ምላሽ ተሰጠ ?

➡️ ኢትዮጵያ ውስጥ ስለ ጉዳዩ ምን ተባለ ?

➡️ ስምምነቱን በተመለከተ ፤ " ስለ ኢትዮጵያ ዝም አንልም ትውልድን ከግብረሰዶም እንታደግ ማህበር " ምን አለ ?

➡️ በኢትዮጵያ የግብረ ሰዶማውያን መስፋፋት ምን ያህል አስከፊና አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ አጠቃላይ ያለውን ሁኔታ ዳሷል ያንብቡ ፡ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-10

@tikvahethiopia