#ትግራይ

በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ውድመት እንደደረሰበት የገለጸልን የዓዲግራት ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሃገረ ስብከት ተራድኦ ድርጅት ለ364 ሺህ 311 የጦርነት ተፈናቃዮች የድርቅና ረሃብ ተጠቂዎች እርዳት በማቅረብ ላይ እንደሚገኝ ገለፀ።

ከፓለቲካ ነፃ መሆኑ የሚጠቅሰው የካቶሊካዊት ቤተክርስትያን የተራድኦ ድርጅት በትግራይ ጦርነት ጊዜ ለሰብአዊ አገልግሎት ስራ ሲጠቅምባቸው  የነበሩ 14 መኪኖች መዘረፉ አስታውሶ ዘራፊዎቹ ለሰብአዊ አገልግሎት መኪኖቹ እንዲመልሱ " በፈጣሪ ስም እማፀናለሁ " ብሏል።

የምግባረ ሰናይ ድርጅቲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ተወልደ ሃይለስላሴ ወደ ዓዲግራት ለተጓዘው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል በሰጡት ቃለመጠይቅ እንደገለፁት ፤ ምግባረ ሰናይ ድርጅቱ ባለፈው 2023 የፈረንጆች ዓመት ብቻ ከ433 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለ364 ሺህ 311 ህዝብ አስቸኳይ እርዳታ አቅርበዋል።

ከተረጂዎቹ 50 በመቶ በላይ ሴቶች መሆናቸው ያብራሩት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ እገዛው በመላ ትግራይና ዓፋር ዞን 2 እንደተከናወነ አብራርተዋል።

ያንብቡ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-03-09

#TikvahFamilyAdigrat

@tikvahethiopia