TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ትግራይ

ትንሳኤ 70 እንደርታ የተሰኘው ፓርቲ ፤ በትግራይ ከ1 ሚሊዮን በላይ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ ሲል አሳውቋል።

ፓርቲው አዲስ አበባ ውስጥ በሰጠው መግለጫ፦
* የፕሪቶሪያው ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዲተገበር፣
* የዜጎች የዓመታት ስቃይ እንዲያበቃ፣
* የተፈጠሩ አለመግባባቶች ሕገ መንግሥታዊ በሆነ አግባብ እንዲፈቱ መንግሥት ግዴታውን እንዲወጣ አሳስቧል።

ፓርቲው የፕሪቶሪያው ስምምነት አንጻራዊ ሰላምና መረጋጋት የፈጠረ፣ ተስፋ የሰጠ ቢሆንም ስምምነቱ ሙሉ በሙሉ ባለመተግበሩ ምክንያት ከ1 ሚሊዮን በላይ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው በከፍተኛ ችግር ውስጥ ይገኛሉ ብሏል።

የመሬት ወረራ በተለይም በመቀሌ 70 እንደርታና ራያ አካባቢ በልማት ስም በማይረባና ያለምንም ካሳ ከሕዝቡ ቀምቶ ለጥቅመኞች የማስተላለፍ ስራ እየተሰራ መሆኑን ገልጾ ይህ ሳይውል ሳያድር እንዲቆም ብሏል።

ፓርቲው በመግለጫው በክልሉ ባለ የጸጥታ ችግር ፦
- ሕዝብ በሰላም ወጥቶ ለመግባት እንደሚቸገር፣
- የሕዝብና የመንግሥት ንብረት እንደሚዘረፍ ፣
- ሴቶችም በጠራራ ፀሐይ የሚደፈሩበት እና መሰል የወንጀል ድርጊቶች ሕዝቡን ከጦርነት ባልተናነሰ ከባድ ስቃይና መከራ ውስጥ እንደጣለው ገልጿል።

በክልሉ ሕዝቡ ባጋጠመው በድርቅ የማለቅ አደጋ በተጋረጠበት ጊዜ ሕወሓት ማለቂያ በሌለው ስብሰባ መቀመጡም ከሥልጣን ውጪ ሕዝባዊነት የሌለው ነው የሚል ትችትንም ፓርቲው ሰንዝሯል።

Via @thiqamediaeth
#ትግራይ

የመኪና አደጋ የአባትና ልጅ ህይወት ቀጠፈ።

ሦስት ተጓዦች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሷል።

ዛሬ ጠዋት ጥር  25/2016 ዓ.ም ከዓድዋ ወደ መቐለ 5 ሰዎች ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ባለቤትነቱ የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ የሆነ ትዮታ ዳብል ጋቢና መኪና ተምቤን ልዩ ቦታ " መነወ " በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ በውስጡ የነበሩ ሁሉም ተጓዦች ላይ የሞትና የጉዳት አደጋ አድርሷል።

በመኪናው የነበሩ የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ ማርኬቲንግ መምሪያ ሃላፊ ከነልጃቸው ህይወታቸው ሲያልፍ ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 3 ተጓዦች ደግም በመቐለ ዓይደር ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።

የራስ አሉላ አባነጋ የትውልድ ቦታ የሆነው " መነወ " ጠመዝማዛ ቦታና ተደጋጋሚ የመኪና አደጋ የሚከሰትበት በመሆኑ መንገዱ ትኩረት እንደሚያሻው አደጋው አስመልክተው የሚሰጡ የህዝብ አስተያየቶች ያመለክታሉ። 

የመኪና አደጋው መንስኤ ምን እንደሆነ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ፓሊስ ትራፊክ ገልጿል።

መረጃውን የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው የላከው።
                                    
@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ትግራይ

አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ በዛሬው እለት በወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያተኮረ ቃለመጠይቅ ለክልሉ ሚድያዎች ሰጥተው ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ተሳትፎውበት ከፌደራል መንግስት ጋር በአዲስ አበባ ስለተካሄደው ውይይትና ውጤት አስመልክቶ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።

አቶ ጌታቸው ፤ " ለፌደራል መንግስት የስራ አፈፃፀም ሪፓርት አቅርበናል። በአከባቢያችን ያለው ፓለቲካዊ ሁኔታ እጅግ ጥንቃቄ የሚሻ በመሆኑ እንደ አገር የውስጥ ሰላማችን መጠበቅና መንከባከብ እንደሚገባ ከፌደራል መንግስት ጋር መግባባት  ተደርሷል " ብለዋል።

ከፌደራል መንግስት በተካሄደው ውይይት በሃይል ስለተያዙ የትግራይ ግዛቶች መነሳቱ ያብራሩት ፕረዚደንቱ " በተለይ በምዕራባዊ ዞን  በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ሰፋሪዎች በሰፈሩበት፤ የፌደራል ተቋማት ዴሞግራፊ ለመቀየር በሚንቀሳቀሱበትና ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ባልተመለሱበት ፤ መፍረስ የሚገባቸው ሳይፈርሱ ፤ ህዝባችን ነፃ ባልወጣበት ሁኔታ ሪፈረንደም ማድረግ አይቻልም " ሲሉ ተናግረዋል።

በሚቀጥለው ወር መጋቢት የአፍሪካ ህብረት ፣ የተባበሩት መንግስታትና የአሜሪካ መንግስት ተወካዮች በተገኙት የፕሪቶሪያ ስምምነት አተገባበር ላይ ያተኮረ ውይይት ይካሄዳል ያሉት አቶ  ጌታቸው የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ለውይይቱ ስኬት የበኩሉ አስተዋፅኦ ለማድረግ ዝግጁ ነው ብለዋል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ህወሓት መልሶ እንደ ፓለቲካ ፓርቲ የመመዝገብ ጉዳይ የሚመለከት ጥያቄም ቀርቦላቸው ምላሽ ሰጥተዋል።

በዚህም፤ ከህወሓት የፓለቲካ ፓርቲነት ምዝገባ ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድን ውሳኔ የፌደራል መንግስት እንደማይደግፈው በመግለፅ ያለው የህግ ክፍተት በአስቸኳይ ታርሞ ምዝገባው እንዲፈፀም ጉዳዩ ወደ ፍትህ ሚኒስቴር ተመርቷል ብለዋል።

መረጃውን የትግራይ ሚድያዎችን ዋቢ አድርጎ ያዘጋጀድ የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
                 
@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
" ደማቁ የዓድዋ የድል መታሰብያ በዓልን በእርስ በርስ ግጭት ማቆሸሽ አይገባም " - ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መልእክት አስተለልፈዋል። ከ3 ዓመት ተኩል በኃላ በትግራይ ታሪካዊትዋ የዓድዋ ከተማ በመገኘት በዓሉን ለማክበር በመቻላቸው እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል። ፕረዚደንትዋ #እንባ_እየተናነቃቸው ያለፈውን አስከፊ ጦርነት በማስታወስ ፣ ተፈናቃዮች ያሉበትን አስከፊ ሁኔታ…
#ትግራይ

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ 😢

" ጠላት ሊወረን ሲመጣ የኢትዮጵያ ህዝብ በዘር ፣ በሃይማኖት ፣ በፆታ ሳይለያይ የመሪውን ዳግማዊ አጼ ሚኒሊክን ጥሪ በመቀበል ተሰባስቦ በመዝመት በነዚህ ተራሮች እና ኮረብታዎች ታሪክ እንዳልሰራ ሁሉ ለራሱ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ፤ ለአፍሪካ አህጉራችን እንዲሁም ለመላው የተጨቆነ ህዝብ ተስፋ የሰጠ ሳለ በዚህች መሬት፦
- ወንድም በወንድሙ ላይ ቃታ የሳበበት የተጋደለበት
- ንፁሃን የተገደሉበት
- ብዙዎች የተሰደዱበት
- በርካቶች በገዛ ሀገራቸው የተንከራተቱበት፣ የተፈናቀሉበት
- ንብረት የወደመበት
- #ሴቶች_የተደፈሩበት ሁኔታ ታሪክ ጅብዱ በተሰራበት ምድር እንዲያይ ያደረግነው። እነዚህ ተራራዎች ለዚህም እማኝ እንዲሆኑ ያደረግነው።

እነዚህ ተራሮች መናገር ቢችሉ እንዲነግሩን የምንፈልገው ግን የህዝባችንን ጀግንነት፣ ታሪክ ሰሪነት፣ አንድነት ነው፤ ምስክሮቻችን ናቸው።

በትግራይ ጦርነቱ እንደጀመረ ሰሞን መጥቼ ነበር። ከጦርነቱ ሁለት ወር በፊት እዚህ ነበርኩ። የጦርነት ደህና ገፅታ የለውም እጅግ አስከፊውን ግን አላየሁም ብዬ ነው የማስበው። "

#TikvahFamilyAdawa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ 😢 ፦ " ጠላት ሊወረን ሲመጣ የኢትዮጵያ ህዝብ በዘር ፣ በሃይማኖት ፣ በፆታ ሳይለያይ የመሪውን ዳግማዊ አጼ ሚኒሊክን ጥሪ በመቀበል ተሰባስቦ በመዝመት በነዚህ ተራሮች እና ኮረብታዎች ታሪክ እንዳልሰራ ሁሉ ለራሱ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ፤ ለአፍሪካ አህጉራችን እንዲሁም ለመላው የተጨቆነ ህዝብ ተስፋ የሰጠ ሳለ በዚህች መሬት፦ - ወንድም በወንድሙ ላይ ቃታ የሳበበት የተጋደለበት…
#ትግራይ

" ' ያንቺ እቃ ብቻዬን ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን 2 ወንድ ልጆቼን ይመልስልኛል ወይ ? ' ነው ያለችኝ ! " - ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በታሪካዊቷ ዓድዋ ከተማ በነበረው የዓድዋ ድል በዓል  ላይ እምባ እየተናነቃቸው 😭 ንግግር አድርገው ነበር።

እሳቸው በእንባ ንግግር ሲያደርጉ የበዓሉ ታዳሚ ህዝብ ከፍተኛ የሀዘን ስሜቱ ከፊቱ ይነበብ እንደነበር በስፍራው የነበረው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ምን አሉ ?

" ዛሬ ወደ ትግራይ ስመለስ በህሊናዬ የሚመጡብኝ ብዙ ትዝታዎች አሉብኝ።

ይቅርታ አድርጉልኝና አጋጣሚውን ተጠቅሜ ማንሳት እፈልጋለሁ።

በትምህርት ቤት ውስጥ ተጠልለው ከነበሩ ወገኖች መካከል አንዷ ፈንጠር ብላ የተቀመጠች አንዲት ሴት ለማነጋገር ሞክሬ ነበር።

በተፈናቃዮች ካምፕ ጉብኝት ልብን የሚሰብር  ነው። ከቤት ንብረታቸው ወጥተው ፣ ክብራቸውን አጥተው ቁጭ ብለው ጉብኝት .. እኛ ደግሞ እንመጣለን ልናያቸው።

ታዲያ ያችን ሴት ጠጋ ብዬ ሳነጋግራት፤ በጥሩ አልመለሰችልኝም። ጥቂት ያመጣሁትን እቃ እንድታከፋፍልልኝ ነበር ልጠይቃት የነበረው ' ያንቺን እቃ አልፈልግም ' አለችኝ።

በሆስፒታል እና በመጠለያ ጣቢያቸው ሄጄ ያየዋቸዋን ሴቶች በእጅጉ አስባቸዋለሁ። እቺን ሴትዮ ለምንድነው የምትመልሽልኝ ስላት ' ያንቺ እቃ ብቻዬን ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን ሁለት ወንድ ልጆቼን ይመልስልኛል ወይ ? ' ነው ያለችኝ መልስ የለኝም ፤ አይመልስም ብቻ ነው ያልኳት።

ጦርነቱ ተዛምቶ በአፋር ክልል ሰመራ ሆስፒታል ህክምና ላይ የነበሩ የተማረኩ የህወሓት ታጋይ ሴቶችን አግኝቻቸዋለሁ ሳናግራቸው ያሉኝ ከልቤ አይጠፋም ፤ ቦታቸው እዛ አልነበራም ትምህርት ቤት ነው።

ያሉኝ ' እኛ መመለስ የምንፈልገው ወደ ትምህርት ቤት ነው ' ይሄንን ወግቼ ያንን አሸንፌ የሚል ዓላማ አልነበራቸውም። በክፍላቸው ግርግዳ ላይ የፃፉት የለጠፉት የአፋር ህዝብ እንዴት ደግ እንደሆነ ነው። ኢትዮጵያዊ ለኢትዮጵያዊ እንዴት እንደሚረዳዳ ነው።

ሌሎችም አሉ ብዙ እርጉዝ ሆነው ሶስት ልጅ ወልደው ሲንከራተቱ የነበሩ ... ለማንኛውም ብዙ መንከራተት ነበር።

ዛሬ እዚህ ቆሜ የትግራይ እናቶች ያሳለፉትን #ሰቆቃ በእውነቱ እረዳለሁ ለማለት ነው ይሄን ሁሉ የምናገረው። እግዚአብሔር ብርታቱን ይስጥዎ !!

ዞሮ ዞሮ የማንኛውም ግጭት መጨረሻው ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ የሰላም ስምምነት መፈረሙ አይቀርምና ይህ ሳይሆን ተጨራርሰን ተጨካክነን ፣ ዘርና ሃይማኖት መለያያ አድርገን ሃይማኖቶችን ከፋፍለን ሳይሆን በቅድሚያ መከላከል እንዳለብን መገንዘብ አለብን።

የዓድዋ ባለቤቶች እንዳልሆንን ገፅታችንን አጉድፈን አበላሽተናል። "

#TikvahFamilyAdawa

@tikvahethiopia
#ትግራይ

"...መግለጫው የኤርትራ ጦር የተለያዩ አካባቢዎችን በኃይል ይዞ እንደሚገኝ ያመላከተ ነው " - አቶ ረዳኢ ኃለፎም

የትግራይ ጦርነት መቀስቀስን ተከትሎ የኤርትራ ጦር  የኢትዮጵያን መሬት በኃይል ተቆጣጥሮ እንደሚገኝ ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላም ቢሆን መሬቱን ለቆ እንዳልወጣ የትግራይ ጊዜዊ አስተዳደርን ጨምሮ ሀገራትና ተቋም በተደጋጋሚ መግለፃቸው ይታወሳል።

በቅርቡ እንግሊዝ የሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲ አውጥቶት በነበረ አንድ መግለጫ የኤርትራ ጦር በትግራይ ግዛት ውስጥ እንደሌለ፣ ባድመም ጨምሮ ሌሎችም አከባቢዎች ህወሓት በህገወጥ መንገድ ለሁለት አስርት ዓመታት ይዟቸው የቆዩ የኤርትራ ሉዓላዊ ግዛቶች ናቸው ብሏል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኤርትራ ጦር በምስራቃዊና ሰሜን ምዕራብ የትግራይ አካባቢዎች ጨምሮ በተለያየ አካባቢ እንዳለ በተደጋጋሚ በመግለፅ በኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ያሉ የውጭ ኃይሎችን የማስወጣትና ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው የመመለስ ኃላፊነት የፌዴራል መንግሥት መሆኑን ገልጿል።

የትግራይ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ረዳዒ ኃለፎም በኤርትራ መግለጫ ዙሪያ ምን አሉ ?

- የኤርትራው ኤምባሲ መግለጫ የኤርትራ ጦር የተለያዩ አካባቢዎችን በኃይል ይዞ እንደሚገኝ አመላካች ነው።

- ከአልጀርስ ስምምነት አፈፃፀምናና ሌሎች የድሮ በ90ዎቹ የሚነሱ ጥያቄዎች ጉዳዮች ካሉ በህጋዊ መንገድ በዓለም አቀፍ ስርዓት እንዲፈፀም ማድረግ እንጂ ጉልበት አለኝ ብሎ በጉልበት የያዛቸውን አካባቢዎች " የኔ ናቸው " የሚል መግለጫ መስጠቱ ተቀባይነት የለውም።

- ከአልጀርስ ስምምነት አፈፃፀም ጋር በተያያዘ በኃይል የተወረረው መሬት ከተመለሰ በኃላ በህጋዊ መንገድ ሊፈፀም የሚችል ነው።

- መግለጫው አንድ ውለታ የዋለው በኃይል የያዧቸው አካባቢዎች እንዳሉ ገልጸ " በኃይል የያዝኩት የኔ ነው " የሚል መስፋፋት ነው። " የለሁም " አላለም መኖሩን አምኗል ይሄ የያዘው ቦታ ነው በጉልበት ስለያዝኩት " የኔ ነው " እያለ ያለው ይሄ በፍፁም ተቀባይነት የለውም።

- የፌዴራል መንግሥት ማስወጣት አለበት እነዚህን ኃይሎች ሁሌም እያልን ነው። ማለት ያለበትን ማለትም አለበት። ኃላፊነቱን መወጣት አለበት።

- በትግራይ ከኤርትራ ጦር በተጨማሪ የአማራ ክልል ታጣቂዎችም አሉ። ይህ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የሚፃረር በትግራይ ያለውን አሳሳቢ የተፈናቃዮች ችግር እንዳይፈታ ያደረገ ነው።

- እንዚህ ኃይሎች እያሉ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ ማድረግና ማቋቋም አይቻልም። ከሞት አምልጠው የመጡ ገዳዮች ወዳሉበት እንዴት ነው የሚመለሱት ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የዶቼቨለ ሬድዮ መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
#ትግራይ

በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ውድመት እንደደረሰበት የገለጸልን የዓዲግራት ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሃገረ ስብከት ተራድኦ ድርጅት ለ364 ሺህ 311 የጦርነት ተፈናቃዮች የድርቅና ረሃብ ተጠቂዎች እርዳት በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገለፀ።

ከፓለቲካ ነፃ መሆኑ የሚጠቅሰው የካቶሊካዊት ቤተክርስትያን የተራድኦ ድርጅት በትግራይ ጦርነት ጊዜ ለሰብአዊ አገልግሎት ስራ ሲጠቅምባቸው  የነበሩ 14 መኪኖች መዘረፉ አስታውሶ ዘራፊዎቹ ለሰብአዊ አገልግሎት መኪኖቹ እንዲመልሱ " በፈጣሪ ስም እማፀናለሁ " ብሏል።

የምግባረ ሰናይ ድርጅቲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተወልደ ሃይለስላሴ ወደ ዓዲግራት ለተጓዘው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በሰጡት ቃለመጠይቅ እንደገለፁት ፤ ምግባረ ሰናይ ድርጅቱ ባለፈው 2023 የፈረንጆች ዓመት ብቻ ከ433 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለ364 ሺህ 311 ህዝብ አስቸኳይ እርዳታ አቅርበዋል።

ከተረጂዎቹ 50 በመቶ በላይ ሴቶች መሆናቸው ያብራሩት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ እገዛው በመላ ትግራይና ዓፋር ዞን 2 እንደተከናወነ አብራርተዋል።

ያንብቡ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-03-09

#TikvahFamilyAdigrat

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ጥያቄ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምን ነበር ? ከትግራይ ወደ አ/አ የመጡ የማህበረሰቡ ተወካዮችና እዚህም ያሉ ተወላጆች ከጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ የትግራይ ህዝብ ከማንም ህዝብ ጋር  መጋጨት እንደማይፈልግ ገልጸው ፓለቲከኞችም ልጓም ማበጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፅንኦት በጦርነቱ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው…
#ትግራይ
 
የትግራይ የማህበረሰብ ተወካዮች ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር በመከሩበት ወቅት የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ አባላት ከጦርነት በፊት ለንግድና ኢንቨስትመንት ማስፋፍያ የወሰዱት የብድር ወለድ ፣ የወለድ ወለድና ቅጣት እንዲነሳ የሚል ጥያቄ ማንሳታቸው ይታወሳል።

ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ምን የተደረሰ ውሳኔ አለ ? ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ፤ የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ ከፍተኛ አመራሮችን አነጋግሯል።

አመራሮቹ፤ ጠቅላይ ሚንስትሩ በሰጡት ትእዛዝ እና ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት ከጦርነቱ በፊት የተወሰደው የብድር ወለድ ፣ የወለድ ወለድና ቅጣት በሚመለከት አጥንቶ በ10 ቀናት ውስጥ የውሳኔ ሃሳብ የሚያቀርብ አገር አቀፍ ኮሚቴ ተቋቁሞዋል ብለዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በሰጡት ትእዛዝና ባስቀመጡት አቅጣጫ መሰረት ፤ በጠቅላይ ሚንስትሩ የኢኮኖሚ አማካሪ አቶ ግርማ ብሩ የሚመራ ፦
- የመከላከያ ሚንስትሩ ዶክተር አብራሃም በላይ 
- የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ
- የብሄራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ
- የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ 
- የጠቅላይ ሚንስትሩ የኢኮኖሚ አማካሪ አቶ ተክልወለድ አጥናፉ 
- የትግራይ የማህበረሰብ ንግድ ከፍተኛ አመራሮች በአባልነት ያካተተ አገር አቀፍ ኮሚቴ ተቋቁሞ በመስራት ላይ ይገኛል ሲሉ ገልጸዋል።

አገር አቀፍ ኮሚቴው ፦
ከጦርነቱ በፊት የተወሰደው በድር ምን ያህል እንደሆነ ?
የብድሩ ወለድ የወለድ ወለድና ቅጣት ስንት እንደሆነ ? አጥንቶ ያቀርባል ያሉት የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ ከፍተኛ አመራሮች ፤ በጦርነቱ የወደመ የንግድና የኢንቨስትመንት የገንዘብ መጠን ሳይጨምር የወለድ ፣ የወለድ ወለድና ቅጣት ብቻ እስከ 60 ቢሊዮን ብር እንዲሰረዝ በጥናት ያቀርባል ብለዋል።
 
ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት ለብሄራዊ ባንክና ገንዘብ ሚንስቴር ጨምሮ ጥያቄው ለሚመለከታቸው ከፍተኛ የፌደራል የሚንስቴር መ/ቤቶች በተደጋጋሚ መቅረቡም አስታውሰው ጠቅላይ ሚንስትሩ በሰጡት ትእዛዝና ባስቀመጡት አቅጣጫ ጥናቱ አስከ መጋቢት 20/2016 ዓ.ም ተጠናቅቆ ቀርቦ እንደ ጡረታው የመጨረሻ ውሳኔ ያገኛል ብለው እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

መረጃው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
                        
@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ጥያቄ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምን ነበር ? ከትግራይ ወደ አ/አ የመጡ የማህበረሰቡ ተወካዮችና እዚህም ያሉ ተወላጆች ከጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ የትግራይ ህዝብ ከማንም ህዝብ ጋር  መጋጨት እንደማይፈልግ ገልጸው ፓለቲከኞችም ልጓም ማበጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፅንኦት በጦርነቱ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው…
#ትግራይ #አማራ

" እኔ #ከሪፈረንደም ውጭ መፍትሄ ያለ አይመስለኝም " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በትግራይ እና አማራ በኩል ላለው ችግር " ዘላቂው መፍትሄ ህዝባዊ ሪፈረንደም " ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ጠቅለይ ሚኒስትሩ ፥ ከዚህ ቀደምም በትግራይ እና አማራ ላለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ " ህዝቡ ህዝበ ውሳኔ ሲያደርግ " እንደሆነ በተደጋጋሚ እንደተናገሩት ጠቁመዋል።

" የሆነን ሰዎች እዛ ተቀምጠው ፣ እዛ ተቀምጠው ሲናገሩ አይደለም። ህዝቡን መልሰን ህጋዊ በሆነ መንገድ ዓለም እያየው ሪፈረንደም አድርገው ወደሚፈልጉት ቢጠቃለሉ ከዚያ በኃላ ለጥያቄ አይመችም " ብለዋል።

" አሁን ላይ ግን ሪፈረንደም የሚባል ነገር አይፈልገም " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " እራሱ ነዋሪው ሳይሆን ሌላ ሰው ነው መወሰን የሚፈልገው እዚህ እየመጣ ጥያቄ ያቀርባል ' አልተፈታም ' እያለ እኔ ደግሞ አቅጣጫ አስቀምጫለሁ እንዲፈታ " ሲሉ ተናግረዋል።

እሳቸው ያስቀመጡት አቅጣጫ በመጀመሪያ የተፈናቀውለው ህዝብ እንዲመለስ ከዛ ህዝቡ እንዲወስን (ሪፈረንደም እንዲያደርግ) መሆኑን ተናግረዋል።

" ሪፈረንደም ከተደረገ በኃላ ህዝቡ የወሰነውን እናክብርለት ፤ እኔ እዚህ ሆኜ መወሰን አልችልም " ብለዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በትግራይ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን እና በአማራ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን በጣም የተራራቀ ነው ምንም የተቀራረበ አይደለም ለማቀራረብ የሚቻለው ህዝቡ እራሱ ሲወስን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ (ሪፈረንደም) ውጭ ለጊዜው ሌላ #መፍትሄ ያለ እንደማይመስላቸውም ገልጸዋል።

" ህዝቡ እንዲወስን ከተደረገ የተረጋጋ አካባቢ ይፈጠራል " ብለዋል።

" እያባላን ያለው የቦታ ችግር አይደለም እኛን የሚያባላን እንደ ንብ ቀፎ ውስጣችን የሚጮኸው ጩኸት ነው እንጂ ሀገሩማ በቂ ነው ቢሰራበት ቦታዎቹ ክፍት ናቸው መንገድ የላቸው ፣ ቤት የላቸው ክፍት ናቸው ' አልገባሁም ገባሁ ' እንጨቃጨካለን እንጂ የቦታ ችግር የለም ቦታው ላይ የሚስራት ችግር ነው የሚያጨቃጭቀን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ታዳጊዋ የት ናት ? በትግራይ ዓድዋ ከተማ የታገተችውና ለማስለቀቅ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት ታዳጊዋ ማህሌት ተኽላይ እስካሁን እንዳልተገኘች እና ድምጿም እንዳልተሰማ ቤተሰቦቿ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። እገታው ከተፈፀመ 7 ቀናት ሆኖታል። የ16 አመቷ ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ መጋቢት 11 ባጃጅ ይዘው በመጡ ' ማንነታቸው አልታወቀም ' በተባሉ ሰዎች ታፍና ከተወሰደች በኃላ በራሷ ስልክ ለአባቷ…
#ትግራይ

ታጋቹ ከ3 ወር መሰወር በኃላ የማስለቀቂያ ክፍያ ተጠየቀባቸው። 

"አጋቾች ነን" ባዮች የጠየቁት ገንዘብ በ1 ሳምንት ጊዜ ካልተከፈላቸው ታጋቹን እንደሚገድሉት እንደዛቱ የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

እገታው እንዴት እና መቼ ተፈፀመ ? 

የሰዎች እገታ ከህፃናት አልፎ እድሜያቸው በገፉት ላይም በመቀጠል በህብረተሰቡ ውስጥ ቀውስን ማቀጣጠል መቀጠሉ እየተገለፀ ይገኛል።

ታጋቹ ሃለቃ ኣከቦም መሓሪ ኣባይ በትግራይ ፤ ምስራቃዊ ዞን ጉለመኻዳ ወረዳ የፍረዳሽም ቀበሌ ነዋሪ ናቸው።

ከ3 ወራት በፊት ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ / ም ከቤት እንደወጡ አለመመለሳቸው ያሳሰባቸው ቤተሰቦቻቸው ወደ አቅራቢያ ፓሊስ አመልክተው ራሳቸውንና ሌላውን በማሳተፍ በፍለጋ ቢታክቱም ሳይሳካላቸው ቆይተዋል።

የታጋቹ ሃለቃ ኣኮቦም ቤተሰቦች በከፍተኛ የተስፋ መቁረጥና የሀዘን ስሜት ውስጥ ባሉበት ሁኔታ ታድያ መጋቢት 15/2016 ዓ.ም የሞባይል ስልክ ጥሪ ይደርሳቸዋል።

የታጋቹ ቤተሰቦች የተደወለላቸው የሞባይል ስልክ ቁጥር የወንድማቸው ሃለቃ ኣከቦም ቢሆንም  ሞባይሉን ሲያነሱት የሰሙት ድምፅ ግን ከዛ በፊት ሰምተውት አያውቁም።

ይህ ማንነቱ ያልታወቀው ደዋይ በወንድማቸው የሞባይል ቁጥር በመጠቀም ፥ "...ወንድማችሁ ኣከቦም በህይወት ለማትረፍና በአካል ለማግኘት ከፈለጋችሁ 350 ሺህ ብር ክፈሉ። " የሚል ትዕዛዝ ያስተለልፋል።

የታጋቹ ወንድም ግደይ መሓሪ አባይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል በሰጠው ቃል ፥ ስልክ ደዋዩ ከአጋቾቹ አንዱ መሆኑን በማሳወቅ የተጠየቀው ብር እንዲከፍሉ የአንድ (1) ሳምንት ጊዜ ብቻ እንደሰጣቸውና ብሩን ካልከፈሉ ወንድማቸውን እንደሚገድሉባቸው እንደ ዛተ ተናግረዋል።

የታጋቹ ሃለቃ ኣከቦም መሓሪ ኣባይ በማህበራዊ ሚድያ ተሰራጭቶ ያነበቡ አስተያየት ሰጪዎች ፦ " ይህንን ያልተለመደና መጤ የእገታ ተግባር እጅግ አሳስቦናል !፤ ይህ እገታ ማቆምያው የት ይሆን ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

" አስከፊው ተግባር ወደየ ቤታችን ከመድረሱ በፊት መፍትሄ ያሻዋል " ያሉ አስተያየት ሰጪዎች " ከህግ አካላት በቅንጅት መስራት ሲቻል ችግሩ መፍትሄ ሊያገኝ ይችላል " ብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዓድዋ ከተማ መጋቢት 11/2016 ዓ.ም የታገተችውና እንድትለቀቅ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ 12 ቀናት ቢያልፋትም ደብዛዋ ሊገኝ አልቻለም።

መረጃው የተዘጋጀው በመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

ፎቶ 1 ፦ ሃለቃ ኣከቦም መሓሪ ኣባይ
ፎቶ 2 ፦ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ

@tikvahethiopia