TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
“አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #የመኪና_አደጋ አልደረሰባቸውም” አቶ አሰማኸኝ አስረስ
.
.
በማህበራዊ ሚዲያ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው የመኪና አደጋ እንደደረሰባቸው ተደርጎ እየተናፈሰ ያለው ወሬ ሃሰት መሆኑን የክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አሰማኸኝ አስረስ ተናግረዋል።

via Ahadu Radio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
“አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #የመኪና_አደጋ አልደረሰባቸውም” አቶ አሰማኸኝ አስረስ
.
.
.
በማህበራዊ ሚዲያ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው የመኪና አደጋ እንደደረሰባቸው ተደርጎ እየተናፈሰ ያለው ወሬ ሃሰት መሆኑን የክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ #አሰማኸኝ_አስረስ ተናገሩ።

በምዕራብ ጎንደር ገንዳ ውሃ ከተማ ሰሞኑን በተከሰተው ግጭት ዙሪያ ትናንት ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት ያደረጉት የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ወደ ባህር ዳር ሲመለሱ የመኪና አደጋ እንደደረሰባቸውና የሾፌራቸውም ህይወት እንዳለፈ በእርሳቸው ላይም ጉዳት እንደደረሰ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ ትክክለኛ አለመሆኑን የክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አሰማኸኝ አስረስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ወደ ገደውሃ ሲሄዱም ሆነ ወደ ባህር ዳር ሲመለሱ በሄሌኮፍተር እንደተጓዙ አስታውሰው በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ #ከእውነት_የራቀ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ገዱ በተከሰተው ግጭት ዙሪያ ከገንዳ ውሀ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገው መመለሳቸውን አቶ አሰማኸኝ ገልፀዋል፡፡

ምንጭ፦ EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአማራ እና የትግራይ ክልሎች ርዕሰ መስተዳድሮች በዝግ እየመከሩ ነው። ርዕሰ መስተዳድር #ገዱ_አንዳርጋቸው እና ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር #ደብረጽዮን_ገብረሚካኤል አዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል ላይ እየተወያዩ ነው፡፡ በሁለቱ ክልሎች ወቅታዊ ሁኔታና ሠላም ላይ ነው እየተወያዩ ያሉት፡፡ የሀይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎችም አብረው እያወያዩዋቸው ይገኛሉ።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አማራ🕊ትግራይ!!

‹‹አዲስ አበባ ስለሰላም ተናግሬ ከዚያ ሌላ ብናገር ይጠይቀኛል፤ ሄጄ የምሠራውም ከዚህ እንደምናገረው ነው፡፡›› የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው

‹‹ይህች መሬት ሄደች ለኛ አጀንዳ አይደለም፤ ሊያጋጨንም አይገባም፡፡ ሕዝቡም ግጭት አይፈልግም፤ የአማራ ሕዝብ ከግጭትም አትርፎናል እላለሁ፡፡›› የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር #ደብረጽዮን_ገብረሚካኤል
.
.
የአማራና ትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድሮች በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል ከሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ጋር እየተወያዩ ነው፡፡ በመድረኩም ሁለቱ ርዕሰ መስተዳድሮች ንግግር አድርገዋል፡፡

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ‹‹ስለሰላም ተጨንቃችሁና አስባችሁ ባሕር ዳርና በሌሎችም ክልሎች ተዘዋውራችሁ አስተምራችሁናል፤ መክራችሁናል፡፡ ይህ ደግሞ ከሃይማኖት አባቶች፣ ሽማግሌዎችና እናቶች የሚጠበቅ ነው፡፡ የሰላም አጀንዳ ይዛችሁ በዚህ ወቅት በመንቀሳቀሳችሁና እንድንገናኝ ጥረት ስላደረጋችሁ በአማራ ክልል ሕዝብ ስም አመሠግናለሁ›› ብለዋል፡፡

‹‹ኢትዮጵያ ሰላም እንድንትሆን የምንመኛው ስለሆነ አካል ብለን ሳይሆን ለሁሉም መሠረት ስለሆነ ነው፡፡ ትንሽ ጊዜ እንኳ ግጭቶች ሲኖሩ ምን ያህል ጉዳት እንደሚደርስ እያየነው ነው፡፡ የአማራ ሕዝብ ከወንድሞቹና ከጎረቤት ክልሎች፣ ከትግራይ ሕዝብ ጋር ሰላም መሆን ይፈልጋል፤ ለዚህ የሰላም አጀንዳችሁም አመሠግናለሁ፡፡ የምመራው ሕዝብም ሰላም ይፈልጋል፤ ለመሥራት፣ ለመኖር፣ ለመሻሻል… የሚፈልግ ነው፡፡ ይህንንም ስታወያዩት ነግሯችኋል፡፡ እኔም ዝግጁ ነኝ፡፡ ሰላምን የሚጠላው ሰይጣናዊ አስተሳሰብ የተጠናወተው ነው›› ነው ያሉት አቶ ገዱ፡፡

‹‹የአማራና ትግራይ ሕዝቦች ለሺህ ዘመናት የጋራ ሃይማኖት፣ ባሕልና እሴት ያላቸው አንዱ በአንዱ የሚሰጋ ሳይሆን የሚኮራ ሕዝቦች ናቸው፤ ይህ ግን ከጊዜ ጊዜ እየተሸረሸረ መጥቷል፡፡ ሕዝቡ ሰላማዊ ፍላጎቱ በሰላም እንዲፈታ እንጅ እንዲጋጭ በፍጹም አይፈልግም፡፡ ያሉ ጥያቄዎች በውይይት በሰላም የሚፈቱበትን ሁኔታ ነው የሚፈልገው›› ሲሉም ተናረዋል፡፡

የአማራ ክልል ሕዝብ የተጀመረው ለውጥ እንዳይቀለበስ የሚሰጋና ከፍተኛ ጉጉት ያለው መሆኑንም ነው የተናሩት፡፡ ‹‹እኛም የዚህ ሕዝብ መሪዎች ነን፡፡ እኔ የምመራው ሕዝብ ችግሮቹን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ውጭ ብሔድ ይጠይቀኛል፡፡ ከክልሎች ጋር በሰላም መኖር ይፈልጋል፡፡ አዲስ አበባ ስለሰላም ተናግሬ ከዚያ ሌላ ብናገር ይጠይቀኛል፤ ሄጄ የምሠራውም ከዚህ እንደምናገረው ነው፡፡ አትጠራጠሩ የአማራ ሕዝብ ከትግራይ ሕዝብ ጋር ግጭት ጀማሪ አይሆንም፡፡ ከወንድሞቻችን የትግራይ አመራሮችና የትግራይ ሕዝብ ጋር በውይይት መፍታት እንችላለን፡፡ ቃሌ ፊርማዬ ነው ለሰላም እሠራለሁ›› ብለዋል አቶ ገዱ አንዳርቸው፡፡

የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤም የሀገር ሽማግሌዎችንና የሃይማኖት አባቶችን አመስግነዋል፡፡ ‹‹በሕዝብ ብትመረጡም ባትመረጡም የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ስለሆናችሁ አክብሬያችሁ ተገኝቻለሁ፡፡ እኛ የፖለቲካ መሪዎች መሥራት የሚገባንን ስላልሠራንና ስለተጨነቃችሁ አመሠግናለሁ፡፡ በታሪክ ያላየናቸውን ድርጊቶች እያዬን ስለመጣን አሳስቧችሁ ስለመጣችሁ አመሠግናለሁ›› ብለዋል፡፡

‹‹ግንኙነታችን ከወንድምነትም በላይ ነው፤ የፖለቲካ ጓዶች ነን፡፡ የሀገራችን እሴቶች ብቻ ሳይሆን የድርጅታችንም እሴት መሸርሸር ስላለ ነው እናንተንም ወደዚህ ጉዳይ የጋበዝናችሁ፡፡ ከዚህ ችግር ቶሎ መውጣት አለብን፤ መጨነቅ ብቻ ሳይሆን ብዙ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች አሉ›› ነው ያሉት ዶክተር ደብረጽዮን፡፡

‹‹ተግባራችን ታሪካችንን የሚያስጠብቅ አይደለም፡፡ ወደኋላ ተመልሰን ታሪካችን ስናይ ከሀገራቸው የተሰደዱና በሃይማኖት የማይመስሉንን ሰዎች በመሆናቸው ተቀብለናል›› ነው ያሉት ዶክተር ደብረጽዮን፡፡

‹‹ፍትሕ ላጡ የሚረዳና ልዩነትን የማይቀበልና እንደ ሰው አብሮ መኖርን የሚያውቅ ታሪክ ያለን ነን፤ አሁን እየታዬ ያለው ድርጊት መጤ ነው፡፡ ባሕላችንና ታሪካችን አሁን ከሚታዬው የተለዬ ነው፡፡ የምንገኘው ከውርደትም ውርደት ውስጥ ነው፡፡ የድሮ የወላጆቻችንን መከባበር በመያዝ ብቻ ብዙ ርቀት መጓዝ እንችላለን፡፡ ለሌላው ዓለም የሚተርፍ ታሪክ ነው ያለን፤ እንዲህ ያለ ታሪክ እያለን ግን እንዲህ ወዳለው ሁኔታ እንዴት ገባን?›› ሲሉም ጥያቄ አዘል ሐሳባቸውን ዶክተር ደብረጽዮን ገልጸዋል፡፡

የድንበርም ሆነ የሰላም ጉዳይ በድርድር መሆን ያለበት ነው ያሉት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ‹‹መገዳደል ኋላ ቀርነት ነው፤ የአራዊት ሥራና ኃጢአትም ነው፡፡ ግን የአመራሩ አካል ስለሆንን የችግሩም አካል ነን፡፡ የተበላሸ ፖለቲካ ስላለ ወደኋላ ትተን ተደጋግፈን መሥራት እንዳለብን አምናለሁ›› ብለዋል፡፡

‹‹የተበላሸውየ እገሌ የእገሌ ነው ስለማይባል ፖለቲካችን ውለን አድረን ማስተካከል አለብን፤ የሰላም ጉዳይ ግን ለነገ አይባልም፡፡ የፖለቲካ ልዩነት አስቀድመን ሰላማችንን ማጣት የለብንም፡፡ በአማራ ላይ የምናነሳው የተለዬ ጥያቄ የለንም፤ ጥቂት ሰዎች ግን የሚያበጣብጡን አሉ፡፡ ይህች መሬት ሄደች ለኛ አጀንዳ አይደለም፤ ሊያጋጨንም አይገባም፡፡ ሕዝቡም ግጭት አይፈልግም፤ የአማራ ሕዝብ ከግጭትም አትርፎናል እላለሁ፡፡ ተፈናቅለው የመጡ የትግራይ ሰዎች አሉ፤ ግን የአማራ ሕዝብ ግጭቱን ቀንሶታል›› ነው ያሉት ዶክተር ደብረጽዮን፡፡

‹‹የአማራና የትግራይ ሕዝብ ዘመድ ብቻም አይደለም፤ ከዚያ በላይ ነው ግንኙነቱ፡፡ ችግር ያለው ፖለቲከኞች ላይ ነው፡፡ ሕዝቡ ወደግጭት አታስገቡን ነው እያለ ያለው፡፡ በእኛ በኩልም እንደ አመራር ለመጋጨት አንፈልግም፡፡ ከትግራይ የሚተኮስ ነገር አይኖርም፤ ግፊቶች ግን አሉ፡፡ ሁሉም ኃላፊነት ከወሰደ ግጭቶች አይኖሩም፤ ታሪካችንም አይፈቅድም፡፡ ፖለቲካችን በፖለቲካው መድረክ እናየዋለን፤ ድርጅትም መንግሥትም ሕዝብም እየተናበብን እየሠራን ነው፤ የምትመክሩንን እየሰማን እያስተካልን እንሄዳን›› ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ🔝ርዕሰ መስተዳድር #ገዱ_አንዳርጋቸው እና ርዕሰ መስተዳድር #ለማ_መገርሳ በኔዘርላንድ በሚገኙ ኩባንያዎች ያደረጉት ጉብኝት።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው መልቀቂያ ጥያቄ አቀረቡ። የአማራ ክልል ምክር ቤት እያደረገ ባለው ስብሰባ ጥያቄው ተቀብሏል፡፡

Via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ #ተሿሚ ሚኒስትሮች ቃለ መሃላ ፈጽመዋል!

--- አቶ #ለማ_መገርሳ - ሀገር መከላከያ ሚኒስትር
--- አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
--- ኢንጂነር #አይሻ_መሀመድ - የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ግብፅ

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ምኒስትር #ገዱ_አንዳርጋቸው ወደ ግብፅ አቅንተው ከፕሬዝዳንት አብዱል ፋታኅ አል-ሲሲ ተገናኝተዋል። ውጭ ጉዳይ ምኒስትሩ ፕሬዝዳንቱን ሲያገኙ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ እና የጠቅላይ ምኒስትሩ ልዩ አማካሪ አቶ ግርማ ብሩ አብረዋቸው ነበሩ።

Via #Eshet_Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ክቡር አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው ግብፅ ናቸው...

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ክቡር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በግብፅ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ካይሮ ይገኛሉ፡፡ በጉብኝታቸውም ከግብፁ ፕሬዚደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት ፣ በአካባቢያዊና በአለም አቀፋዊ የጋራ ጉዳዮች ላይ #መወያየታቸውን በግብፅ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አመልክቷል። እንዲሁም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በካይሮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጽህፈት ቤት በመገኘት ከሰራተኞቹ ጋር ዉይይት አድርገዋል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሀምሌ 22 የሚካሄደውን #የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር መሠረት በማድረግ በሚሲዮኑ ጽህፈት ቤት የችግኝ ተከላ አካሂደዋል፡፡

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ #ገዱ_አንዳርጋቸው፣ የመከላከያ ሚኒስትር አቶ #ለማ_መገርሣ ና በዩጋንዳ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዓለምፀሐይ መሰረት በካምፓላ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ አባላት ጋር በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia