TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
“አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #የመኪና_አደጋ አልደረሰባቸውም” አቶ አሰማኸኝ አስረስ
.
.
.
በማህበራዊ ሚዲያ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው የመኪና አደጋ እንደደረሰባቸው ተደርጎ እየተናፈሰ ያለው ወሬ ሃሰት መሆኑን የክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ #አሰማኸኝ_አስረስ ተናገሩ።

በምዕራብ ጎንደር ገንዳ ውሃ ከተማ ሰሞኑን በተከሰተው ግጭት ዙሪያ ትናንት ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት ያደረጉት የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ወደ ባህር ዳር ሲመለሱ የመኪና አደጋ እንደደረሰባቸውና የሾፌራቸውም ህይወት እንዳለፈ በእርሳቸው ላይም ጉዳት እንደደረሰ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ ትክክለኛ አለመሆኑን የክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አሰማኸኝ አስረስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ወደ ገደውሃ ሲሄዱም ሆነ ወደ ባህር ዳር ሲመለሱ በሄሌኮፍተር እንደተጓዙ አስታውሰው በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ #ከእውነት_የራቀ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ገዱ በተከሰተው ግጭት ዙሪያ ከገንዳ ውሀ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገው መመለሳቸውን አቶ አሰማኸኝ ገልፀዋል፡፡

ምንጭ፦ EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአማራ ክልል መንግስት‼️

የአማራ ክልል መንግሥት በማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች #የተፈናቀሉ ዜጎችን በሁለት ወራት ውስጥ ወደ ቀያቸው ለመመለሥ እየሠራ መሆኑን የክልሉ መንግሥት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ #አሰማኸኝ_አስረስ ተናገሩ፡፡

አቶ አሰማኸኝ እንዳሉት በክልሉ ያሉት አጠቃላይ ተፈናቃዮች ቁጥር 90 ሺህ 736 ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ 60 ከመቶ አካባቢው ተፈናቃዮች ደግሞ ከማዕከላዊ እና ምዕራብ ጎንደር የተፈናቀሉ ናቸው፡፡

ተፈናቃዮችን በሁለት ወራት ውስጥ መልሶ ለማቋቋም የክልሉ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሆነም አቶ አሰማኸኝ አስታውቀዋል፡፡

በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር የተቃጠሉ ቤቶችን ለመገንባት ከሚፈለገው የቤት ክዳን ቆርቆሮ 50 ከመቶውን መንግሥት መግዛቱን ያስታወቁት አቶ አሰማኸኝ ቀሪውን መንግሥት ከለጋሽ አካላት እየጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በማዕከላዊ ጎንደር 4 ሺህ 361 ቤቶች እና በምዕራብ ጎንደር 1 ሺህ 500 ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡

በመሆኑም የክልሉ መንግሥት 5 ሺህ 861 ቤቶችን ገንብቶና መንደር መሥርቶ ዜጎችን ሊያቋቁም መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡

የሚገነቡት ቤቶች እንደ ቤተሰብ ብዛት የሚለያዩ ናቸው፤ አራትና ከዚያ በታች አባላት ላሉት ቤተሰብ ባለ 40 ቆርቆሮ፣ ከአራት በላይ የቤተሰብ አባላት ላሏቸው ደግሞ ባለ 60 ቆርቆሮ ቤት እንደሚገነባ ነው የተናገሩት፡፡

#የመከላከያ_ሠራዊትና የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች ኃላፊነቱን ወስደው በዞኖቹ እየሠሩ እንደሆነ አስታውቀው ‹‹ከዚህ በኋላ ወንጀለኞችን ለአንድም ደቂቃ ቢሆን አንታገስም›› ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
በአማራ ክልል ከሚገኙ 90 ሺህ 736 ተፈናቃዮች 25 ከመቶው በመጠለያ ይገኛሉ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ በዘመድ ወዳጅ ተጠግተዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ናቸው፡፡

ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ቀያቸው #ለመመለስም እየተሰራ መሆኑን አቶ አሰማኸኝ አስታውቀዋል፡፡ ለዚህም ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ጋር ውጤታማ #ምክክር እየተደረገ ነው ብለዋል። አፈጻጸሙም የተፈናቀሉት ወገኖች ጋር መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ የሚተገበር ይሆናል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቤንሻንጉል ጉምዝ
/ከጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት/

የአማራ ክልል ቃል አቀባይ አቶ #አሰማኸኝ _አስረስ በቤንሻንጉል ጉሙዝ በነበረው ግጭት ዙርያ ለአለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት የተናገሩት፦

"በቤንሻንጉል ሰሞኑን በነበረው ሁከት በአማራ ተወላጆች (በአካባቢው 'ቀይ' ይባላሉ) ላይ የግድያ፣ የዘረፋ እንዲሁም የማሳደድ ተግባር ተፈፅሟል። እስካሁን ባለኝ መረጃም ወደ 17 ሰዎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 11ዶቹ የአማራ ክልል ተወላጆች ሲሆኑ ቀሪዎቹ የአካባቢው ሰዎች ናቸው። እስካሁን መረጃ ባልተሰበሰበባቸው አካቢዎች ሌሎች ሰዎች ተገድለውም ሊሆን ስለሚችል ማጣራት እያረግን ነው። ግጭቱ የጀመረው ሚያዝያ 17 በዳንድር ወረዳ ሲሆን መነሻው በእቃ ጫኝ እና አውራጆች መሀል ነበር። በዚህ መሀል የአንድ የአካባቢው ሰው ህይወት ያልፋል። ከዚያ በሁዋላ ባሉት ሶስት ቀናት ያንን ለመበቀል ጥቃቶች በቀስት፣ ወንጭፍ እና በጥይት ተፈፀመዋል። #በሁለቱም ወገን የበቀል እንቅስቃሴዌች ሲደረጉ ነበር። ትናንት ብቻ በፓዌ ወረዳ አባወሬኛ ቀበሌ 25 ቤቶች ተቃጥለዋል፣ እነዚህ የጉሙዞች ቤቶች ናቸው። ዛሬ አንድ ግብረ- ሀይል ሁኔታውን ለማርገብ ወደቦታው እያመራ ነው።" @eliasmeseret

@tsegabwolde @tikvahethiopia