TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች‼️

"የፀጥታ እና የደህንነት ስጋት እንዳይኖር ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል።"
*
*
*
ነባርና አዲስ ተማሪዎች ተቀብሎ ለማስተናገድ የሚያስችል በቂ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉንና የተማሪ ቤተሰቦችና ተማሪዎች #ከጸጥታና #ደህንነት ሥጋት ነጻ ለማድረግ #ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ መሆኑን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡

የተማሪችን አቀባበል አስመልክቶ በዩኒቨርሲቲው በተካሄደ የምክክር መድረክ ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲጎለብት የድርሻቸውን
ሚና እንደሚወጡ ባለድርሻ አካላት ጠቁመዋል፡፡
*
*
*
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ባለፉት አስራ አንድ አመታት ሰላም የሰፈነበት የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመስራቱ በሃገር አቀፍ ደረጃ ሠላማዊ ዩኒቨርሲቲ መባሉ ይታወሳል፡፡ በዚህም በበርካታ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች ዘንድ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ እየሆነ መጥቷል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በ2020 ከሃገሪቱ ምርጥ አምስት እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን የሚያስችለውን ተግባር በማከናወንና የተማሪዎች ቅበላ አቅሙን በማሳደግ የትምህርት መርሃግብሮቹን መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ በማሻሻል ፍላጎትን መሰረት አድርጎ እየሰራም ይገኛል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የ2011 ዓ.ም የተማሪዎች ቅበላን አስመልክቶ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተወካዮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ተጠሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና የሚመለከታቸው አካላትን በማሳተፍ ምክክር በማድረግ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

በምክክር መድረኩ ተገኝተው መግለጫ የሰጡት የዩኒቨርቲው አካዳሚክ ጉዳዩች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ወንድሙ ወልዴ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደትን በማስፈንና የተማሪ ቅበላ አቅሙን 29ሺህ በማድረስ በትጋት እየሰራ መቆየቱን ነው የተናገሩት፡፡

ሠላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለማስፈን እንዲቻል ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በቅርበት ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ም/ፕሬዝዳንቱ፣ ከወቅታዊ ሃገራዊ ሁኔታዎች ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን ስጋት ለመቆጣጠር የሚያስችል ዘርፈ ብዙ ስራ ከሚመለከታቸው ባለከድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱንም አውስተዋል፡፡

ሠላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲሰፍን ከአካባቢው ማህበረሰብ፣ ከሃይማኖት አባቶች፣ መንግስትና ተቋሙ ልዩ ክትትል የሚያደርግና የተማሪ ቤተሰቦችና ተማሪዎች ከጸጥታና ከደህንነት ስጋት ነጻ ለማድረግ የሚያስችል ስራ መሰራቱንም ም/ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል፡፡

ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተናገድ እንዲቻል አስፈላጊው ዝግጅት ሁሉ በበቂ ሁኔታ መደረጉን የተናገሩት ዶ/ር ወንድሙ፣ የአካባቢው ማህበረሰብ በተለይም የጸጥታ አስከባሪዎች፣በጎ አድራጎት ማህበራት፣የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በሙላት ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገዱ ሂደት በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በመድረኩ በመሳተፍ መግለጫ ከሰጡት መካከል የሃገር ሽማግሌዎችን በመወከል አቶ ሚልኪያስ ኦሎሎ እና የሃይማኖት ተቋማትን በመወከል አቶ ሰይፉ ለታ እንደገለጹት ሠላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተናገዱ ሂደት ሁሉም ባለድርሻ በባለቤትነት ሊሳተፍ ይገባል ብለዋል፡፡

ወላይታና አካባቢው እንግዳ ተቀባይ መሆኑንና አሁን ላይ ከተማሪ ቅበላ ጋር በተያያዘ አንዳች የሚያሰጋ የጸጥታና የደህንነት ስጋት እንደሌለ ጭምር ተሳታፊቹ አውስተዋል፡፡

የወላይታ ሶዶ ከተማ ፍትህና ጸጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አንዱዓለም አዳነ አካባቢውን ከደህንነትና ከጸጥታ ስጋት ነጻ በማድረግ የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማጠናከር ከአቀባበል ጀምሮ በዘላቂነት ሰላምን ለማረጋገጥ የሚያስችል ተግባር ዘርፉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡

በዩቨርሲቲው የሰላም ፎረም ጽ/ቤት ፕሬዝዳንት ተማሪ በረከት አፈወርቅ ከዚህ ቀደም ከነበረው የተሻለ አቀባበል እንዲኖር ለማስቻል በተማሪዎች አደረጃጀት ዘርፍ የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት መደረጉንና አዳዲስ ተማሪዎችን ከዩኒቨርሲቲውና ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ለማላመድ መዘጋጀታቸውን ተናግሯል፡፡

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የህግ ት/ቤት ዲን እና የወላይታ በጎፈቃደኞች ማህበር አባል መምህር ተከተል ለቤና አዲስና ነባር ተማሪዎችን የመቀበሉን ተግባር ከማሳካት ረገድ ማህበሩና የማህበሩ አባላት ጉልህ ተሳትፎ እንደሚኖራቸው ጠቁሟል፡፡

ተማሪዎችን በበጎ ፈቃድ ለማገልገል የማህበሩ አባላት ከምንጊዜውም በበለጠ ዝግጅት ማድረጋቸውንና አቀባበሉንም ደማቅ ለማድረግ
ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርበው እየሰሩ መሆናቸውን መምህር ተከተል አውስቷል፡፡

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በ2011 የትምህርት ዘመን ከ 15 ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎችን ተቀብሎ የሚያስተናግድ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 3 ሺህ 4 መቶ ያህሉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡

የመደበኛ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ከጥቅምት 10 እስከ 14 ባሉት ጊዜያት ውስጥ እንደሚካሄድ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስተራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት መግለጹም ይታወቃል፡፡

ምንጭ፦ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቀለ⬆️ከክልላቸው ውጭ በሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት #የተመደቡ የትግራይ ክልል ተማሪዎች #ደህንነት ያሳስበናል ያሉ የመቀለ ከተማ ነዋሪዎች፣ በሮማናት አደባባይ ሰልፍ አካሂደዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወቅታዊ መግለጫ‼️

‹‹ወደ አማራ ክልል የሚመጡ የየትኛውም አካባቢ ተማሪዎች የአማራ #ልጆች ናቸው፡፡››

‹‹የግለሰቦችን ችግር #በግለሰብ ደረጃ መጨረስ ሲገባ ለጋ ወጣቶችን #መጠቀሚያ ማድረግ ተቀባይነት የለውም፡፡›› ርዕሰ መስተዳድር አቶ
ገዱ አንዳርጋቸው
.
.
.
ሃገራችን በለውጥ እንቅስቃሴ በምትገኝበት በዚህ ወቅት አልፎ አልፎ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተፈጠረው ችግር ተማሪዎች የህይዎት እና የአካል ጎዳት ደርሶባቸዋል፡፡ በዚህም የክልሉ መንግስት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን የገለፁት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የግለሰቦች ግጭት ወደ ቡድን ወይም አካባቢ ወስዶ በተደራጀ አግባብ ዕርስ በዕርስ ተማሪዎችን #ማጋጨት በምንም መንገድ #ተቀባይነት አይኖረውም ብለዋል፡፡

ችግሩ የተለየ የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው እና አሁን እየተፈጠረ ያለው አንፃራዊ ሰላምና መረጋጋት ያላስደሰታቸው አካላት በታቀደ መንገድ የሚያራምዱት የግጭት ሴራ ነው ያሉት አቶ ገዱ ተማሪዎችም #ስሜታዊ በመሆን የሌሎች አጀንዳ ፈፃሚዎች ሳይሆኑ ችግር ፈጣሪዎችን
አጋልጠው እንዲሰጡ ጠይቀዋል፡፡

ከመላ ሃገሪቱ የሚመጡ ተማሪዎችና ልጆቻቸውን አምነው የሚልኩ ወላጆች ዓላማቸው ግልፅ ነው፤ እሱም ተምሮ ትልቅ ደረጃ ላይ መድረስ፡፡ ይህንን የተማሪዎችና የወላጆች ዓላማ ስኬታማ ለማድረግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የእውቀት እንጅ የግጭት ማዕከል መሆን ስለሌለባቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለዘላቂ ሰላም በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ፡፡

ወደ አማራ ክልል የሚመጡ የየትኛውም አካባቢ ተማሪዎች የአማራ ልጆች ናቸው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የአካባቢው ማህበረሰብ ተማሪዎቹን ሲቀበል ያሳየውን ጨዋነት እና እንግዳ ተቀባይነት እስከመጨረሻው ማሳየት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡

ግጭት በተፈጠረባቸው አካባቢዎች ካሉ የዩኒቨርሲቲ #አመራር አካላት፣ የክልል መስተዳድሮችና ከፊዴራል መንግስት ጋር በተማሪዎቹ #ደህንነት ዙሪያ እየተነጋገርን ነው ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ🔝

የቡሌ ሆራ ከተማ ወደቀደመ #ሰላማዊ እንቅስቃሴዋ ብትመለስም በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተፈጠረው አለመረጋጋት ግን እስካሁን እልባት አላገኘም። ከላይ በፎቶው የምትመለከቱት ትላንት ምሽት ተማሪዎች ያደሩበትን ሁኔታ ነው። በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት መንግስት ለተቋሙ አስቸኳይ መፍትሄ ለፈልግ ይገባል ብለዋል። ጥፋተኞች እና የተማሪውን #ደህንነት አደጋ ላይ የጣሉ እንዲሁም የተቋሙ ሰላም እንዲደፈርስ እጃቸውን ያስገቡ ሁሉ ተይዘው መጠየቅ አለባቸው ሲሉ ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በቤኒሻንጉል ጉሙዝና በኦሮሚያ ክልሎች አጎራባች አካባቢዎችን የጸጥታ ችግር ለመፍታት #ኮማንድ_ፓስት ተቋቁሞ ወደ ስራ ገባ።
የኮማንድ ፖስቱ አባል አቶ ሰይፈዲን ሐሩን ፥ ኮማንድ ፖስቱ የፌደራል፣ የሁለቱ ክልሎች መንግሥታት፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊትና ፌዴራል ፖሊስ ያቀፈ ነው፡፡ኮማንድ ፖስቱ የተቋቋመው በክልሎቹ አጎራባች አካባቢዎች የመሸገውን የታጠቀ ኃይል በመቆጣጠር የኅብረተሰቡን #ደህንነት ለማስጠበቅ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

Via~fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በድጋሚ Alert‼️

√አክሱም ዩኒቨርሲቲ እና
√ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተፈጠረውን ችግር የሚመለከተው አካል ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው እና የተማሪዎችን #ደህንነት በአስቸኳይ እንዲያስጠብቅ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ጠይቀዋል።

ወጣት ተማሪዎች ከግጭት እና አለመግባባት የሚገኝ ትርፍ እንደሌለ በማወቅ ለሰላም ቅድሚያ ትሰጡ ዘንድ እንለምናችኃለን!!

ተጨማሪ መረጃዎችን አጣርቼ አደርሳለሁ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጨፌ_ኦሮሚያ

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የህዝብን #ሰላምና #ደህንነት ለማረጋገጥ የህግ የበላይነት ለማስከበር ትኩረት እንዲሰጥ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ አሳሰቡ።

አፈ ጉባዔዋ ዛሬ በአዳማ ከተማ የከልሉን ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ጉባዔ ሲከፍቱ እንዳስገነዘቡት ለሕግ የበላይነት መከበር ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ ይገባል፤ የህዝብ የመልካም አስተዳደርና የእኩልነት ጥያቄ መመለስ አማራጭ እንደሌለው ያስገነዘቡት አፈ ጉባዔዋ ፣ በክልሉ ያለው ችግር የህግ የበላይነት ጥስትና የህዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎችን ያለመመለስ ነው ብለዋል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ህዝቡ በትግሉ የተጎናፀፈውን ድልና ለውጥ ማደናቀፍ ሳይሆን ፣ የሰፈነውን የፖለቲካ ምህዳር በመጠቀም በምርጫ ተወዳድሮ ለማሸነፍ እንዲሰሩ አሳስበዋል። ጨፌው ችግሮቹን ለማስወገድና ለውጡን ለማስቀጠል ድጋፍ እንደሚያደርግም አፈ ጉባዔዋ አረጋግጠዋል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ምስራቅ_ዕዝ

የህብረተሰቡን #ሰላምና #ደህንነት የማስጠበቅ ስራን እንደሚያጠናክር የምስራቅ ዕዝ አስታወቀ። የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ስራን በተጠናከረ መልኩ እንደሚያስቀጥል በሀገር መከላከያ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ዘውዱ በላይ አስታወቁ።

ዋና አዛዡ ዛሬ በጅግጅጋ ገርባሳ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋም የመካከለኛ አመራሮች ስልጠና በተጀመረበት ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት የህብረተሰቡን ሰላም የሚያውኩ አካላትን በመከላከሉ ረገድ ሰራዊቱ ከነዋሪው ጋር በመሆን የሚጠበቅበትን ግዳጅ ተወጥቷል።

“በአሁኑ ወቅትም በቀጠናው የተለያዩ የጸብ አጫሪነትና የጸረ ሰላም ተግባር ሲፈጠሩ ሰራዊቱ ከክልል የጸጥታ አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሰላምን የማስከበር ስራ እያከናወነ ይገኛል” ብለዋል። በዚህም የቀጠናው የሰላም ሁኔታ ከዓመት ዓመት መሻሻል እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።

በቅርቡ በቀጠናው አንዳንድ ከተሞች በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ለማሰማት ዜጎች ወደ አደባባይ የወጡበትን አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን አጀንዳ ለማራመድ የሞከሩ ጥቂት ግለሰቦች እንደነበሩ አስታውሰዋል። ይህም ህብረተሰቡ በብሔርና በሃይማኖት ግጭት ውስጥ እንዲገባ ለማድረግ እንደነበረ ጠቅሰዋል።

ምንጭ፡- ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ዛሬ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት አንደኛ ዓመት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል። በዚህም መግለጫ የሰላም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ እንዲከበር ቁርጠኛ መሆኑን አሳውቋል። በአከራካሪ ቦታዎች ተፈናቃዮች እንዲመለሱና በህገመንግቱ መሰረት ህዝበ ውሳኔ እንዲደረግ አቋም ይዞ ተግባር ላይ እንዳለ አመልክቷል። የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ፤ መንግሥት በጦርነቱ የመጨረሻ…
" ለትግራይ ህዝብ ደህንነት የሚያሰጋ ነገር ከሌለ #ከመከላከያ_ሃይል ውጪ ያሉት የታጠቁ ሃይሎች ከትግራይ መሬት ከወጡ ትጥቅ ተሸክመን የምንኖርበት ምክንያት የለም  " - አቶ ጌታቸው ረዳ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አንደኛ አመት በማስመልከት ከ " ትግራይ ቴሌቪዥን " ጋር ሰፊ ቃለመጠይቅ አድረገዋል።

በዚህም ቃለመጠይቃቸው ፥ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የትግራይ ግዛትን የተቆጣጠሩት ኃይሎችን ማስወጣትና ፣ በትግራይ ግዛት በአማራ ሃይሎች የተመሰረቱት አስተዳደሮች የማፍረስ ጉዳይ የፌደራል መንግስት ግዴታዎች ናቸው ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ " የፕሪቶሪያ ውል የቶክስ ድምፅ የማቆም ስምምነት ነው " ያሉ ሲሆን  ከዚህ አኳያ ስኬታማ ውልና ስምምነት ነው ብለውታል።

በቃለመጠይቁ ላይ  ' ስለመሬት ይገባኛል ' ጉዳይም አንስተው የተናገሩት አቶ ጌታቸው " በአማራ ክልል በኩል ሃቅ የሚመስል የመሬት ይገባኛል ጥያቄ እንዳለ አስመስሎ የሚቀርብ አለ። በኔ አረዳድ እንደዛ አይነት ጥያቄ የለም ነው የምለው " ሲሉ ተደምጠዋል።

በኢትዮጵያ #የፌዴራል_መንግስት_ተደራዳሪዎች በኩል የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር አጨቃቂዎቹን የምእራብ ፣ ሰሜን ምእራብን ደቡብ ትግራይ ማስተዳደር የለበትም የሚሉ እንደነበሩ የክልሉ አስተዳዳሪ አንስተዋል።

አቶ ጌታቸው " ለትግራይ ህዝብ ደህንነት የሚያሰጋ ነገር ከሌለ #ከመከላከያ_ሃይል ውጪ ያሉት የታጠቁ ሃይሎች ከትግራይ መሬት ከወጡ ትጥቅ ተሸክመን የምንኖርበት ምክንያት የለም " ያሉ ሲሆን " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የፈረምነው የትግራይ መሬት ቆርሰን ለመስጠት ሳይሆን ፤ በህገ-መንግስት መሰረት ይፈታ ስለተባለ ነው " ብለዋል። 

ከተፈናቃዮች መመለስ ጋር በተያያዘም የትግራይ ምእራባዊና ደቡባዊ አከባቢዎች እንዲሁም ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የመመለስ ጉዳይ ቀደም ብሎ መፈፀም የነበረበት ተግባር እንደነበር ገልጸዋል።

" ይሁን እንጂ የፌደራል መንግስት ተፈናቃዮች እስከ ሰኔ 21/2015 ዓ.ም ወደ ቄያቸው ይመለሳሉ ብሎ የገባውን ቃል አልፈፀመም " ብለዋል።

የሰላም ስምምነት ትግበራው እንዲፋጠን ከአማራ ክልል አመራሮች ለመስራት ጥረት መደረጉን ያነሱት አቶ ጌታቸው " በፕሪቶሪያ ውል ላይ መደራደርና መገምገም ስለጀመሩ ዉይይቱ ተቋረጠ " ሲሉ ገልጸዋል።

ከዚህ ባለፈ በቃለመጠይቁ የሪፈረንደም ጉዳይም ተነስቶ ነበር።

አቶ ጌታቸው ሪፈረንደም ለማካሄድ የትግራይ ክልል ተወካዮች ምክር ቤት የግድ መቋቋም እንዳለበት ተናግረዋል።

" ከዚህ ውጭ የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሪፈረንደም የማካሄድ ህገ-መንግስታዊ ስልጣን የለውም " ሲሉ አሳውቀዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ፤ " የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የፕሪቶሪያ ውል እንዳይፈፀም እግር እየጎተተ ነው የሚለው ንግግር የተጋነነ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ፤ #የአፍሪካ_ህብረት ግጭት ዳግም እንዳይነሳ በማረጋገጥና ውሉ በተማሏ መንገድ እንዲፈፀም ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት አስገንዝበው " ሁሉም ልዩነቶች ሰላም ብቻ ነው መፈታት ያለባቸው ፣ ከጥይት ቶክስ #ለውይይት ቦታ መስጠት አለብን። ትግራይ የአውዳሚ ጦርነት መነሃሪያ እንድትሆን አንፈቅድም። " ብለዋል። 

አቶ ጌታቸው የጊዜያዊ አስተዳደራቸው ዋና ትኩረት የትግራይ ህዝብ #ደህንነት_ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸው ፤ " የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ለማደናቀፍ የሚንቀሳቀስ ማኛውም አካል ወይም ሃይል ተቀባይነት የለውም እንታገለዋለን። " ብለዋል።

በትላንትናው ዕለት የፌዴራል መንግሥት ባወጣው መግለጫ ፦

-  የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በአንዳንድ ነገሮች ወደኋላ እየቀረና የሰላም ስምምነቱን በተሟላ ሁኔታ ሳይፈፅም እያነከሰ ነው ሲል መተቸቱ ፤

- አከራካሪ የሚባሉ አካባቢዎችን በተመለከተ አቋም ወስዶ እንደሰራ እንደሆነ ፤ ክረምት ደርሶ የእርሻ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ተፈናቃዮች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱ፣ የአካባቢ ነዋሪዎች በመረጧቸው አካላት እንዲተዳደሩ፣ በመጨረሻም ደረጃ በደረጃ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ሕዝበ ውሳኔ እንዲደረግ አቅጣጫ መቀመጡን እና ይሄንንም ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደሚገኝ ማስታወቁ ፤

- የሰላም ስምምነቱ #በተሟላ_ሁኔታ_እንዲፈፀም ማድረግ ያለበትን ሁሉ ቢደረግም በዚያኛው ወገን እግር የመጎተት አዝማሚያ እንደሚታይ መግለፁ አይዘነጋም።
  
@tikvahethiopia
#ጅግጅጋ

የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ሙሴ ባሂ አብዲ ልኡካን ቡድናቸውን ይዘው ዛሬ ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ገብተዋል።

ፕሬዜዳንቱና ልኡካቸው ገራድ ዊልዋል ኤርፖርት ሲደርሱ የሱማሌ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ እና ሌሎች የክልሉ ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በሁለቱም በኩል ያሉ ባለስልጣናት የንግድ ትብብርን በተመለከተና በድንበር #የፀጥታ እና #ደህንነት ጉዳዮች (በሶማሌ ክልል እና በሶማሌላንድ) ዙሪያ ይመክራሉ ተብሏል።

የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ከትላንት በስቲያ በአዲስ አበባ ከተማ ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ፍላጎቷን እውን ያደርጋል የተባለለንትን የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው አይዘነጋም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከኤስአርቲቪ ሶማሊኛ ክፍል ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የባሕር በር ጉዳይ የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው " - ኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ምን አሉ ? " ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የቅንጦት ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው። ከሶማሌላንድ ጋር የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ ከዓላማው ውጪ የሆኑ የተሳሳቱ መረጃዎች ተሰራጭተዋል። የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የቅንጦት ሳይሆን…
#ኢትዮጵያ🇪🇹

" ... ለሶማሊያ በችግር ጊዜ ብዙ ድጋፍ ያላደረጉ #አንዳንድ_ተዋናዮች ራሳቸውን እንደ እውነተኛ ወዳጆቿ አድርገው ለማሳየት እየሞከሩ ነው " - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ምን አሉ ?

- ኢትዮጵያ ለሶማሊያ #ሰላም እና #ደህንነት ያላትን ቁርጠኝነት በውድ ልጆቿ #ደም እና #ላብ በግልፅ አሳይታለች።

- ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ድንበር ተጋርተው የሚኖሩ ጎረቤቶች ብቻ ሳይሆኑ የጋራ የሆነ ቋንቋ፣ ባህል እና ህዝብ የሚጋሩ ወንድማማች ሀገራት ናቸው።

- ኢትዮጵያ እና ሶማሊያን የሚያስተሳስሩ ጉዳዮች ጠንካራ ናቸው ፤ እጣ ፈንታችን የማይነጣጠል ነው።

- ከሶማሌላንድ ጋር የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ለኢትዮጵያ የንግድ ግንኙነት የሚሆን የባህር አገልግሎት የሚሰጥ የትብብር እና አጋርነት ስምምነት ነው። ስምምነቱ በየትኛውም ሀገር ላይ ሉዓላዊነትን የሚጥስ / የሚገዳደር / በግዳጅ የየትኛውንም ሀገር ሉዓላዊነት የሚረግጥ አይደለም።

- እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ለሶማሊያ በችግር ጊዜ ብዙ ድጋፍ ያላደረጉ አንዳንድ ተዋናዮች ራሳቸውን እንደ እውነተኛ ወዳጆቿ ለማሳየት እየሞከሩ ነው። ለዚህ ደግሞ ያነሳሳቸው ለሶማሊያ ያላቸው ወዳጅነት ሳይሆን #ለኢትዮጵያ_ያላቸው_ጥላቻ / የጠላትነት ስሜት መሆኑ ግልጽ ነው።

- እነዚህ ተዋናዮች አጀንዳቸው የአፍሪካ ቀንድ ሰላም ፣ መረጋጋት እና ደህንነት አይደለም። ሊዘሩ የፈለጉት #አለመግባባት እና #ትርምስን ነው። እየታየ ያለው ነገር ውጥረት የሚያባብስ እንዲሁም ደግሞ አጋጣሚውን ለመጠቀም ለሚፈልጉ የውጭ ተዋናዮች ፍላጎት ብቻ የሚያገለግል ነው።

- ኢትዮጵያ በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመስረተ ሁሉን አቀፍ ቀጠናዊ ትስስርን ለመፍጠር ከሁሉም ጎረቤቶቿ ጋር በትብብር መንፈስ ለመስራት እየጣረች ነው።

- ኢትዮጵያ ውጥረትን ከሚፈጥሩና ከሚያባብሱ መግለጫዎች፣ ንግግሮች እና ትርክቶች ይልቅ ቀጣይነት ያለው ውይይት ማድረግ የተሻለ አማራጭ እንደሆነ በጽኑ ታምናለች።

#AmbassadorRedwanHussien #X

@tikvahethiopia