TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba #ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፦ " የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና ፦ * ለአመራሮች ፣ * ለባለሙያዎች * ለሰራተኞች ፈተና እንዲሰጡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ኃላፊነት ሰጥቷል። ሆኖም ግን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና በቴክኒክ ችግር ምክንያት በመሰረዙ #ይቅርታ ጠይቋል። ቀጣይ የቴክኒክና…
#Update

ባለፈው ሳይሰጥ የቀረው የመንግሥት ሰራተኞች ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ ይሰጣል ተባለ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ባለፈው ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ መላው ሰራተኞችን በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።

የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተና፦
- ለአመራሮች ፣
- ለባለሙያዎች
- ለሰራተኞች አርብ 12/04/2016 ሊሰጥ የነበረ ሲሆን ፈተናው የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ባጋጠመው " ቴክኒካል ችግር " ምከንያት ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙ መገለፁ ይታወሳል።

ሰራተኞች በእለቱ ከረፋዱ 5:00-11:30 ፈተናው ሲጠብቁ የነበረ ሲሆን ከፍተኛ መጉላላት እና እንግልት ሲደርስባቸው ነው የዋለው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ለደረሰው መጉላላት እና እንግልት ሁሉ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።

ቢሮው በቀጣይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው ፈተና ቅዳሜ ታህሳስ 20/04/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን አስታውቋል።

ተፈታኞች ከዚህ ቀደም በኦረንቴሽን ወቅት የተቀመጡ መስፈርቶችን በሙሉ አሟልተው ለፈተና እንዲገኙ ቢሮው ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia