TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Hawassa

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባለፈው አርብ ሀዋሳ ከተማ ላይ ተፈፅሟል ስለተባለ አንድ የወንጀል ድርጊት ጥቆማ ደርሶት ተመልክቷል።

ጉዳዩን በተመለከተ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስን እንዲሁም ድርጊቱ ተፈፅሞበታል የተባለውን ክ/ከተማ ፖሊስ ኃላፊዎችን አነጋግሯል።

👉 ተጎጂ የራስሰው ገዛኸኝ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ፦

" ሀዋሳ ላይ ቀን ነው በሚባልበት 12:30 የምናሽከረክረውን ' ላንድሮቨር ' መኪና ባስቆሙ በተደራጁ ዘራፊዎች ተዘርፈናል ፤ በመሃል ከተማ በሳንጃም የግድያ ሙከራም ተደርጎብናል። "

👉 የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦

" ... ' ችግሩ ተፈጽሞብን ፍትህ አጣን ' የሚሉ አካላት በየትኛዉም ጊዜ ማመልከት ቢፈልጉ ቢሮዬም ሆነ ስልኬ ክፍት ነው። ብዙዎች ሰላሟን የሚመሰክሩላትን ሀዋሳ ከተማን በትንሹ መገመት አግባብ አይደለም "

👉 የታቦር ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ኢንስፔክተር ወንድዬ ከበደን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦

" . . . ተጎጅዎች ' በተደራጀ ዝርፊያ ጥቃት ተፈጽሞብናል ' የሚሉት የተሳሳተ ነው። በወቅቱ ' ግጭት ውስጥ የነበሩ ወጣቶች ' ውስጥ በመግባታቸዉ ለስርቆት ተዳርገዉ ሊሆን ይችል እንደሆነ እንጅ በከተማዉ የተባለዉ አይነት ዝርፊያ በፖሊስና በማህበረሰቡ ትብብር ታሪክ የሆነ ጉዳይ ነው። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Hawassa ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባለፈው አርብ ሀዋሳ ከተማ ላይ ተፈፅሟል ስለተባለ አንድ የወንጀል ድርጊት ጥቆማ ደርሶት ተመልክቷል። ጉዳዩን በተመለከተ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስን እንዲሁም ድርጊቱ ተፈፅሞበታል የተባለውን ክ/ከተማ ፖሊስ ኃላፊዎችን አነጋግሯል። 👉 ተጎጂ የራስሰው ገዛኸኝ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ፦ " ሀዋሳ ላይ ቀን ነው በሚባልበት 12:30 የምናሽከረክረውን ' ላንድሮቨር…
#Hawassa

የራስሰው ገዛኸኝ የተባሉ ግለሰብ ሀዋሳ ላይ የተደራጀ ዝርፊያ እና ሳንጃ በማውጣት የግድያ ሙከራ እንደተፈፀመባቸው በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፅፈው አሰራጭተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ይህ መልዕክት በውስጥ ደርሶት ተመልክቷል። የሀዋሳ ፖሊስንም ስለጉዳዩ ደውሎ ጠይቋል።

" በሀዋሳ ከተማ ላይ የተደራጀ የዝርፊያ እና የግድያ ሙከራ ተፈፅሞብናል " ያሉት የራሰው ገዛኸኝ ፅፈው ባሰራጩት ፅሁፍ መሰረት ፦

- ድርጊቱ የተፈፀመው ሀዋሳ፣ በተለምዶ ከአቶቴ ወደ ፉራ በሚወስደው መንገድ " ቦሌ መንደር " አካባቢ በሚገኘው የትራፊክ መብራት ጋር ነው።

- ቀኑ 12/04/2016 ዕለተ #አርብ ከምሽቱ 12:30 ላይ ነው።

- ሲያሽከረክሩት የነበረው ላንድ ሮቨር መኪና ሲሆን ውስጥ እንግዶቻቸው ከሆኑ 3 የመንግስት አካላት ጋር ሆነው ሲጓዙ ነበር።

- በተለምዶ " ቦሌ መንገደር  " የትራፊክ መብራቱ ጋር ሲደርሱ የሚያሽከረክሩት መኪና ከጎን በኩል በከፍተኛ ምት ይመታባቸዋል። አደጋ ያደረሱ ስለመሰላቸው መኪናውን ዳር በማስያዝ ያቆማሉ።

- በመኪናው ውስጥ ከነበሩት አንዱ ከመኪና ፈጥነው በመውረድ የተመታውን መኪና ዙሪያውን ቢመለከቱም የደረሰ አደጋ የለም። ግን ሰዎች ተሰብስበዋል።

- የወረደው ሰው ከመኪናው ኃላ የተሰበሰቡ ወጣቶች የደረሰውን ግጭት ምንነት እየጠየቃቸው በነበረበት ወቅት የራስሰው ገዛኸኝም ከመኪናቸው ወርደው ወደ ወጣቶቹ በመሄድ ምን ተፈጠረ ? ማለት ጥያቄ ይጀምራሉ።

- በዚህ ሁኔታ አስፓልቱ ዳር ከሚገኝ 2 ፑል ቤት አንድ ግሮሰሪ ተጨማሪ ወጣቶች ወጥተው ከበባ ያደርጋሉ፤ ወዲያው አንድ ወጣት በተለምዶ በአከባቢው አጠራር " ባንጋ " የተባለ የሚጠራውን ሳንጃ ይዞ ማሳደድ ይጀምራል።

- በተፈጠረው ሁኔታው #ተደናገጠው ቢያፈገፍጉም ወጣቱ ሊተዋቸው ባለመቻሉ ወደ መኪናው ለመግባት ሲሞክሩ እዛው ጋር የነበሩት ሌሎች ወጣቶች በሩን እንዳይገቡ ይይዙታል።

- ሁኔታው በተደራጀ መልኩ #ዘረፋ መሆኑ ስለገባቸው በሳንጃው ላለመወጋት ይሸሻሉ።

- በዚህ መካከል ከመኪና ውስጥ ያልወረዱት ሰዎች መኪናውን ሎክ ለማድረግ ቢሞክሩም ሌሎች ወጣቶች ከኃላ በር በመክፈት፦
* ላፕቶፕ የያዘ ሻንጣ
* ከአንድ ፕሮግራም ቀረፃ እየተመለሱ በመሆኑ ብላክ ማጂክ ካሜራ ፣
* መቅረፀ ድምፅ የያዘ ቦርሳ ይዘው ተሰውረዋል።

- አካባቢው ላይ የነበሩ ሰዎች ዘራፊዎቹ ከአከባቢው መሰወራቸውን ተመልክተው " ስፍራውን ቶሎ ለቃችሁ ካልሄዳችሁ አሁን ከመጡ #ይገሏችኋል " በማለት አከባቢውን ለቀው እንዲሸሹ ያስፈራሯቸዋል።

- በተጠና ሁኔታ ከፍተኛ የሆነ የዘረፋ ኦፕሬሽን በመሆኑ ከአከባቢው ለመሄድ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተው የፓሊስ አካል እስኪመጣ ጠበቁ።

- በዚህ መካከል አንድ የፓሊስ አባል ይመጣል። ቀርቦ ምንድነው ? ሲል ይጠይቃል። እነሱም የደረሰባቸውን የዘረፋ ወንጀልና የግድያ ሙከራ አስረድተው የህግ ከለላ ቢጠይቁም። ፓሊሱ " በቃ አሁን ከዚህ ሂዱ ልጆቹ ከላልታወቁ ምን ማድረግ ይቻላል ? " በማለት መልሷል።

- የፖሊስ አባሉ ቢያንስ እንኳን #ፓትሮል ደውሎ ኃይል እንዲያስጨምርላቸው ቢነግሩትም ፤ " እኔ የናንተ ጠባቂም ተላላኪም አይደለሁም " የሚል ምላሽ እንደሰጣቸው ገልጸዋል።

- ወደ አንድ የሲዳማ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣን ዘንድ ደውለውም እንዲደርሱላቸው ፤  የደረሰባቸውን በደል ቢያስረዱም ከባለስልጣኑ ዘንድ ምንም አይነት እርዳታ አላገኙም።

- ወደ ተለያዩ የህግ አካላት በመደወል #ከ40_ደቂቃ በኃላ አንድ የፓሊስ ፓትሮል ሊመጣ ችሏል።

- የመጡት የፖሊስ አባላት ችግሩን ለመስማት የሞከሩ ሲሆን " የዘራፊዎችን ማንነት እና ስም " ከተፈራፊዎች ይጠይቃሉ። እነሱም መንገደኛ በመሆናቸው ገልጸው የዘራፊዎቹን ማንነት በስምና በአድራሻ ለይቶ ለፓሊስ መናገር የሚችሉበት መንገድ ስላልገባቸው ቢያንስ የተወሱ ወጣቶች የወጡበትን ግሮሰሪ እና ፑል ቤት አሳዩ።

- ከፍተኛ #ክርክር እና አለመግባባት ከተፈጠረ በኃላ የፖሊስ አባላቱ የተፈፀመውን ነገር የዕለት መዝገብ ላይ እንዲያስመዘግቡ በማለት ወደ ታቦር ክፍለ ከተማ ፓሊስ ማዘዣ ጣቢያ እንዲሄዱ አድርገዋል።

- ፖሊስ " የፑል ቤቱ ባለቤቶች  " አንዳንድ ነገር ሲናገሩ በመስማታቸው አስረዋቸዋል። ነገር ግን ዋናዎቹ የተደራጁትን የዘራፊ ቡድኖች የያዘም ሆነ በወቅቱ ለመከታተል የሞከረ አካል የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን መልዕክት ከተመለከተ በኃላ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስን ለማነጋገር ጥረት አድርጓል።

የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ፤ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ አሁን ላይ በከተማዋ ዉስጥ በተሰሩ በርካታ ስራዎች በኢትዮጵያ ካሉ ከተሞች በጅጉ የተሻለ ሰላም ያላት ከተማ ሀዋሳ መሆኗን ጠቅሰዋል።

ተፈፅሟል የተባለውን ጉዳይ በሶሻል ሚዲያ ሲያዩት #ማዘናቸዉን ገልጸዋል።

ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ፤ ችግር ተፈጥሮ ከሆነ በተዋረድ ለሚመለከተዉ አካል ማቅረብ እንደሚቻልና በተለይ እንዲህ ያለዉን ጉዳይ እንኳን ፖሊስ የትኛዉም የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ከማስቆም ወደኋላ እንደማይል ገለጸዋል።

አሁንም " ችግሩ ተፈጽሞብን ፍትህ አጣን " የሚሉ አካላት በየትኛዉም ጊዜ ማመልከት ቢፈልጉ ቢሯቸዉም ሆነ ስልካቸዉ ክፍት መሆኑን በመግለጽ ብዙዎች ሰላሟን የሚመሰክሩላትን ሀዋሳ ከተማን በትንሹ መገመት አግባብ አይደለም ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህን ጉዳይ በተመለከተ ተጎጅዎች እንዲያመለክቱና ቃላቸውን እንዲሰጡ የተደረጉበትን የታቦር ክ/ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ኢንስፔክተር ወንድዬ ከበደን አነጋግሯል።

እሳቸው በሰጡት ምላሽ በወቅቱ መኪናችን ተመታብን ያሉት አካላት ወደፖሊስ ጣቢያዉ በመምጣት ባስመዘገቡት መሰረት በአካባቢዉ ላይ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን ተይዘዉ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ኢ/ር ወንድዬ ፤ የተጠቀሱት ንብረቶች መሰረቃቸዉን በወቅቱ አለመስማታቸውን እና አለመመዝገባቸዉን አስታውሰዉ አሁንም ቢሆን ጉዳዩን በአግባቡ ወደሚመለከተዉ የህግ አካል በማቅረብ በተያዘዉ ምርመራ እንዲካተት ማድረግ እንደሚቻል ገልጸዋል።

ተጎጅዎች " በተደራጀ ዝርፊያ ጥቃት ተፈጽሞብናል " የሚሉት የተሳሳተ መሆኑን የሚያነሱት ኢንስፔክተሩ በወቅቱ ' ግጭት ውስጥ የነበሩ ወጣቶች ' ውስጥ በመግባታቸዉ ለስርቆት ተዳርገዉ ሊሆን ይችል እንደሆነ እንጅ በከተማዉ የተባለዉ አይነት ዝርፊያ በፖሊስና በማህበረሰቡ ትብብር #ታሪክ_የሆነ ጉዳይ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በቀድሞ የአርበኞች ግንቦት 7 አባል የነበሩት አቶ ጃንከበድ ዘሪሁን ረቡዕ ጠዋት ታህሳስ 10 ቀን 2016 ዓ/ም አባዶ 'መስቀለኛ' አካባቢ ከመኖሪያ ቤታቸው በፓሊስ ወደ ሜክሲኮ ፓሊስ ጣቢያ ተወስደው እስከ 8፡00 ቢቆዩም ከዚያ በኋላ ወዴት እንደተወሰዱ ባለማወቃቸው ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን ቤተሰቦቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የፓሊስ አባላት ' በወቅታዊ ጉዳይ ' ብለው እንደወሰዷቸው ያስረዱት የአቶ ጃንከበድ የቅርብ ቤተሰብ፣  "ቢያንስ ያሉበትን ማሳወቅ መቻል አለባቸው የመንግሥት አካል እንደመሆናቸው። ቤተሰብ የመጠየቅ፣ የመጎብኘት፣ ጠበቃ የማግኘት መብቱን አላከበሩም። ያለበትን ለመግለጽ ፈቃደኛ አይደሉም " ሲሉ ወቅሰዋል።

ሌላኛው ቤተሰብ በበኩላቸው፣ ፓሊስ ጋ ካለ ' እኛ ጋ አለ ' እንዲሏቸው፣ የተጠረጠረበትን ጉዳይ በግልጽ እንዲያሳውቋቸው ጠይቀው፣ " ኮንፈርሜሽን ለእኛ ትልቅ ርሊፍ ነው። ለሕይወቱ በጣም ያስጋል " ብለዋል።

በተጨማሪም፤ ፍ/ቤት አልቀረበም። #የፈጸመው ወንጀል ስለመኖሩና ስለተጠረጠረበት በግልፅ #አልተነገረንም። እባካችሁ በመንግሥት ቁጥጥር ስር ከሆነ መረጃ ይሰጡን ዘንድ የሚመለከተውን አካል ጠይቁልን፤ የደረሰበትን ማወቅ አልቻልንም ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአቶ ጃንከበድ ቤተሰቦች ጥያቄ ይዞ የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስን አነጋግሯል።

ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኃላፊነት ተሰጥቷቸው የሚሰሩት ዋና ኢንሰፔክተር ታደለ ፣ " በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስለሆነ አንድ ሰው ብቻ አይደለም እዚህ ላይ ሀሳብ መስጠት ያለበት " ብለዋል።

" እዚህ ላይ እኔ የማውቀው፣ የሰማሁት ነገር የለም። መረጃው የለኝም። ስለዚህ ጉዳዩ እኛን የሚመለከት አይደለም " ያሉት ዋና ኢንስፔክተሩ፣ " በወንጀል የተጠረጠረ ሰው ከሆነ፣ ይጠየቃል፣ ይጣራል ጉዳዩ ማለት ነው። በሕግ ሂደት የሚታይ ይሆናል " ብለዋል።

ታዲያ እዲህ ቢሆን እንኳ ተጠርጣሪዎች ያሉበትን ቦታ ማሳወቅ የለባችሁም ወይ ? ሌላ ጭንቀት ቤተሰብ ላይ ከሚፈጥር ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ ኢንስፔተሩ፣ " የት ይሄዳል ያው ማቆያ ነው የሚሆኑት ሰው ሲያዝ፣ በወንጀል የተጠረጠረ ሰው ማቆያ ነው በሕግ እስኪወሰንበት ድረስ " ሲሉ አክለዋል። 

ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረብላቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ምክትል ዳይሬክተር ኮማደር ማርቆስ ታደሰ በበኩላቸው፣ ስለጉዳዩ መረጃው እደሌላቸው፣ ማንኛውም የተጠረጠረ ሰው ሊያዝ እንደሚችል፣ ስለሆነም ተያዙ የሚባሉት ግለሰብ ምናልባት ተጠርጥረው በአድስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባላት ተይዘው ከሆነም ሊቀመጡ የሚችሉት በተያዙበት ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ሊሆን እደሚችል ገልጸዋል። 

አክለውም፣ ተያዙ የሚባሉት ግለሰብ  እዛ ካሉ ቤተሰቦቻቸው ሂደው መጠየቅ እደሚችሉ፣ ከዚህ ባሻገርም ወደ ፖሊስ ኮሚሽኑን ሂደው መጠየቅ እደሚችሉ አስረድተዋል።

መረጃውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba #ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፦ " የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ፦ * ለአመራሮች ፣ * ለባለሙያዎች * ለሰራተኞች ፈተና እንዲሰጡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኃላፊነት ሰጥቷል። ሆኖም ግን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና በቴክኒክ ችግር ምክንያት በመሰረዙ #ይቅርታ ጠይቋል። ቀጣይ የቴክኒክና…
#Update

ባለፈው ሳይሰጥ የቀረው የመንግሥት ሰራተኞች ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ይሰጣል ተባለ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ባለፈው ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ መላው ሰራተኞችን በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።

የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና፦
- ለአመራሮች ፣
- ለባለሙያዎች
- ለሰራተኞች አርብ 12/04/2016 ሊሰጥ የነበረ ሲሆን ፈተናው የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ባጋጠመው " ቴክኒካል ችግር " ምከንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ መገለፁ ይታወሳል።

ሰራተኞች በእለቱ ከረፋዱ 5:00-11:30 ፈተናው ሲጠብቁ የነበረ ሲሆን ከፍተኛ መጉላላት እና እንግልት ሲደርስባቸው ነው የዋለው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።

ቢሮው በቀጣይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን አስታውቋል።

ተፈታኞች ከዚህ ቀደም በኦረንቴሽን ወቅት የተቀመጡ መስፈርቶችን በሙሉ አሟልተው ለፈተና እንዲገኙ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#SafaricomEthiopia M-PESA

ወዝ ወዝ እንበል ፏ ባለ መኪናችን ወደ ህልማችን
እንመዝገብ እንገበያይ እናሸንፍ እድሉ አያምልጠን

የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ ያውርዱ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia

#MPESASafaricom #TerekBeMPESA
#FurtherAheadTogether
#CentralEthiopia

ከሰሞኑን ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ ፓርቲ (ጎጎት) በዞኑ እየደረሰ ነው ያለውን የመብት ጥሰት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።

ፓርቲው " የመብት ጥሰቱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ይህን መግለጫ መነሻ በማድረግ በመንግሥት በኩል ምላሽ ይኖር እንደሆን ጠይቆ ምላሽ አግኝቷል።

ፓርቲው ምን አለ ?

- በጉራጌ ዞኖች እየተፈፀመ ያለው የመብት ጥሰት ተባብሶ ቀጥሏል።
- በምስራቅ መስቃን ወረዳ የታሰሩ ሰዎች ለወራት ፍትህ ሳያገኙ እየተጉላሉ ይገኛሉ።
- በወልቂጤ ከተማ የታሰሩ በርካታ ሰዎች ችሎት ቀርበው ፍትህ የማግኘት መሰረታዊ መብታቸው ተጥሶ ይገኛል።
- የታሰሩ ሰዎች ምቹ ባልሆኑ ቦታዎች ታጉረው ፍትህ የማግኘት መብታቸው ተነፍገዋል።
- በወልቂጤ ከተማ እና አካባቢው ግለሰቦች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በጨለማ ቤታቸው ተሰብሮ ብርበራ እና እስር ይፈፀምባቸዋል። የፓርቲአችን ከፍተኛ አመራሮች እና አባላትም የእስር እና ብርበራው ሰለባ እየሆኑ ይገኛሉ።
- ሰዎች በሚታሰሩበት ወቅት ከፍተኛ ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ከታሳሪዎች ማረጋገጥ ችለናል።
- አዲሱ ክልል ከተመሰረተ ጀምሮ የጉራጌ አካባቢዎች በኢንሴኖ፣ በቆሴ፣ በጢያ እና በወልቂጤ አካባቢዎች የበርካታ ንፁኃን ዜጎች ህይወት ተቀጥፏል።
- ላለፉት 2 ወራት መንግስታዊ እና ህዝባዊ አገልግሎቶች በስርአቱ እየተሰጡ አይደለም። ትምህርት ቤቶች፣ የንግድ ተቋማት፣ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ በአብዛኛው መደበኛ ስራቸውን በአግባቡ መስጠት አልቻሉም።
- የህዝቡ በሰላም ወጥቶ የመንቀሳቀስ መብት ተገድቧል።
- አካባቢው አሁንም በወታደራዊ ኮማንድ ፖስት ስር ተቀፍድዶ ምንም አይነት የመብት ጥያቄ ማንሳት የማይቻልበት እስር ቤት ሆኗል።
- በአሁን ሰዓት ከ25 በላይ ወጣቶች በወልቂጤ ከተማ ከ17 በላይ ወጣቶች በቡታጀራ እና በኢንሴኖ ከተማ ያለ ፍትህ እስር ቤት ታጉረው ይገኛሉ።

ፓርቲው መንግሥት የመብት ጥያቄ የሚያቀነቅኑ፣ ህዝባዊ ውግንና ያላቸው ብሩህ ወጣቶችን እያሳደደ በአንፃሩ በገንዘብ እና በስልጣን የተገዙ ወጣቶችን ለመፍጠር ጥረት እያደረገ ነው ሲል ባወጣው መግለጫ ከሷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጫውን ተመልክቶ በዚህ ጉዳይ መንግሥት የሚለውን ለመስማት ጥረት አድርጓል።

በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡት የዞኑ ኮማንድ ፖስት ኃላፊ ኮሚሽነር ቦጋለ ካሊሬ ፤ እንዲህ ያለዉ ሀሳብ የዞኑን ብሎም የክልሉንና የሀገር ሰላም የማይፈልጉ አካላት ሀሳብ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ የጸጥታ ኃይሉ ትኩረት ማህበረሰቡን ማወያየትና ሰላም ማስፈን መሆኑን ገልጸዋል።

ኮሚሽነሩ ፤ በህግ ጥላ ስር የሚገኙ አካላት ጉዳያቸዉ በፍርድቤት እየታዬና አላግባብ የተያዙ ሰዎችም እየተጣሩ መሆኑን በማንሳት #በዘረፋና በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረዉ የተያዙትም ክስ እንደተመሰረተባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ አሁን ላይ ከሀገር ሽማግሌዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የተለያዩ ዉይይቶች እየተደረጉና ዞኑን ወደሰላምና የተለመደ ሰላማዊ ህይዎቱ እየተመለሰ መሆኑን አመላክተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ባለፈው ሳይሰጥ የቀረው የመንግሥት ሰራተኞች ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ይሰጣል ተባለ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ባለፈው ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ መላው ሰራተኞችን በይፋ ይቅርታ ጠይቋል። የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና፦ - ለአመራሮች ፣ - ለባለሙያዎች - ለሰራተኞች አርብ 12/04/2016…
#AddisAbaba

" ... አስተዳደሩ የብሔር ኮታ ምደባን አስመልክቶ ለከተማዋ ነዋሪዎች በአፋጣኝ ግልጽ ማብራሪያ ይሰጥ " - ኢዜማ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ ፤ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ሊሰጥ በዝግጅት ላይ ስላለው የመንግሥት ሰራተኞች የብቃት ምዘና ፈተና ጉዳይ ግልጽ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቋል።

ፓርቲው ፤ በመርኅ ደረጃ ምዘናው ለማኅበረሰቡ የሚሰጡ አገልግሎቶች በተሻለ ብቃት እና ኢትዮጵያዊ ጨዋነት በተላበሰ ሥነምግባር እንዲሠጡ ታላሚ ያደረገ ከሆነ ለአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ጥራት ያለው ቀልጣፋ አገልግሎት ለማግኘት የሚረዳ መሆኑን ለሠራተኞች ደግሞ ሁልጊዜም ተወዳዳሪ የሚያደርግ አሠራር ስለሚሆን የሚበረታታ ተግባር እንደሆነ ገልጿል።

" በእነዚህ አስተዳደር መ/ቤቶች ፦
- የተገልጋይን ስም እንኳ በቅጡ በሠነዶች ላይ ማስፈር የማይችሉ፣
- ፈጣን አገልግሎት እንዲሠጡ ታስበው አገልግሎት ላይ የዋሉ ቴክኖሎጂዎችን በአግባቡ መጠቀም የማይችሉ፣
- ከሥነምግባር ያፈነገጡ እና በሌብነት የተተበተቡ ሠራተኞችን መመልከት የተለመደ ሆኗል " ያለው ኢዜማ ፤ " ሌላው ቀርቶ አንድ ዜጋ በነፃነት ለመንቀሣቀስ የሚያስፈልገውን የነዋሪነት መታወቂያ ለማግኘት እንኳ ሲጉላላ እና እጅ መንሻ ሲጠየቅ ይስተዋላል። " ብሏል።

ከዚህ አንጻር የአገልግሎት ጥራትን ለማስፈን የምዘና ጅምሩ የሚበረታታ መሆኑን አመልክቷል።

ነገር ግን እነዚህን አስተዳደር መስሪያ ቤቶች የሚመሩት #የገዢው_ፓርቲ አመራሮችም ሆነ ገዢው ፓርቲ እንደተቋም #ለብሄርተኝነት ባላቸው የተዛባ ውግንና በተደጋጋሚ በሚያደርጓቸው አግላይ የአደባባይ ንግግሮች እና አሠራሮች ምክንያት እያንዳንዱ በነዚህ አካላት የሚደረግ እንቅስቃሴና ውሳኔ በማኅበረሰቡ በጥርጣሬ የሚታይ እንዲሆን አድርጎታል ብሏል።

በመሆኑም አስተዳደሩ " የብቃት ደረጃን ለማረጋገጥ እና አገልግሎትን ለማሻሻል የሚደረጉ እርምጃዎች ናቸው " ቢልም ከላይ በተጠቀሰው ምክንያት በጥርጣሬ እንዲታዩ መሆናቸውን መገንዘብና ተገቢውን ማብራሪያ በወቅቱ መስጠት ዜጎችን ከስጋትና ከውዥንብር ያድናል ሲል አሳውቋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በአንድ መ/ቤት የሚገኙ ዳይሬክተሮች እና የቡድን መሪዎች ከአንድ ብሔር ከ 40 % በላይ ሊበልጡ እንደማይገባ መገለጹ አገልግሎት የሚሰጡ መሥሪያ ቤቶች ውሰጥ ለምዘና ሊቀመጥ የሚገባውን ዋነኛውና መሠረታዊ የሆነውን ከትምህርት ዝግጅት እና ከሥራ ልምድ የሚመነጩ የችሎታና የብቃት ጉዳይ አሳንሶ እንዳይመለከት ጥብቅ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ፓርቲው አሳስቧል።

ፓርቲው ፤ የከተማ መሥተዳደሩ ስለፈተናው እና ለማኅበረሰቡ ጥራት ያለው አገልግሎት ከመስጠት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የለውም ስላለው #የብሔር ኮታ ምደባን አስመልክቶ ለነዋሪዎች በአፋጣኝ ግልጽ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቋል።

ኢዜማ በኃላፊነት ቦታዎች ላይ ለሚደረጉ ምደባዎች በምንም ዓይነት መንገድ የብሔር ማንነትን መሠረት ያደረገ መድልኦ የሚደረግባቸው እንዳይሆኑ፤ አሠራሩም ለሁሉም ዜጎች ግልፅና ችግር በሚፈጥሩ አመራሮች ላይ የማያወላዳ ተጠያቂነት ማስፈን የሚችል እንዲሆን ማድረግ ይገባል ብሏል።

(ፓርቲው የላከው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#ንግድፍቃድ #እድሳት

የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፤ የንግድ ስራ ፈቃድ የሚያድሱ ተገልጋዮች ከሰኞ እስከ እሁድ ባሉት የስራ ሰዓት አገልግሎቱን በኦንላይን ማግኘት እንደሚችሉ ገልጿል።

በክልሎች ሲሠጡ የነበሩ የአስመጪነት እና የላኪነት የንግድ ምዝገባ እና ፈቃድ አገልግሎቶች እንደ ቀድሞው ወደ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መመለሳቸውንም አሳውቋል።

በሚኒስቴሩ የሚሠጡ የንግድ ስራ መደቦች ላይ በበጀት ዓመቱ ከሐምሌ1/2015 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 30/ 2016 ዓ.ም ድረስ የንግድ ስራ ፈቃድ ለሚያድሱ ተገልጋዮች፤ ከሰኞ እስከ እሁድ በመንግስት የስራ ሰዓት የፈቃድ ዕድሳት አገልግሎቶችን በኦንላይን ማግኘት ይቻላል ተብሏል።

ወቅቱ የዕድሳት አገልግሎት የሚሰጥበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ፤ በመጨረሻ ቀናት የሚከሰቱ የሲስተም ወረፋዎችን ለመከላከል እንዲቻል፤ ተገልጋዮች የሚያስፈልጉትን መስፈርቶች በሟሟላት የንግድ ስራ ፈቃዳቸውን በቀሩት ቀናት አስቀድመው በኦንላይን እንዲያድሱ በሚኒስቴሩ ጥሪ ቀርቧል።

የንግድ ፍቃድ ማደሻ አድራሻ (ድረገፅ) www.etrade.gov.et. ነው።

ምንም እንኳን ሚኒስቴሩ ንግድ ፍቃዳችሁን በኦንላይን ከሰኞ እስከ እሁድ በስራ ሰዓት ማደስ ትችላላችሁ ቢልም የንግድ ፍቃድ ማደሻው ድረገፅ እንደ ከዚህ ቀደሙ በአግባቡና በፍጥነት አገልግሎት እየሰጣቸው እንዳልሆነ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል። ይህ ችግር እንዲስተካከልም ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
4ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 18 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ከ4ኛ ዙር ጀምሮ ባሉት ውድድሮች አስር አስር አሸናፊዎች በየሳምንቱ ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#AbolJobs

ስራ በምንፈልግበት ጊዜ ከሚያስፈልጉን ነገሮች ውስጥ CV ዋነኛው ሲሆን እንዴት መስራት እንዳለብን በማሰብ የምናባክነው ጊዜ ሰፊ ነው። ይህንን ችግር ለመፍታት ደረጃውን የጠበቀ ፣ አስፈላጊውን መረጃ ያካተተና ከክፍያ ነጻ የሆነ CV በቀላሉ ማግኘት የሚቻልበት መንገድ ተዘርግቶ በስራ ላይ ውሏል። እንዴት?

ወደ https://aboljobs.net/user/register በመግባት እና በመመዝገብ ከዚያም የ Abol-Profile በመሙላት በሰከንዶች ውስጥ ያስገቡትን መረጃ (CV) ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በPDF ማግኘት ይችላሉ። ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን https://publielectoral.lat/aboljobs ይቀላቀሉ።

Website | Facebook | Tiktok | Linkedin
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ • " ከ13,000 በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው የከፋ ችግር ውስጥ ናቸው " - የዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፅ/ቤት • " በሰሃላ ወረዳ 94 በመቶ ነፍሰጡሮችና የሚያጠቡ እናቶች፣ 45 በመቶ ከአምስት ዓመት በታች ሕጻናት በምግብ እጥረት ተጎድተዋል " - የዞኑ ጤና መምሪያ ቢሮ በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በአበርገሌና…
#አማራ #ዋግኽምራ

" ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ 9 አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። … የህፃናትና የእናቶች የህክምና አገልግሎት አደጋ ውስጥ ነው " - የዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ

ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ፦
* የመድኃኒት፣
* የትራንስፖርት፣
* የሕክምና መሣሪያዎች እጥረት በማጋጠሙ በዞኑ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት ፈተና እንደሆነባቸው በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ ምን አሉ ?

- ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ ዘጠኝ አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። በሰርቪስ፣ በሥራ ጫና ከጥቅም ውጪ ሆነዋል። 

- በተፈለገና ባለቀ ሰዓት ወቅቱን ጠብቆ መድኃኒት ለመግዛት እንቅስቃሴዎች ገድበውናል። የሴኩሪቲ ችግር በጣም አሳሳቢ ነው። ሪፈራሎች በሚፈለገው መልኩ እየተንቀሳቀሱ አይደለም። ስለዚህ በእናቶችና በህፃናት የጤና አገልግሎት ጠቅላላ አደጋ ውስጥ ነው። 

- ሰውከፍሎ መታከም አልቻለም። የጤና መድህን ሽፋናችን ዝቅተኛ ነው። ራሳቸውን ሰርቫይብ ማድረግ ያልቻሉ፣ ለመከላከያ፣ ለልዩ ኃይል ለሌሎች ቁስለኞች ሁሉ ጠቅላላ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ የጤና ተቋማት ናቸው ያሉት። እየጠፉ ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው። ግን ደግሞ በትግል እንደምንም እየተቋቋምን ማኅበረሰቡን ለማዳረስ እየሞከርን ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጸጥታው ችግር በድርቅ ለተጎዱት ምን ጉዳት አስከተለ ? ሲል ጠይቋል።

° ይህ ሁኔታ በተለይ በዞኑ በድርቅ ምክንያት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች እያሳደረው ያለው ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው።

* ኮሌራ ተከስቶብናል። እንደ ጤና ተቋማት ትልቅ ሥጋት፣ ከባድ ወረርሽኝ ላይ ነው ያለነው። ቁጥር አንድ ተጋላጭ የሚባሉት ህፃናት፣ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች፣ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች ናቸው። 

° ከኅዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የልየታ ሥራ በሁሉም ወረዳዎች አሰርተን ነበር። በዚያ መሠረት አስደንጋጭ ቁጥር ነው ያገኘነው። ከለየናቸው ነፍሰጡር፣ አጥቢ እናቶች 81 በመቶ የሚሆኑት አጣዳፊ መካከለኛ የምግብ እጥረት ያለባቸው ናቸው።

° እንደ ዞን ከለየናቸው ህፃናት 45 በመቶዎቹ አጣዳፊ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ችግር ያለባቸው ናቸው። ይህ ቁጥር ከተቀመጠው ስታንዳርድ በላይና አስደንጋጭ ነው። አስደንጋጭ ከመሆኑም በላይ አሁን እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች በጣም ዘገምተኛ ናቸው ብለዋል።

የዋግኽምራ ብሄረሰብ ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፦
☑️ 95 በመቶ እናቶች በምግብ እንደተጎዱ፣
☑️ የህፃናት የረሃብ መጠን 15 በመቶ ከደረሰ እንኳ ከስታንዳርድ በላይ እንደሆነ ነገር ግን ከ30 በመቶ በላይ ህፃናት በምግብ እጥረት እንደተጎዱ ገልጾ ነበር።

አሁን የጤና መምሪያ ኃላፊው በገለጹት መሠረት ደግሞ የህፃናቱ የምግብ እጥረት ጉዳት ወደ 45 በመቶ ከፍ ብሏል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ፤ በተለይ የጸጥታው ችግር ከድርቁ ጋር ተያይዞ በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ፈተና መሆኑን፣ ድርቅ፣ ጦርነት፣ ወረርሽኝ በዞኑ መደራረባቸውን ገልጾ እስካሁን ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው፣ አሁንም መንግሥት፣ በጎ አድራጊ ድርጅቶች ከችግሩ ውስብስብነት አንፃር ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተረድተው #እርዳታቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል።

መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተጠናክሮ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA #Eurobond ኢትዮጵያ የቦንድ ብድር ወለድ በወቅቱ ያልከፈለችው ለምንድነው ? ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ ለሸጠችው የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ ሰኞ ዕለት መክፈል የነበረባትን ወለድ እስካሁን አልከፈለችም። የ1 ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ለሽያጭ የቀረበው ከ9 ዓመት በፊት በ2007 ዓ.ም ነበር። ኢትዮጵያ ይህንን ቦንድ ሸጣ ከገዢዎች አንድ ቢሊዮን ዶላር ብድር ያገኘች ሲሆን ብድሩ የሚመለሰው…
#Update

ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ ለሸጠችው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ወለድን በቀነ ገደቡ መክፈል ባለመቻሏ ዕዳቸውን መክፈል ካልቻሉ አገራት ተርታ እንደተመደበች ሮይተርስ የዜና ወኪል አስነብቧል።

ኢትዮጵያ ትናንት ሰኞ ታኅሳስ 15/ 2016 ዓ.ም. መክፈል የነበረባትን የ33 ሚሊዮን ዶላር ባለመክፈሏ ዕዳዋን መክፈል ያልቻለች ሶስተኛዋ የአፍሪካ አገር መሆና መመዝገቧ ተገልጿል።

ከ10 ዓመት በፊት በታኅሣሥ 2007 ዓ.ም. የ1 ቢሊዮን ዶላር የቦንድ ሽያጭ አድርጋ ላገኘችው ብድር የወለድ መክፈያ ጊዜያው ከሁለት ሳምንት በፊት ታኅሣሥ 1/2016 ዓ.ም. ነበር።

ከመክፈያ ጊዜው ቀነ ገደብ በኋላ የነበረው የ14 ቀናት የእፎይታ ጊዜም እንዲሁ ተጠናቀቋል።

ከዚህ ቀደም መንግስት ወለዱን እንደማይከፍል ማስታወቁ ይታወሳል።

የገንዘብ ሚኒስቴር የማሻሻያ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ሂንዣት ሻሚልም ፤ ክፍያው አለመፈጸሙን እና የሚከፈል አለመሆኑንም ማረጋገጣቸውን ብሉምበርግ ዛሬ ማለዳ ዘግቧል።

ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ ዕዳቸውን መክፈል የማይችሉ (Sovereign default ውስጥ ከገቡት) ሁለት የአፍሪካ አገራት ጎራ ተሰልፋለች። ዕዳቸውን መክፈል የማይችሉ የተባሉት ሁለት የአፍሪካ አገራት #ጋና እና #ዛምቢያ ናቸው።

ገንዘብ ሚኒስቴር ከጥቂት ቀናት በፊት በዚህ ጉዳይ በሰጠው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ዕዳዋን የማትከፍለው፤ የውጭ ምንዛሬ ገንዘብ እጥረት ሳለልባት ሳይሆን ሁሉንም አበዳሪዎች " በእኩል ለማስተናገድ " በሚል መሆኑን ተናግሯል።

የፕላን እና ልማት ሚኒስትሯ ዶ/ር ፍጹም አሰፋም ከቀናት በፊት ከፋና ቴሌቭዢን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ይህንን የክፍያ ጉዳይ አንስተው ነበር።

ዶ/ር ፍፁም ምን አሉ ?

- ኢትዮጵያ የዩሮ ቦንድ ወለድንያልከፈለችው የውጭ ምንዛሬ ዕጥረት ችግር ስላለባት አይደለም።

- በዓመት በርካታ ቢሊዮን ዶላሮች ከውጭ ለምናስገባው ዕቃ የምንከፍል ሀገር ነን ስለዚህ 30 ሚሊዮን ዶላር [ገደማ] ገንዘብ ተቸግረን አይደለም ያልከፈልነው ኢትዮጵያ እንዲያውም ብድሯን በጣም በመክፈል የምትታወቅ አገር ናት በችግር ውስጥም ቢሆን።

- ወለዱ ያልተከፈለው ሁሉም አበዳሪ እና ተበዳሪ ተመሳሳይ አይነት አያያዝ ነው ሊያዝ የሚገባው በሚል ምክንያት ነው።

መረጃውን ቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ሮይተርስ እና ብሉምበርግን ዋቢ በማድረግ ነው ያስነበበው።

@tikvahethiopia