TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኤዶ በኦሮሚያ እና ሲዳማ ክልል አዋሳኝ  በምትገኘው በሲዳማ ክልል፣ ወንዶ ገነት ወረዳ የኤዶ ቀበሌ በትላንትናው ዕለት አለመረጋጋት መፈጠሩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከፀጥታ አከላት እንዲሁም ከነዋሪዎች ያገኘው መረጃ ያመለክታል። " ኤዶ " በኦሮሚያ እና ሲዳማ አዋሳኝ የምትገኝ ቀበሌ ስትሆን ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ መሰል አለመረጋጋት ፣ መንገድ የመዝጋት፣ ንግድ እና ትራንስፖርት የማስተጓጎል ችግሮች ሲከሰቱ…
" ሀገር መከላከያ መግባቱን ተከትሎ ትራንስፖርት ተጀምሯል " - አቶ ገዛህኝ ዴኔሞ

በሲዳማና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ በምትገኘዉ የኤዶ ቀበሌ በተፈጠረ የፀጥታ ችግር አንድ ሰዉ ተጎድቶ ሆስፒታል ሲገባ ለሰአታት መንገድ ተዘግቶ መቆየቱ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከነዋሪዎች ለመረዳት ችሏል።

ከአመታት በፊት በህዝበ ውሳኔ ወደሲዳማ ክልል ከተቀላቀለች ጀምሮ ውጤቱን አንቀበልም ባሉ አካላት በተደጋጋሚ ሰላም ርቋት የቆየችዉና ሰላሟን ለማጽናት የፌደራል የጸጥታ አካላት  በአካባቢዉ እንዲቀመጡ ተደርገዉ የነበሩባት ኤዶ ከትላንት ሌሊት ጀምሮ ውጥረት ውስጥ መሆኗ ታውቋል።

በአካባቢዉ ድንገት ትራንስፖርት ከልክለው የሰዎችን እንቅስቃሴ  የገደቡ አካላት ለተወሰኑ ሰአታት ቀበሌዋን መቆጣጠራቸዉን የገለጹት ነዋሪዎቹ የተኩስ ድምጾች እንደተሰሙና ሰዎች በየቤታቸዉ ለሰአታት መቀመጣቸውን ገልጸዋል።

አንድ የወንዶ ገነት የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ፤ " እኛ መፍትሄ እንፈልጋለን ስንት ጊዜ ሆነን እንዲ ስንሰቃይ ስራ እንኳን በአግባቡ መስራት አልቻልንም በስጋት ነው የምንመላለሰው " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ የኤዶ ጎረቤት የሆነችዉ የወሻ ቀበሌ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ገዛህኝ ዴኔሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት ከኤዶ ወደወሻም ሆነ ከወሻ ወደኤዶ ትራንስፖርት ተቋርጦ ማርፈዱን ገልጸዋል።

አሁን ላይ መከላከያ መግባቱን ተከትሎ ትራንስፖርት መጀመሩን የሚገልጹት አቶ ገዛሀኝ ፤ አንድ እግሩ አካባቢ የተመታ ወጣትም ወደሆስፒታል መወሰዱን ጨምረዉ ነግረዉናል።

በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸዉ የወረዳዉ የጸጥታ ጉዳይ ሀላፊው አቶ ሀማሮ ሀይሶ አሁን ላይ ሁኔታዉን በማረጋጋት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዉ ከሰአታት በኋላ ሙሉ  መረጃዉን እንደሚያደርሱን ገልጸውልናል።

ከወራት በፊት በዚሁ ቦታ የፀጥታ ችግር ተከስቶ ነዋሪው ክፉኛ ሲንገላታ እንደነበር ፤ ሰርተው ገቢ የሚያገኙ ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ ሰዎች ስራ ውለው መግባት እንደተሳናቸው ፣ መንገድ በመዘጋቱም ነዋሪው ብዙ ብር ከፍሎ በሻሸመኔ ዞሮ ወንዶ ገነት ለመግባት ተገዶ እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ መዘገቡ ይታወሳል።

መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው በሀዋሳው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።

(ተጨማሪ መረጃዎች ይኖሩናል ይጠብቁ)

ፎቶ፦ አካባቢውን የሚያሳይ /ፋይል/ በቲክቫህ ኢትዮጵያ ወንዶገነት ቤተሰብ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE  የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ያወጣውን የሃዘን መገለጫ ዋቢ በማድረግ ጥር 3 /2016 በትግራይ ማእከላዊ ዞን ‘የእምባስነይቲ ቅርንጫፍ’ የአምቡላንስ ሹፌር አቶ ወልዱ አረጋዊ በርሀ የወላድ እናትን ህይወት ለማዳን እያሽከረከረ ባለበት ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ማለፉ መዘገባችን ይታወሳል። የቀይ መስቀል የአምቡላንስ ሹፌሩ እንዴት ለህልፈት እንደበቃ የሚያትት…
#ERCS

በአማራ ክልል #ታጣቂዎች የሰብዓዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን መውሰዳቸው ተሰማ።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ንብረት የሆኑ ባለ 5 በር ላንድክሩዘር የሰሌዳ ቁጥራቸው ፦
➡️ 5-02826
➡️ 5-02830 ተሽከርካሪዎች የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ማኅበሩ የሚያከናውነውን ሰብዓዊ ተግባር ለማገዝ ወደ ደቡብ ጎንደር እና ሰሜን ጎንደር ዞኖች በመጓዝ ላይ እያሉ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሞጣ ከተማ 30 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ልዩ ሥሙ " አስተርዮ ማርያም " በሚባል ቦታ በታጠቁ ኃይሎች ተወስደዋል፡፡

ማህበሩ ከላይ የተጠቀሱትን ተሽከርካሪዎች በመጠቀም ለሚፈፀመው የትኛውም ዓይነት ተግባር ኃላፊነት እንደማይወስድ አሳውቋል።

ተሽከርካሪዎቹን የወሰዱት ታጣቂ ኃይሎች ለማኅበሩ እንዲመልሱና ለተለመደው ሰብዓዊ አገልገሎት ተግባር እንዲውሉ ጠይቋል።

በተመሳሳይ የካቲት 09 ቀን 2016 ዓ.ም በዋግ ኸመራ ዞን ያጋጠመውን ድርቅ ተከትሎ ለጉዳት የተጋለጡ ወገኖችን ለመርዳት የሚያስችል ሰብዓዊ ተግባር አከናውኖ ከሰቆጣ ከተማ ወደ ኮረም ከተማ በመጓዝ ላይ በነበረ የማኅበሩ ቀላል ተሽከርካሪ ኮረም ከተማ ለመድረስ 3 ኪ.ሜ ሲቀረው ልዩ ሥሙ " ፋላ ገበያ " በተባለ አካባቢ በታጣቂ ኃይሎች በተከፈተበት ድንገተኛ ተኩስ #በሰው_ላይ_የደረሰ_ጉዳት_ባይኖርም በተሽከርካሪው ላይ ጉዳት ሊደርስ መቻሉ ተገልጿል።

ማኅበሩ ከቀን ወደ ቀን በሠራተኞቹ፣ በጎፈቃደኞቹ እና ተሽከርካሪዎቹ ላይ በሚፈፀምበት ጥቃት ምክንያት ሰብዓዊ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ወገኖች ለመድረስ ፈተና እየሆነበት እንደመጣ አሳውቋል።

ጥቃት ሚፈፅሙ የትኛውም ተፋላሚ ኃይሎች ድርጊቱ ኢትዮጵያ የፈረመችውን ዓለም አቀፍ የጄኔቫ ሥምምነቶችን የሚፃረር እና ከማኅበሩ ዓላማ ውጪ መሆኑን ተረድተው ከመሰል ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እንዲሁም ማኅበረሰቡ ድርጊቶቹን #እንዲያወግዝ ተማፅኗል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ERCS በአማራ ክልል #ታጣቂዎች የሰብዓዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን መውሰዳቸው ተሰማ። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ንብረት የሆኑ ባለ 5 በር ላንድክሩዘር የሰሌዳ ቁጥራቸው ፦ ➡️ 5-02826 ➡️ 5-02830 ተሽከርካሪዎች የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ማኅበሩ የሚያከናውነውን ሰብዓዊ ተግባር ለማገዝ ወደ ደቡብ ጎንደር እና ሰሜን ጎንደር ዞኖች በመጓዝ ላይ እያሉ በምስራቅ ጎጃም ዞን…
#Update

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፤ የሰብአዊ ዲፕሎማሲ እና የኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ኃላፊ አቶ መስፍን ደረጄ በማህበሩ ተሽከርካሪ ላይ ስለተፈፀመው ጥቃት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ምን አሉ ?

- ጥቃቱ የተፈፀመው የካቲት 9/2016 ዓ/ም ከቀኑ 10:30 ነው።

- ጥቃት የደረሰበት ተሽከርካሪ ድርቅ ባለባቸው የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር አካባቢዎች የሚሰጥ ድጋፍን በተመለከተ ጥናት ለማድረግ የተንቀሳቀሰ ሲሆን አንድ የእርዳታ ሰራተኛ እና አሽከርካሪውን የያዘ ነበር።

- " አድ ነባ " የተባለ አካባቢ ሲደርሱ የታጠቁ ኃይሎች ተሽከርካሪው ላይ ጥቃት ከፍተዋል ፤ ቦንብም አፈንድተዋል።

- ጥቃቱ የጥይት ተኩስ ብቻ አልነበረም።

- በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።

-  የተሽከርካሪው መስታወቶች ተበትነዋል።

- ታጣቂዎቹ ሰዎቹ የቀይ መስቀል ሠራተኞች መሆናቸውን ሲያውቁ #ለቅቀዋቸዋል

- ከጥቃቱ በኋላ ሠራተኞቹ በዕለቱ በሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ላይ በተፈጸመ ጥቃት እግሩ ላይ በጥይት የተመታ የ16 ዓመት ልጅን ጭነው ኮረም ከተማ ወደ የሚገኝ ሆስፒታል አድርሰዋል።

- በተፈጸመባቸው ጥቃት የተነሳ ሠራተኞቹ እያከናወኑ የነበረውን ጥናት አቋርጠው በአሁኑ ሰዓት ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ ናቸው።

የጥቃት አድራሾቹን እነማን ናቸው ?

ኃላፊው " እኛ እንደዚህ ዓይነት ነገር የምናጣራበት መንገድ የለም። ግን የታጠቁ ኃይሎች ናቸው " ሲሉ መልሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የቢቢሲ አማርኛው ክፍል መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
#PretoriaAggrement

አሜሪካ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር እና በኢትዮጵያ ከአሜሪካ አምባሳደር ኤቪን ማሲንጋ ጋር ሆነው ወደ ትግራይ መቐለ ተጉዘው ከክልሉ ባለልስጣናት ጋር ውይይት አድርገዋል።

አምባሳደር ሀመር ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ከሌሎች ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ውይይት አሜሪካ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር አሜሪካ ድጋፏን እንደምታደርግ ገልጸዋል።

የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ ቀደመው ህይወት ለመመለስ ለተጀመረው ስራ 15 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ እንደምታደርግም በይፋ አሳውቀዋል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው ፤ የአሜሪካ መንግስት የሰላም ሂደቱ እንዲቀጥል ፣ የፕሪቶሪያው ውል እንዲተገበር የሚያደርገውን ጥረት የሚደነቅ ቢሆንም ከዚህ በላይ አጠናክሮ መስራት አለበት ብለዋል። 

መቐለ የሄዱት አምባሳደር ማይክ ሃመር እና አምባሳደር ማሲንግ ከቀናት በፊት አዲስ አበባ ውስጥ አቶ ጌታቸው ረዳን ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ ጋር በመሆን አግንኝተዋቸው መክረው ነበር።

#TikvahFamilyMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#PretoriaAggrement አሜሪካ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በተሟላ ሁኔታ እንዲተገበር ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች። የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር እና በኢትዮጵያ ከአሜሪካ አምባሳደር ኤቪን ማሲንጋ ጋር ሆነው ወደ ትግራይ መቐለ ተጉዘው ከክልሉ ባለልስጣናት ጋር ውይይት አድርገዋል። አምባሳደር ሀመር ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ከሌሎች…
#USA

አምባሳደር ሃመር እና አምባሳደር ማሲንጋ በመቐለ ቆይታቸው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (TPLF) ሊቀመንበር የሆኑትን ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤልን አገኝተው ተወያይተዋል።

ውይይታቸው የፕሪቶሪያ ስምምነትን አተገባበርን የተመለከተ ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በትግራይ በኩል በፕሪቶሪያ ስምምነት ውል አተገባበር ዙሪያ ብዙ ጉዳዮች ቢፈፀሙም ፦
- ከጦርነት በፊት የነበረው የትግራይ አስተዳደር ግዛት መመለስ
- ህዝብ ነፃ የማውጣት ፣
- ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ ፣
- ለረሃብ ለተጋለጠ ህዝብ ሰብአዊ እርዳታ የማቀረብ ጉዳዮች ሳይፈፀሙ ረጅም ጊዜ መውሰዳቸው ለልኡካኑ ገልፀዋል።

ተመላሽ የሰራዊት አባላት የማቋቋም ጉዳይ ትኩረት የሚሻ ቢሆንም  ቀዳሚው ጉዳይ ከጦርነት በፊት የነበረው የትግራይ አስተዳደር ማረጋገጥና ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ መሆኑ ዶ/ር ደብረፅዮን መግለፃቸውና ውይይቱ በቀጣይ ለሚኖሩ ለውጦች የሃሳብ ልውውጥ እንዲደረገ መግባባት መደረሱ ለማወቅ ተችሏል። 

#TikvahFamilyMekelle
                    
@tikvahethiopia            
#Ethiopia #US

አሜሪካ ከ #አማራ_ፋኖ ታጣቂዎች ጋር የሰላም ንግግር እንዲጀመር የኢትዮጵያ መንግሥትን እንደጠየቀች አሳውቃለች።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ እንዲሁም የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር በኦንላይን መግለጫ ሰጥተው ነበር።

መግለጫቸው ባለፉት ቀናት በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ቆይታ የተመለከተ ነበር። 

በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ጨምሮ ከተለያዩ ባለስልጣናትና የተቋማት መሪዎች ጋር በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች #በውይይት እንዲፈቱ መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።

አሜሪካ በኦሮሚያ እየተካሄደ ያለው ግጭት እልባት እንዲያገኝ የበኩሏን ሚና እየተጫወተች መሆኑን ገልጸው በአማራ ክልልም ግጭቶች በሰላም እንዲቋጩ ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲጀመር ጥሪ መቅርቡን ተናግረዋል።

አምባሳደር ማይክ ሃመር ምን አሉ ?

" ባለፈው ሕዳር ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር በዳሬሰላም በተደረገው ውይይት ላይ በቀጥታ ተሳትፈናል። አሁን ይህን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። ግጭቱ በሰላም እንዲፈታ እንዴት መመቻቸት እንደሚቻል ለሁለቱም አካላት ሃሳብ አቅርበናል።

ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲደረግ አምባሳደር ማሲንጋ ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን እናውቃለን።

ሰላምን ለማረጋገጥ ያሉትን እድሎች በመጠቀም ጥረታችንን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። በተደጋጋሚ እንዳልነው ለነዚህ ግጭቶች ወታደራዊ መፍትሄ አማራጭ አይሆንም አሁንም ትኩረት መደረግ ያለበት ውይይት ላይ ነው። " ብለዋል።

ሞሊ ፊ ምን አሉ ?

" ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያጋጠሟትን ፈተናዎች በሰላም ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ቁርጠንኝነታቸው እንዲቀጥሉ እናበረታታለን።

በታጣቂዎች ለሚፈፀሙት ጥቃቶች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚወስዱት እርምጃ አሳሳቢነት ገልጸናል። የጸጥታው ሁኔታን አሳሳቢነት ብንረዳም የሲቪሎችን መብት ለመጠበቅ ተጨማሪ ጥሪ ያስፈልጋል " ብለዋል።

አምባሳደር ማይክ ሃመር ፤ " ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር በተደረገው ስብሰባ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ውይይት ለማመቻቸት እንዲሁም የቀጠሉትን ግጭቶች በሰላም ለመፍታት ከአማራ ፋኖ ጋር ሊደረግ የሚችል ንግግር ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳለን ገልጸናል " ብለዋል።

ሃመር በኢትዮጵያ ላለው ግጭት ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለ ገልጸው የኢትዮጵያ መንግሥትም ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁነት እንዳለው መግለፁን እናደንቃለን ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ከዚህ ቀደም ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ፅኑ አቋም እንዳለው መግለፁ ይታወቃል። ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋርም በይፋ ሁለት ጊዜ ድርድር ቢቀመጥም መጨረሻ ላይ መሳካት አልቻለም። በአማራ በኩል ከፋኖ ጋር ለድርድር ስለመቀመጥ እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።

አሜሪካውያኑ ባለስልጣናት በሰጡት መግለጫ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ሳይሳካ ቀርቶ የተቋረጠው ድርድር መቼ እንደሚቀጥል እንዲሁም መንግሥት ከፋኖ ጋር ለድርድር ይቀመጥ እንደሆነ በግልፅ ባይናገሩም የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ እንደሆነ እንዳሳወቃቸው ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ / ጋዜጠና ኬኔዲ አባተ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
" ' ባንክ ተዘረፈ ' ተብሎ የሚነዛዉ ወሬ ትክክል አይደለም " - ፖሊስ

በሀዋሳ ከተማ በሚገኘዉ ትልቁ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የተደረገው የዝርፊያ ሙከራ በቁጥጥር ስር መዋሉን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ትናንት በቀን 13/2016 ሌሊት በሀዋሳ ከተማ  በተለምዶ ሀይቅ ዳር በሚባለዉ አካባቢ በሚገኘው ትልቁ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ የዝርፊያ ሙከራ መደረጉን ተከትሎ ከፖሊስ ምርመራ ጋር በተያያዘ አገልግሎት ተቋርጦ መዋሉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

ይህን ተከትሎ በአካባቢዉ የነበሩ ተገልጋዮች ወደሌላ ባንክ ሄደዉ እንዲስተናገዱ የተጠየቁ ቢሆንም በዋናዉ ባንክ ብቻ የሚፈጸሙ ጉዳዮች ያላቸዉ ተገልጋዮች ቅሬታቸዉን ሲገልጹ ተሰተውለዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ በአንድ ወጣት አማካኝነት የዝርፊያ ሙከራ መደረጉን ገልጸዋል።

ተጠርጣሪዉ በባንኩ ጥበቃዎችና በፖሊስ  አባል እንዝህላልነት ወደ ውስጥ መግባቱንና የዝርፊያ ሙከራውን ማድረጉን ተናግረዋል።

በባንኩ ጥበቃዎች ክፍተት ወደባንኩ የገባዉ ዘራፊ በባንኩ ውስጥ ፊት ለፊት የሚገኙ የካሸር ጠረጴዛዎች ዙሪያ የመስረቅ ሙከራ አድርጎ ሊወጣ ሲል በቁጥጥር ስር መዋሉንም አስረድተዋል።

በወቅቱ የነበሩት የጥበቃ ሰራተኞችና ተጠርጣሪው ግለሰብ ተይዘዉ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የገልጹት ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ፤ በሶሻል ሚዲያ " ባንክ ተዘረፈ " ተብሎ የሚነዛዉ ወሬ ልክ ትክክል አይደለም ብለዋል።

ጉዳዩ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉንም ገልፀዋል።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የሀዋሳው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#Infinix_Hot40

ኢንፊኒክስ ሞባይል ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን አጣምሮ ያካተተውን አዲሱን ‘Hot 40 pro’ ስልክ ምርጫዎ ያድርጉ!

#InfinixEthiopia #InfinixMobile #Infinix_Hot40 #Infinix_HotSeries
25 ዓመታት በሕብረት

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

ቴሌግራም- https://publielectoral.lat/HibretBanket
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/HibretBank
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/hibretbank/
ዌብሳይት- https://www.hibretbank.com.et/
#Hibretbank
በ9ው የከተሞች ፈረም ከ1ኛ - 3ኛ የደረጃ ምድብ የተሰጣቸው የትኞቹ ከተሞች ናቸው?

124 ከተሞች ተሳታፊ በሆኑበት 9ኛው የከተሞች ፎረም ከሌሎች ሁነቶች በተጓዳኝ የከተሞች ራስን የማስተዋወቅ ውድድር ተካሂዷል።

ከተሞቹ በየደረጃቸው በ4 ምድቦች ተከፋፍለው በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ለየምድቡ በቀረቡ የመወዳደሪያ መስፈርቶች ተመዝነዋል።

በዚህም ከየምድቡ ከ1ኛ እስከ 3ኛ በተሰጣቸው ደረጃ መሠረት፦

*ምድብ 1፦ አዳማ፣ ሀዋሳ፣ ደሴ
*ምድብ 2፦ ቡታጅራ፣ ባሌሮቤ፣ ነቀምቴ
*ምድብ 3፦ ከሚሴ፣ ወራቤ፤ ሊሙገነት
*ምድብ 4፦ ኮንሶ ካራት፣ ግልገል በለስ፣ እምድብር ከ1ኛ እስከ 3ኛ በመውጣት የውድድሩ አሸናፊዎች ሆነዋል ተብሏል።

እንዲሁም ወላይታ ሶዶ፣ አዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች ደግሞ የ9ኛው የከተሞች ፎረም ልዩ ተሸላሚዎች መሆናቸውን ከመድረኩ ተሳታፊዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በደረሰ መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#ዓዳዋ

128ኛው የዓድዋ የድል በዓል መታሰብያ በልዩ ድምቀት ለማክበር ቅድመ ዝግጅቱ ማጠናቀቁ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አስታውቋል።

የድል መታሰብያ በዓሉ ከየካቲት 16/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ያህል በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር እንደሚጀምር የትግራይ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቀዋል።  

ቢሮው ፤ ከበዓሉ ጋር ተያይዞ ቀደም ሲል የፓን አፍሪካን ዩኒቨርስቲና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ለመገንባት ቃል ተገብተው ያልተፈፀሙ አሉ የተባለ ሲሆን እነዚህ በተለይ በዓድዋና አከባቢው ማህበረሰብ አሉታዊ ጫና አሳድረዋል ተብሏል።

" 128ኛው የዓድዋ የድል መታሰብያ በዓል ሲከበር ላለፉት ክብሮቻችን ትኩረት በመስጠትና ተሰንደው ለተተኪ እንዲተላለፉ በሚያደርግ መልኩ መሆን አለበት " ብሏል።

የዘንድሮ የዓድዋ የድል መታሰብያ በዓል ሲከበር ከአሰቃቂውና ደም አፋሳሹ የትግራይ ጦርነት ማግስት በተነፃፃሪ የሰላም ሁኔታ ተሆኖ ነው ያለው ቢሮ ፤ ሰላሙ ዘላቂ በማድረግ ወደ ጥቅም በሚቀየርበት አንድነትም ካለፈው በበለጠ ለማጠንከር ቃል በሚገባበት ቅኝት መሆን ይገባዋል ሲል አሳውቋል።

መረጃው በመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው ተዘጋጅቶ የተላከው።

@tikvahethiopia