TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ካለባቸው አካባቢዎች የመጡና የተመረቁ ተማሪዎቹ በታኅሳስ መጨረሻ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበ፡፡

እነዚህ 41 የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች፣ ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ አካባቢ፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እና ከትግራይ ክልል የመጡ ሲሆኑ፣ የመጡበት አካባቢ የፀጥታ ችግር በመኖሩ ከተመረቁ በኋላም በዩኒቨርሲቲው ለመቆየት ማመልከቻ አስገብተው ነበር፡፡

ተማሪዎቹ ከተመረቁ በኋላ በግቢው ውስጥ ሆነው የመኝታና የምግብ አገልግሎት ሲያገኙ መቆየታቸውን የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና የተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ማቲዮስ ኤርሳሞ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

አሁን ላይ ግን ተማሪዎቹ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ መስጠቱን ተናግረዋል፡፡

አንዳንድ ተመራቂዎቹ አዲስ አበባ ውስጥ ሥራ ካገኙ በኋላም በግቢው መኖር ቀጥለዋል ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ተማሪዎቹ የመጡበት አካባቢ በትክክል የፀጥታ ስጋት ያለበት ስለመሆኑ ማረጋገጥ አለመቻሉን ገልጸዋል።

ከትግራይ ክልል የመጡት ተመራቂዎች በጊዜ ሂደት ሥራ በማግኘታቸውና ወደ መኖሪያቸው በመመለሳቸው አሁን ላይ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉ ከትግራይ የመጡ ተማሪዎች ቁጥር 'ጥቂት' መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

''ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያላቸው ሕጋዊ ውል ይቋረጣል'' ያሉት ኃላፊው፤ ዩኒቨርሲቲው ለተመረቁ ተማሪዎች ወጪ የማውጣት ሥልጣን እንደሌለው ገልጸዋል፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን መስከረም 30/2014 ዓ.ም ማስመረቁ ይታወሳል።

ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ

@tikvahuniversity
#AAU

" ... የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ያልሆኑ ግለሰቦች በግቢው ረብሻ ለመቀስቀስ ሞክረዋል። በአሁኑ ሰዓት አንድም የታሰረ ተማሪ የለም " - የአ.አ.ዩ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አማካሪ

@tikvahuniversity በአዲሰ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትላንትና እሁድ ስለተከሰተው ነገር የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የኮሚዩኒኬሽን አማካሪ ኢንጂነር ውባየሁ ማሞን ጠይቋል።

ኢጂነር ውባየሁ ማሞ ፦ " ላለፉት ስድስት ቀናት የተለያዩ ነገሮች በግቢው አስተውለናል። ከተማሪዎቻችን ጋር ስንወያይ ቆይተናል። በመጨረሻ ከተማሪዎች አጀንዳ ውጪ የሆነ ነገር እንዳለ ስናውቅ እርምጃ ወስደናል " ብለዋል።

አማካሪው ፤ " ትላንት የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ያልሆኑ አልፈው ገብተው ረብሻ ለመቀስቀስ የሞከሩ ስምንት ግለሰቦች ተይዘው በሕግ ክትትል ስር ይገኛሉ " ሲሉም ገልፀዋል።

" ግለሰቦቹ የፖለቲካ አጀንዳ ይኖራቸዋል። " ያሉት ኢ/ር ውባየሁ " ንጹሀን ተማሪዎች ላይ ያልተገባ ነገር ለመፈጸም እንደገቡ ስላወቅን ግለሰቦቹን ለይተን ይዘናል " ሲሉ አስረድተውናል።

" በአሁኑ ሰዓት አንድም የታሰረ ተማሪ የለም። አንድም ከትምህርት ገበታው ያቋረጠ ተማሪ የለም። የመማር ማስተማር ሂደቱ ሙሉ በሙሉ እየሄደ ነው " ሲሉም ተናግረዋል።

ኢ/ር ውባየሁ ፥ " በተለያዩ ማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን እየተወራ ያለው ሀሰት ነው። ትክክለኛ መረጃ እየወጣ አይደለም። ተማሪዎችንና ቤተሰብን የሚረብሽ ነገር ነው እየወጣ ያለው። " ብለዋል።

አማካሪው ፤ ትላንትና ግለሰቦቹ ለማምለጥ ሲሞክሩ ለመያዝ የተሰራ ነገር ነበር ያሉ ሲሆን በዚህም ምክንያት የተፈጠረው ችግር ወዲያው ከመንግስት አካላት ጋር በመሆን ተፈቷል ሲሉ ገልፀዋል።
 
@tikvahethiopia
#Huawei #AAU

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና ሁዋዌ ሃንድሼኪንግ ፎረም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትናንት ተከፍቷል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያዘጋጀው የምርምርና ፌር ሳምንት Research and Fairs Week በትናትናው ዕለት ተጀምሯል።

በዚህ። የተለያዩ ኤግዚቢሽኖች ተከፍተው ፤ በአዲስ ዩኒቨርስቲ በምርምር ዘርፍ የተሰሩ የምርምር ስራዎች ለእይታ ቀርበው ተጎብኝተዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ በአይሲቲ መሰረተልማት እና ስማርት መጠቀሚያዎችን በማምረት ቀዳሚ የሆነው ሁዋዌ በዩኒቨርስቲው በመገኘት የ Handshaking Forum ጆብ ፌር ከፍቷል ፥ ይህ ዛሬ የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ሁዋዌ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር Handshaking Forum በሚል የተመራቂ ተማሪዎችን ሲቪ ሲያሰባስብ ለ2ኛ ጊዜው ሲሆን በዚህ ፎረም አቅም ያላቸው ተመራቂ ተማሪዎችን ከአሰሪዎች ጋር ለማገናኘት ይሰራል።

ከሁዋዌ ባገኘነው መረጃ መሰረት ሁዋዌ አዲስ ለተመረቁ ምሩቃን ያዘጋጀው የኢንተርንሺፕ ፕሮግራም ሲኖረው በዚህም ለ3 ወራት በሁዋዌ ኢትዮጵያ ቢሮ እንዲሰለጥኑ ካደረገ በኃላ የተሻለ አፈጻጸም ያሰስመዘገቡትን ይቀጥራል።

ባለፈው ዓመት ለ250 ተማሪዎች የኢንተርንሺፕ እድል የፈጠረ ሲሆን ከነዚያም መካከል 200 ያህሉ በድርጅቱ ተቀጥረዋል። በዚህ ዓመት 300 ያህል የመቀበል እቅድ ሲኖረው እስካሁን ከ90 በላይ ተቀብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (ጥቁር አንበሳ) ? በፎቶው የምትመለከቱት ቢንያም ኢሳያስ ይባላል። ተማሪ ቢኒያም ከልጅነቱ አንስቶ በትምህርቱ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ የልጅነት ህልሙ የሆነውን ህክምና ትምህርት ለመከታተል ወደ ጥቁር አንበሳ ሊገባ ችሏል። 4 ዓመት ድረስ ፈታኝ ነው የሚባለውን የህክምና ትምህርት (ሜዲስን) በከፍተኛ ውጤት ከተማረ በኃላ ግን ዩኒቨርሲቲ ከዚህ በኃላ መማር አትችልም ሲል ገልጾለታል።…
#AAU

ዛሬ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ደነቀ በተማሪ ቢንያም ኢሳያስ ጉዳይ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው ላይም ይህን ብለዋል (ከኢፕድ የተወሰደ) ፦

- ተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ 4ኛ አመት ተማሪ እያለ ነው የአካል ጉዳት እንዳለበት የታወቀው ፤ ዩኒቨርሲቲው ላለፉት 8 ወራት ጉዳዩን ይዞ ሲመረምር ቆይቷል።

- ባዋቀረው ኮሚቴ በቀረበለት ምክረ ሀሳብ መሰረት ተማሪ ቢንያም ከጤና ትምህርት ጋር ተያያዥነት ያላቸው ትምህርቶችን እንዲማር ተወስኗል።
• በህክምና ፋርማሲ
• በህክምና ላብራቶሪ ሳይንስ
• በህክምና ላቦራቶሪ በመረጠው ዘርፍ እንዲማርና ባችለር ኦፍ ባዮሜዲካል ሳይንስ እንዲሰጠው ተወስኗል።

- ተማሪው የአካል ጉዳት እያለበት ለህክምና ትምህርት ዘርፍ መመደቡና ለደረሰው ችግር ዋንኛ ምክንያት የህክምና ኮሌጁ ተማሪዎችን ራሱ መመልመል ያለመቻሉ ነው።

- የህክምና ኮሌጁ እና የትምህርት ክፍሉ አስቀድሞ ማድረግ የሚገባውን ነገር ማድረግ ባለመቻሉ በተማሪ ቢንያም ላይ ለተከሰተው ችግር #ሀላፊነት እንወስዳለን።

ዛሬ የተወሰነውን ውሳኔ በተመለከተ ተማሪ ቢንያም ኢሳያስና ቤተሰቦቹን በመጠየቅ ምላሻቸው ምን እንደሆነ እንልክላችኃለን።

ከዚህ ቀደም ተማሪ ቢንያም ያቋረጠውን የሜዲስን ትምህርት ቀጥሎ ሁለት እጅ የማይጠይቁ ስፔሻላይዜሽኖች ላይ መግባት እንደሚችል (ሳይካትሪ፣ ፐብሊክ ሄልዝ ሌሎችም) ገልፆ ነበር።

ከልጅነቱ ጀምሮ " ሜዲስን " የመማር ህልሙን ለማሳካት የለፋው ተማሪ ቢንያም 5ኛ ዓመት ደርሶ በዩኒቨርሲቲው አሰራር ችግር ከሚወደው ትምህርቱ እንዲወጣ መደረጉ ተማሪውን ጨምሮ መላ ቤተሰቡን ያሳዘነ ድርጊት ነው።

(የተማሪ ቢንያም ጉዳይ - https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/71823?single)

@tikvahethiopia
#AAU

አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ በትግራይ ክልል ለሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መልሶ ማቋቋሚያ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል።

ይኸው ድጋፍ ዛሬ ወደ ክልሉ መላኩን ተቋሙ ገልጿል።

ድጋፉ 11 ሚሊዮን ብር በጥሬ ገንዘብ ሲሆን ቀሪው አንድ ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ኮምፒዩተሮችና የህክምና መሳሪያ ቁሳቁሶች መሆናቸው ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው መሰል ድጋፎችን በቀጣይነት ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አሳውቆ በምርምርና ቴክኖሎጂዎች ረገድም በመልሶ ማቋቋሚያ ስራዎች ላይ የራሱን እገዛ እንደሚያደርግም ገልጿል።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመቄዶንያ መስራች አቶ ቢንያም በለጠ እና ለአርቲስት ደበበ እሸቱ ፤ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ለተወዳጇ ድምፃዊት እጅጋየሁ ሽባባው ( #ጂጂ ) የክብር ዶክትሬት ዲግሪ አበርክተዋል። አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ የመቄዶኒያ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢንያም በለጠ ላከናወኗቸው በጎ ስራዎች የክብር ዶክትሬት አበርክቶላቸዋል። በሰሩት ስራ በሰው ልጆች…
#AAU #DrBinyamBelete😢

ዛሬ ከአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት የተበረከተላቸው የሜቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ቢንያም በለጠ በመድረኩ ላይ ንግግር አድርገው ነበር።

ያደረጉት ንግግር እጅግ ስሜትን የሚነካ ስለነበር ተመራቂዎች እና ታዳሚያንን #እያለቀሱ ሲያዳምጡ ነበር።

አቶ ቢንያም በለጠ ምን አሉ ?

" ...ለእኔ ብዙ ትልቅ ቦታ አትስጡኝ ፤ እኔ የማልረባ ሰው ነኝ ፤ ቅድም ስለእኔ ስትገልፁ ከብዶኛል።

እውነቴን ነው እግዚአብሔር ይሰራል እሱን አልክድም ሜቄዶንያ ላይ ፤ ምክንያቱም ካለምንም እርዳታ ይሄን ሁሉ ሺህ ሰው በሀገር ውስጥ በየቀኑ አንድ ሚሊዮን የእግዚአብሔርን ስራ መሆኑ ግልፅ ነው በጣም።

እኔኮ በሽተኛ ነኝ ሲጀምር ብዙ ጊዜ ተኝቼ ነው የምውለው ፤ ስራ ያቆምኩ ሰው ነኝ እኔ እንደውም የህብረተሰብ ሸክም መሆን ያለብኝ ሰው ነኝ እውነት ለመናገር።

እንደ እኔ አይነት ሰው ዝም ብላችሁ ብታስቡት እንኳን እንደዚህ ለማድረግ ይቅርና እራሴንም ለመቻል ወይ አግብቶ ወልዶ ለመኖር ሰው ለመርዳት ቀርቶ ለመለመን እንኳን አንድ ሰው ጤነኛ መሆን አለበት ፤ ለመለመን ወጣ ብሎ አንድ ቦታ መቀመጥ አለበት እኔ መቀመጥም አልችልም።

ለመኖር እራሱ የማይገባኝ ሰው ነኝ ፤ በእግዚአብሔር ኃይል ነው ያለሁት ፤ እውነቴን ነው የምነግራችሁ ቀልዴን አይደለም። አንድ ሰው ለመለመን መንገድ ላይ ቁጭ ብሎ ሰው መጠየቅ አለበት አይደል እንደዛ እንኳን የምችል ሰው አይደለሁም። ስለዚህ እግዚአብሔር ነው የሚሰራው።

አንድ የህብረተሰብ ሸክም የሆነ ሰው ፤ እግዚአብሔር ምን ያህል ሃጥያተኛ ሰዎችን በመንፈስም በስጋም ደካማ የሆኑ ሰዎችን እንዴት መርዳት እንደሚችል አንዳንድ ሰዎች በቤተሰብ፣  በትዳር፣ ወይ ሰው አስቀይሟችሁ እንደው እግዚአብሔርን የለም ብላችሁ/ እግዚአብሔር ረሳኝ ብላችሁ ከሆነ እግዚአብሔር እንደዚህ ይሰራል። በማይረቡ ሰዎች፣ በተራ በጣም በወንጀለኛ ሰዎች መስራቱን ስታዩ ሁሉንም ሰው እግዚአብሔር እንደሚረዳ የሚያሳይ ነገር ነው።

ክብር ዶክትሬት ተብሏል ፤ እኔ ትንሽ ከብዶኛል በጣም ምክንያቱም እናተ ሸልማችሁኛል ፤ የእግዚአብሔር ፍርድ ደግሞ ከባድ ነው እውነት የእግዚአብሔር ፍርድ በጣም አስፈሪ ነውና ከሲኦል እንድድን እግዚአብሔር ከዚያ እንዲያወጣኝ ፀሎት አድርጉልኝ የእውነት። ይሄ በጣም ከባድ ነገር ስለሆነ ነው። ቀልድ አይደለም እግዚአብሔር ዝም ብለን ሃጥያት ስንሰራ ዝም የሚለን አምላክ አይደለም። የእግዚአብሔር ፍርድ ከባድ ነውና እኔ የምፈራው እሱን ነው እንኳን ልሸለም ለፍርድ እንዲቀልልኝ የማስብ ሰው ነኝ።

ሜቄዶንያ ላይ ብዙ ሰው አስተዋጽኦ ያደርጋል። እኔ የተለየ አስተዋጽኦ የለኝም ከዛ ያነሰ ነው የእኔ አስተዋፅኦ። በሽተኛ ስለሆንኩኝ ስራም ስለሌለኝ አንደኛው ተደጓሚ ነኝ እራሴ በመቄዶንያ ነገር ግን መቄዶንያ ባልፉት ዓመታት እዚህ ለመድረስ ብዙ አስተዋፅኦ ያደረጋችሁ ሰዎች አላችሁ ምስጋናም ክብርም የሚገባው ለእናተ ነው።

ተማሪዎች፣ ወጣቶች ፣በጎፍቃደኞች፣ የመንግሥት ኃላፊዎች፤ የሚኒስትር መስሪያ ቤቶች ፣ ሚኒስትሮች ፣ ኮሚሽነሮች፣ የመንግስት የልማት ድርጅቶች፣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ሜቄዶንያን አግዘዋል በየቢሮው ያስተናግዱናል፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የክልል መስተዳደሮች በሙሉ፣ ለሜቄዶንያ እዚህ መድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። "

(የክብር ዶክተር ቢንያም በለጠ ሙሉ ንግግር ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#AAU

አንጋፋው የ " #አዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ " በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆነ።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው  ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ወስኗል።

ውሳኔው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነው የመማር ማስተማር እና የምርምር ሥራዎችን በላቀ መልኩ መፈጸም እንደሚያስችላቸው የታመነበት በመሆኑ እንደሆነ ተገልጿል።

በዚሁ መሰረትም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ሆኖ አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ነፃነቱ ተጠብቆ መንቀሳቅስ እንዲችል፣ በትምህርት ዘርፍ ለተጀመረው የሪፎርም እንቅስቃሴ ፈር ቀዳጅ ሆኖ እንዲወጣ እድል ይፈጥርለታል ተብሏል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ስርዓትን በቀዳሚነት ተግባራዊ እንደሚያደርግና ለሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተምሳሌት እንደሚሆን ይጠበቃል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

@tikvahethiopia
#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው ዓመት ጀምሮ የቅደመ ምረቃ ተማሪዎችን በውድድር ብቻ እንደሚቀበል ገለጸ።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከመጪው 2016 ዓ.ም. ጀምሮ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን የሚቀበለው በምደባ ሳይሆን #በውድድር መሆኑን አስታውቋል።

ዩኒቨርስቲው ክፍያ የሚፈጽሙ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎችን " በልዩ " ሁኔታ ለማስተማር እንዳቀደም ገልጿል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ይህንን ያስታወቀው የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ መሆኑን አስመልክቶ ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 16፤ 2015 በዋናው ቅጥር ግቢ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።

መግለጫውን የሰጡት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ራስ ገዝ ለመሆን ላለፉት ሁለት ዓመታት ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ወደ ራስ ገዝነት የሚያደርገውን ሽግግር " ሁለት ዓመት ባልሞላ " ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ማቀዱን አስታውቀዋል።

መረጃው የ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር እና የኢዜአ " ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AAU አንጋፋው የ " #አዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ " በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆነ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው  ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ወስኗል። ውሳኔው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ…
#AAU

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ #የአዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ።

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ #ቻንስለር ተደርገው በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተሹመዋል።

ሹመቱ የተሰጣቸው፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆኖ እንዲቋቋም እንዲቋቋም በአዋጅ መጽደቁን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተከትሎ ከተሾሙት ቻንስለር በተጨማሪ አዳዲስ የቦርድ አመራሮች የተሰየሙለት ሲሆን ፤ ቦርዱም ዩኒቨርሲቲውን በሃላፊነት ሊመሩ የሚችሉ ፕሬዚዳንት እና ም/ፕሬዚዳንቶችን በቀጣይነት እንደሚሾም ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

#Update

ቦርዱ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩን የቦርድ ሊቀመንበር አድርጎ መሾሙን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ደግሞ ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መሾማቸውን ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ወጪያቸው በመንግሥት የሚሸፈንላቸውን ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ሰጥተን እንቀበላለን " - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ትምህርት ሚኒስቴር ከሚያስቀምጠው የመቁረጫ ነጥብ በላይ ያመጡ ተማሪዎችን አወዳድሮ እንደሚቀበል መገለጹ ይታወቃል፡፡ በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የሆነው ዩኒቨርሲቲው፣ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን የሚቀበልበት መስፈርት…
#AAU

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሽግግር ሂደቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ በነባሩ አሰራር እንደሚቀጥል ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ተናግረዋል።

በዚህም የ2016 የትምህርት ዘመን ተማሪ ቅበላ ከዚህ ቀደም በነበረው ነባሩ ስርአት የሚከናወን ሲሆን ፤ አዲስ አሰራሮች ከመጡ በየጊዜው ይፋ እንደሚደረግ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሰራተኞች ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች የተሰጠው ፈተና #ውጤት ይፋ ሆኗል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው እና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው ፈተናን በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል። በዚህ መግለጫም ፤ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተናው የወሰዱት የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣…
#AddisAbaba #Exam

ለአዲስ አበባ አስተዳደር አመራሮች ፣ ባለሞያዎች / ሠራተኞች የተሰጠውን የቴክኒክ እና ባህሪ ብቃት ፈተና የማለፊያ ነጥብ አምጥተው ያለፉ #የክዋኔ_ክህሎት ስልጠና ይሰጣቸዋል ተብሏል።

የማለፊያ ነጥብ ማምጣት ሳይችሉ ቀርተው #ያላለፉት ደግሞ #የአቅም_ግንባታ_ስልጠና እንደሚሰጣቸው ተጠቁሟል።

በተጨማሪ የማለፊያ ውጤት ያላመጡት ዝቅ ብለው እንደሚመደቡ ፤ አሁን ላይ #ስንብት የሚባል ነገር እንደሌለ ፤ ስንብት የሚፈፀመው መጨርሻ ላይ ሁሉ ነገር ከተጠናቀቀና ሌላ አማራጭ ከጠፋ ብቻ መሆኑ ተነግሯል።

የፈተናው ውጤት፦

👉 የቴክኒክና የባህሪ ብቃት ምዘና ፈተናውን የወሰዱ አመራሮች፣ ባለሙያዎች / ሠራተኞች አጠቃላይ ቁጥር 15 ሺህ 151

ፈተናውን የወሰዱት አመራሮች ቁጥር 4 ሺህ 213 ፤ የፈተውን ማለፊያ ውጤት ያመጡት 1 ሺህ 422 ፤ ፈተናውን ያላለፉ አመራሮች 2,791 ፤ በአጠቃላይ ፈተናውን ያለፉት 34 በመቶ አመራሮች ብቻ ናቸው።

NB. አመራሮች ለማለፍ ከ60 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸው ነበር።

ፈተና የወሰዱ የሠራተኞች ቁጥር 10 ሺህ 257 ፤ ፈተናውን ያለፉት 5 ሺህ 95 ናቸው። 5,162 ሠራተኞች አላለፉም። ያለፉት 50 በመቶ የሚሆኑት ናቸው።

NB. ሰራተኞች ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸው ነበር።

#AAU #KotebeUniversityofEducation

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
መንትዮቹ👏

ዛሬ ራዝ ገዙ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 271 የህክምና ተማሪዎቹን አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ  198 የሚሆኑት በማዕረግ፣ በከፍተኛ ማዕረግ እና በእጅግ ከፍተኛ ማዕረግ የተመረቁ ናቸው።

ከነዚህ ውስጥ ደግሞ መንትዮቹ  ዶ/ር ቸርነት ተስፋሁን እና ዶ/ር ብሩክ ተስፋሁን በከፍተኛ ማዕረግ በህክምና ዶክትሬት ተመርቀዋል።

#AAU

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
🥇3.87 GPA👏

አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው እለት ካስመረቃቸው ሴት ተማሪዎች መካከል ዶ/ር ረድኤት ጌቱ ከበደ በህክምና ዶክትሬት 3.87 GPA በማስመዝገብ ተሸላሚ ሆናለች።

#AAU

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ተማሪዎችን አወዳድሬ ነው የምቀበለው " - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ-ገዝ ዩኒቨርሰቲ የሆነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በራሱ ፖሊሲና መስፈርት ፤ ምዘናና የክፍያ ስርዓት ተማሪዎችን አወዳድሮ እንደሚቀበል አሳውቋል። በመደበኛ፣ በማታና በርቀት በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ አመልካቾች በቅርቡ ዝርዝር ማስታወቂያ እንደሚያወጣ…
#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአዲስ የተማሪዎች ቅበላ አሰራርን አስተዋወቀ።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ2017 ዓ.ም የአዲስ የተማሪዎች ቅበላ አሰራርን በተመለከተ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጫው ተከታትሏል።

ዩኒቨርስቲው የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ እና ልዩ ብቃት ያላቸው ተማሪዎችን አወዳድሮ እንደሚቀበል በዚሁ መግለጫ አስታውቋል።

የዩኒቨርስቲው ተጠባባቂ ፕረዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ፥ ራስ-ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆኖ የተቋቋመው ዩኒቨርሲቲው ተቋማዊ ነጻነት፤ አስተዳዳሪዊ ነጻነት፤ የፋይናንስ ነጻነት እና አካዳሚክ ነጻነት ማግኘቱን ገልጸዋል።

" ይህም መምህራኑን ሆነ ተማሪዎችን የመምረጥ መብት ይሰጠዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

አዲስ ይተገበራል በተባለው የቅበላ አሰራር በ2014፤ 2015 እና 2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ የመልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች የሚወጣውን መስፈርት ታሳቢ አድርገው በዩኒቨርሲቲው ፖርታል https://portal.aau.edu.et መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።

መስፈርቶቹ ምንድን ናቸው ?

ዶ/ር ሳሙኤል ፥ አንዱ መስፈርት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን 50 በመቶ በላይ ማምጣት እንደሆነ ገልጸዋል።

ይህ ግን የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ባገናዘበ መልኩ 60 ወይም 70 በመቶ ድረስ ከፍ ሊል እንደሚችል ጠቁመዋል።

በመቀጠልም ዩኒቨርስቲው በራሱ የሚያዘጋጀው የመግቢያ ፈተና (Undergraduate Admission Test) የሚኖረው ሲሆን ይህንን ፈተና ማለፍም ሌላው ዩኒቨርሲቲው ያስቀመጠው መስፈርት ነው ብለዋል።

ፈተናው ምን መልክ ይኖረዋል ?

በዩኒቨርስቲው መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች የሚቀርበው የፈተና ይዘት ምን መልክ አለው በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ዶ/ር ሳሙኤል ፈተናው የአፕቲቲውድ (Apptitude) መልክ የሚኖረው እንደሆነ ጠቅሰው የተማሪዎችን የቋንቋ፤ የማመዛዘን እንዲሁም የቀመር አቅማቸውን የሚለካ እንደሚሆን ጠቁመዋል።

ፈተናው ከሌሎች የመግቢያ ፈተና ጋር ተመሳሳይነት ሊኖረው እንደሚችል ያነሱት ፕሬዝዳንቱ ሆኖም የሚወጣው ፈተና ሙሉ በሙሉ የዩኒቨርስቲው እንደሚሆን አስረድተዋል።

የክፍያ እና የስኮላር ሺፕ ሁኔታ በተመለከተ ምን ተባለ ?

በዩኒቨርስቲው ለመማር ጥያቄ የሚያቀርቡ ተማሪዎች በሁለት አይነት መንገድ እንደሚስተናገዱ ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።

አንደኛው መስፈርቱን አሟልተው እና ሙሉ ክፍያ ከፍለው የሚማሩ ተማሪዎች ሲሆኑ ሌላው መንግስት ስፖንሰር ሺፕ እንዲሰጣቸው የሚጠይቁ ተማሪዎች ናቸው።

ይህን በተመለከተ የተቀመጠ ኮታ እንደሌለ የገለጹት ዶ/ር ሳሙኤል እንደ እቅዳቸው ግን 50 በመቶ በመንግስት 50 በመቶ በግል ወጪያቸው የሚሸፈንላቸውን ተማሪዎች ለመቀበል እንደሆነ ገልጸው ካልሆነም ቁጥሩ በተወሰነ መልኩ ልዩነት ሊኖረው እንደሚችልም ጠቁመዋል።

መንግስት ከፍተኛ ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለሀገር በሚፈለጉ የስልጠና መስኮች ወጪን ጭምር በመሽፈን የሚያስተናግድበት ሥርዓት እንደሚኖር እና ለሴቶች ለአካል ጉዳተኞች እና ከታዳጊ ክልል ለሚመጡ ተማሪዎች ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥም ተመላክቷል።

ተማሪዎች በሚያመለክቱበት ወቅት ብዙ ቅጾችን እንደሚሞሉ ፤ ስኮላርሺፕ የሚጠይቁ ተማሪዎች ከፍለው መማር እንደማይችሉ የሚያሳይ ማስረጃ ከሚመለከተው አካል ማሟላት እንደሚጠበቅባቸው እና የሚያስገቡት መረጃ ትክክለኛነቱ እንደሚጣራና ሐሰተኛ ሆኖ ከተገኘ የህግ ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ጭምር አንስተዋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ዩኒቨርስቲው በተከታታይ እንደሚሰጥ አረጋግጧል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AAU #GAT

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መስከረም 3/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡ 

በተቋሙ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ የአመልካቾች ምዝገባ ከዛሬ ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 1/2017 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል፡፡

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕሮፌሰር እንድርያስ እሸቴ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳንት እና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት የፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ የቀብር ስንስርዓት እሁድ ጷጉሜን 3/2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስትያን ይፈፀማል።

በዕለቱ ከጠዋቱ 4:00-6:00 ሰዓት ባስተማሩበትና በሰሩበት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ራስ መኰንን አዳራሽ የስንበት ስነ-ስርዓትም የሚከናወን ይሆናል።

#AAU

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የመመዝገቢያ ቀናት ከጳጉሜ 5/2016 ዓ.ም - መስከረም 8/2017 ዓ.ም ድረስ ነው " - የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋዉ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2017 ዓ /ም  ለቅድመ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች ለመቀበል መዘጋጀቱን አሳውቆናል። ዩኒቨርሲቲው ለ2017 ቅድመ ምረቃ ትምህርት በቀን በመደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል ከፍለዉ ለሚማሩ እንዲሁም በማታ በተከታታይ መርሃ ግብር…
#AAU

ራስ ገዙ አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቀን በመደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል በመጀመሪያ ዲግሪ በ2017 ዓ/ም መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ያቀረበው ጥሪ ነገ ያበቃል።

በ2017 ዓ/ም በቅድመ ምረቃ መደበኛ መርሃ ግብር በትምህርት ሚኒስቴር ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  የተማሪዎች ምደባ እንደማይኖር  ይታወቃል።

በመንግስት ስኮላርሺፕ እንዲሁም በግል ከፍለው በዩኒቨርሲቲው መማር ለሚፈልጉ በሙሉ የአ.አ.ዩ  የሚያወጣውን የመግቢያ ፈተና (UAT) እንዲሁም ሌሎች መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

በዚህም መሠረት በዩኒቨርሲቲው ድረ ገጾች ፦
➡️ www.aau.edu.et
➡️ https://portal.aau.edu.et ላይ የተመለከቱትን ዝርዝር የማመልከቻ መስፈርቶች በማሟላት መመዝገብ ይችላሉ።

የመመዝገቢያ ቀኑ ነገ መስከረም 8/ 2017 ዓ.ም ያበቃል።

የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀናት ወደፊት ይገለጻል።

በመንግስት ስኮላርሽፕ ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለመማር የሚያያዘው ማስረጃ ምንድነው ?

በቀን መደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሽፕ ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለማመልከት ከተጠየቁት መስፈርቶች አንዱ የቤተሰብ የገቢ መጠንን የሚገልፅ ማስረጃ ማያያዝ ነው።

በዚህ መሰረት ፦

1. ከወረዳ/ቀበሌ ወይም መስሪያ ቤት ስለገቢያቸዉ ዝቅተኛነት የሚገልፅ ማስረጃ ከሚመለከተዉ ከወረዳ ወይም ቀበሌ ወይም መስሪያ ቤት ዘርፍ ኃላፊ ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

2. የቤተሰቡ ኃላፊ ጡረታ ላይ የሚገኙ መሆናቸዉን የሚገልፅ ደብዳቤ ወይም የታደሰ የጡረተኝነት መታወቂያ ወይም የባንክ ደብተር ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

https://publielectoral.lat/TikvahUniversity/12317

(Addis Ababa University)

@tikvahethiopia
#AAU

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ላስመዘገቡ 200 ተማሪዎች በውድድር ነጻ የትምህርት እድል (ሶኮላርሺፕ) ሊሰጥ እንደሆነ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን የመጀመርያው ራስገዝ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን ተወስኖ ተማሪዎችን በራሱ የቅበላ ስርዓት ተቀብሎ ለማስተማር ምዝገባ እያከናወነ ነው።

ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ ያዘጋጀውን የተማሪዎች መግቢያ ፈተና ይሰጣል። በዚህም ብቃትን፣ ብዝሃነትንና ፍትሐዊነትን ማዕከል አድርጎ ተማሪዎችን እንደሚቀበል ገልጿል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ላስመዘገቡ 200 ተማሪዎችን በውድድር ነፃ የትምህርት እድል ከዶርሚታሪና የካፌ አገልግሎት ጋር እንደሚሰጥ አሳውቋል።

አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ " ብቃትና ተሰጥዖ ያላቸው ተማሪዎች መዳረሻ ለመሆን ያለኝን ቁርጠኝነት እገልጻለሁ " ብሏል።

@tikvahethiopia