#ERCS
በአማራ ክልል #ታጣቂዎች የሰብዓዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን መውሰዳቸው ተሰማ።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ንብረት የሆኑ ባለ 5 በር ላንድክሩዘር የሰሌዳ ቁጥራቸው ፦
➡️ 5-02826
➡️ 5-02830 ተሽከርካሪዎች የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ማኅበሩ የሚያከናውነውን ሰብዓዊ ተግባር ለማገዝ ወደ ደቡብ ጎንደር እና ሰሜን ጎንደር ዞኖች በመጓዝ ላይ እያሉ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሞጣ ከተማ 30 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ልዩ ሥሙ " አስተርዮ ማርያም " በሚባል ቦታ በታጠቁ ኃይሎች ተወስደዋል፡፡
ማህበሩ ከላይ የተጠቀሱትን ተሽከርካሪዎች በመጠቀም ለሚፈፀመው የትኛውም ዓይነት ተግባር ኃላፊነት እንደማይወስድ አሳውቋል።
ተሽከርካሪዎቹን የወሰዱት ታጣቂ ኃይሎች ለማኅበሩ እንዲመልሱና ለተለመደው ሰብዓዊ አገልገሎት ተግባር እንዲውሉ ጠይቋል።
በተመሳሳይ የካቲት 09 ቀን 2016 ዓ.ም በዋግ ኸመራ ዞን ያጋጠመውን ድርቅ ተከትሎ ለጉዳት የተጋለጡ ወገኖችን ለመርዳት የሚያስችል ሰብዓዊ ተግባር አከናውኖ ከሰቆጣ ከተማ ወደ ኮረም ከተማ በመጓዝ ላይ በነበረ የማኅበሩ ቀላል ተሽከርካሪ ኮረም ከተማ ለመድረስ 3 ኪ.ሜ ሲቀረው ልዩ ሥሙ " ፋላ ገበያ " በተባለ አካባቢ በታጣቂ ኃይሎች በተከፈተበት ድንገተኛ ተኩስ #በሰው_ላይ_የደረሰ_ጉዳት_ባይኖርም በተሽከርካሪው ላይ ጉዳት ሊደርስ መቻሉ ተገልጿል።
ማኅበሩ ከቀን ወደ ቀን በሠራተኞቹ፣ በጎፈቃደኞቹ እና ተሽከርካሪዎቹ ላይ በሚፈፀምበት ጥቃት ምክንያት ሰብዓዊ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ወገኖች ለመድረስ ፈተና እየሆነበት እንደመጣ አሳውቋል።
ጥቃት ሚፈፅሙ የትኛውም ተፋላሚ ኃይሎች ድርጊቱ ኢትዮጵያ የፈረመችውን ዓለም አቀፍ የጄኔቫ ሥምምነቶችን የሚፃረር እና ከማኅበሩ ዓላማ ውጪ መሆኑን ተረድተው ከመሰል ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እንዲሁም ማኅበረሰቡ ድርጊቶቹን #እንዲያወግዝ ተማፅኗል።
@tikvahethiopia