TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአማራ ክልል መንግስት‼️

የአማራ ክልል መንግሥት በማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች #የተፈናቀሉ ዜጎችን በሁለት ወራት ውስጥ ወደ ቀያቸው ለመመለሥ እየሠራ መሆኑን የክልሉ መንግሥት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ #አሰማኸኝ_አስረስ ተናገሩ፡፡

አቶ አሰማኸኝ እንዳሉት በክልሉ ያሉት አጠቃላይ ተፈናቃዮች ቁጥር 90 ሺህ 736 ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ 60 ከመቶ አካባቢው ተፈናቃዮች ደግሞ ከማዕከላዊ እና ምዕራብ ጎንደር የተፈናቀሉ ናቸው፡፡

ተፈናቃዮችን በሁለት ወራት ውስጥ መልሶ ለማቋቋም የክልሉ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሆነም አቶ አሰማኸኝ አስታውቀዋል፡፡

በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር የተቃጠሉ ቤቶችን ለመገንባት ከሚፈለገው የቤት ክዳን ቆርቆሮ 50 ከመቶውን መንግሥት መግዛቱን ያስታወቁት አቶ አሰማኸኝ ቀሪውን መንግሥት ከለጋሽ አካላት እየጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በማዕከላዊ ጎንደር 4 ሺህ 361 ቤቶች እና በምዕራብ ጎንደር 1 ሺህ 500 ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡

በመሆኑም የክልሉ መንግሥት 5 ሺህ 861 ቤቶችን ገንብቶና መንደር መሥርቶ ዜጎችን ሊያቋቁም መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡

የሚገነቡት ቤቶች እንደ ቤተሰብ ብዛት የሚለያዩ ናቸው፤ አራትና ከዚያ በታች አባላት ላሉት ቤተሰብ ባለ 40 ቆርቆሮ፣ ከአራት በላይ የቤተሰብ አባላት ላሏቸው ደግሞ ባለ 60 ቆርቆሮ ቤት እንደሚገነባ ነው የተናገሩት፡፡

#የመከላከያ_ሠራዊትና የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች ኃላፊነቱን ወስደው በዞኖቹ እየሠሩ እንደሆነ አስታውቀው ‹‹ከዚህ በኋላ ወንጀለኞችን ለአንድም ደቂቃ ቢሆን አንታገስም›› ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
በአማራ ክልል ከሚገኙ 90 ሺህ 736 ተፈናቃዮች 25 ከመቶው በመጠለያ ይገኛሉ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ በዘመድ ወዳጅ ተጠግተዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ናቸው፡፡

ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ቀያቸው #ለመመለስም እየተሰራ መሆኑን አቶ አሰማኸኝ አስታውቀዋል፡፡ ለዚህም ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ጋር ውጤታማ #ምክክር እየተደረገ ነው ብለዋል። አፈጻጸሙም የተፈናቀሉት ወገኖች ጋር መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ የሚተገበር ይሆናል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ተስፋዎች🔝

#የTikvah_Ethiopia ሴት አባላት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እና በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ሊሰሩ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ አጭር ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: ለበርካታ ወጣት #ሴቶች አርአያ ለመሆን እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች በቀጣይ ሊሰሯቸው ባሰቧቸው ስራዎች ዙሪያም በመጪው ሳምንት #ምክክር ያደርጋሉ:: በዛሬው ውይይት ላይ የተካፈሉት #አብዛኞቹ #የStopHateSpeech አስተባባሪዎች ናቸው::

@tsegabwolde @tikvahethiopia