TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
በሌላ መረጃ ፦ ምንም እንኳን በኬንያ " ስቴት ሀውስ " ኦፊሴላዊ መረጃ ባያሰራጭም ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊየም ሩቶ በነገው ዕለት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ለመገኘት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ተሰምቷል። ℹ️ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት የማስጀመሪያ ልዩ መርሃ ግብር ነገ ከአመሻሽ ጀምሮ እንደሚያካሂድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ…
#Kenya #Ethiopia

የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የመጀመሪያ የአፍሪካ ሀገር ጉዟቸውን ወደ #ኢትዮጵያ እንደሚያደርጉ የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ገልፀዋል።

ነገ በአዲስ አበባ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚታደሙ የተነገረላቸው ሩቶ ፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ይመክራሉ።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ምርጫ ማሸነፋቸው በIEBC በተገለፀበት ዕለት ከዓለም ሀገራት መሪዎች ሁሉ በቅድሚያ የ " እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት ያስተላለፉላቸው መሪ እንደነበሩ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶክተር ዊሊያም ሩቶ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዜዳንቱ አዲስ አበባ ሲደርሱ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተቀብለዋቸዋል። ሩቶ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚያደርጉ የተገለፀ ሲሆን ሁለቱ መሪዎች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል። ዶ/ር…
#Kenya #Ethiopia

ፕሬዜዳንት ዶክተር ዊሊያም ሩቶ የኢትዮጵያ የስራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ኬንያ አመሻሹን ተመልሰዋል።

ጉብኝታቸው ምን ይመስል ነበር ? የኬንያ ፕ/ት ፅ/ቤት ምን አለ ?

- ፕሬዝዳንት ሩቶ ጥዋት አዲስ አበባ ሲገቡ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ከፍተኛ ባለስልጣናት ናቸው ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው የተቀበሏቸው።

- ከዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል።

- ከቀናት በፊት የተመረቀውን የኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየምን ከዶ/ር ዐቢይ ጋር ሆነው ጎብኝተዋል።

- ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ጋር ሆነው በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

እንደ ኬንያ ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት (ስቴት ሀውስ) መረጃ ፦

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ረጅም ጊዜ የዘለቀ ግኝኑነት እና ቅርበት በመጠቀም የድንበር ተሻጋሪ ንግድን ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላት የገለፀች ሲሆን ፕሬዜዳንት ሩቶም ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

" የኬንያ - ኢትዮጵያ አጋርነት ለጋራ ተጠቃሚነታችን እና ቀጠናዊ መረጋጋት የማዕዘን ድንጋይ ነው " ሲሉ ሩቶ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ፕሬዜዳንቱ ኢትዮጵያ #የላሙ_ወደብን ለደቡብ ኢትዮጵያ ክፍል እንደ መነሻ ወደብ እንድትጠቀም ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ጠይቀዋል።

ምንጭ፦ የኬንያ ፕ/ት ፅ/ቤት / የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ፅ/ቤት

@tikvahethiopia
#KENYA

የጎረቤታችን ኬንያ ፤ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አማፂያንን ለመዋጋት እና የቀጠናውን ሰላም ለማስከበር ወደ ምስራቃዊ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ ይሰማራሉ።

የሰራዊቱ አባላት ዛሬ ተሸኝተዋል።

ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ከቀጠናው ጦር ጋር የሚቀላቀሉትን የኬንያ መከላከያ ሰራዊት አባለትን ስንብት ስነ ስርዓት ያካሄዱ ሲሆን በስነስርዓቱ ላይ የሰንደቅ አላማ የመስቀል ስነስርዓት ተካሂዷል።

በዲሞክራቲክ ኮንጎ የሚሰማራው የኬንያ ጦር የምስራቅ አፍሪካ ማህብረሰብ አካል በመሆን የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ጦር በአገሪቱ ግጭትና ሁከትን ለማስቆም የሚያደርገውን ጥረት ያግዛል ተብሏል።

" የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ አባል ሃገራት " በያዝነው አውሮፓውያኑ ዓመት መጀመሪያ ላይ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ አማጽያንን ለመዋጋት ወታደሮችን የማሰማራት ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

የኬንያ ጦር ሰራዊት የመጀመሪያ ተልዕኮ በሰኔ ወር በM 23 አማፂያን ቁጥጥር ስር ያለችውን የድንበር ከተማ ቡናጋናን መልሶ ለመቆጣጠር የሚደረገውን ዘመቻ ማገዝ እንደሚሆን ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#Kenya

የኬንያ ፖሊስ 41 ኢትዮጵያውያንን ናይሮቢ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገለፀ።

ግለሰቦቹ ወደ ደቡብ አፍሪካና ሌሎች አገራት ለመዘዋወር በአንድ ቤት ውስጥ ለአራት ቀናት ያህል ሲጠባበቁ ሰኞ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም መያዛቸውን ገልጿል።

ኢትዮጵያውያኑን በሕገ ወጥ መንገድ ሊያዘዋውሩ ነበሩ የተባሉ ሁለት አዘዋዋሪዎችም በዚሁ አጋጣሚ የተያዙ ሲሆን አንደኛው #ኢትዮጵያዊ መሆኑም ፖሊስ አሳውቋል።

ፖሊስ ጥቆማ ደርሶት በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው እነዚህ የሕገ ወጥ ሰዎች አዘዋዋሪዎች በአገሪቱ ውስጥ ካሉ ሌሎች በርካታ ዝውውሮች ጀርባ እንዳሉበት ተገልጿል።

ኢትዮጵያውያኑ በዚህ ሳምንት ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ወደ ኬንያ እንዴት እንደገቡ ተጨማሪ ምርመራ እስኪደረግ ድረስ ለተጨማሪ ስድስት ቀናት በእስር እንዲቆዩ መታዘዙን #ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ቲክቶክ " ኬንያ ውስጥ እንዲታገድ አቤቱታ ቀረበ። የኬንያ ፓርላማ " #ቲክቶክ " የተሰኘው የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ እንዲያግድ አቤቱታ እንደቀረበለት የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። " ወጣቶች ትምህርታቸውን ትተው የ 'ቲክቶክ' ቁራኛና የአዕምሮ ህመምተኛ እየሆኑ ነው " የሚለው አቤቱታው ፓርላማው አፋጣኝ ውሳኔ እንዲሰጥ ጠይቋል። የፓርላማው አፈጉባኤ ሞሰስ ዋታንጉላ፣ " ሁከትን እና የጥላቻ ንግግርን…
#TikTok #Kenya

በኬንያ ቲክቶክ ላይ የሚወጡ ቪዲዮች ቁጥጥር እንዲደረግባቸው ከኩባንያው ጋር መስማማቷን ሀገሪቱ ማስታወቋን ቪኦኤ ዘግቧል።

ስምምነቱ የተደረሰው " ቲክቶክ ያልተገቡ ቪዲዮዎችን ያሰራጫል " በሚል እንዲታገድ ከአንድ ግለሰብ ለሀገሪቱ ፓርላማ ከቀናት በፊት ጥያቄ መቅረቡን ተከትሎ ነው፡፡

የአጭር ቪዲዮ ማጋሪያው ኩባንያ ቲክቶክ፣ በመድረኩ ላይ የሚወጡትን ቪዲዮዎች መቆጣጠርን በተመለከተ ከኬንያ ጋር በጋራ ይሠራል ሲል የፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ጽ/ቤት አመልክቷል።

ይህን በተመለከተም ከኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሾ ዚ ችው ጋር መነጋገራቸውን ቢሮው ጨምሮ አስታውቋል።

በስምምነቱ መሠረት፣ " ያልተገቡ ናቸው " የሚባሉ ቪዲዮች ከመድረኩ እንደሚወገዱ ታውቋል።

በአፍሪካ በቲክቶክ ላይ የሚወጡትን የቪዲዮዎች ይዘት በተመለከተ ቁጥጥር ለማድረግ ኩባንያው በኬንያ ቢሮ እንደሚከፍት ዋና ሥራ አስፈጽሚው ሾ ዚ ችው ይፋ ማድረጋቸውም ታውቋል።

ቲክቶክ ኬንያ ውስጥ እንዲታገድ ለሀገሪቱ ፓርላማ ጥያቄ ከቀረበ በኃላ የፓርላማው አፈጉባኤ ሞሰስ ዊታንጉላ ፤ " ቲክቶክ በኬንያውያን በወጣቶች ዘንድ ተዘውታሪ በመሆኑ ፦
- ግጭቶችን በማባባስ፣
- ልቅ ወሲብን በማስፋፋት፣
- የጥላቻ ንግግሮችን በማስፋፋት፣
- የብልግና ቃላትን በማስፋፋት፣
- አደገኛ ባሕሪያትን በማስፋፋት ለአገሪቱ ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ እሴቶች ጠንቅ እየሆነ ነው " ብለው ነበር።

በሌላ በኩል ፤ ሌላኛዋ የምስራቅ አፍሪካ ሀገር ሶማሊያ የአሸባሪዎች መፈንጫ ሆኗል ፤ ህዝቡንም እያሳሳተ ነው በሚል ቲክቶክ እንዲታገድ አዛለች። እግዱ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ ነው የሚጠበቀው። በተመሳሳይ ቴሌግራምም እንዲታገድ ውሳኔ ከተሰጠባቸው መተግበሪያዎች አንዱ ነው።

ሶማሊያ አሸባሪ ድርጅቶችና ቡድኖች አሰቃቂ የሆኑ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን እንዲሁም ፎቶግራፎችን በማሰራጨት ሕብረተሰቡን ለማሳሳት ጥቅም ላይ ውሏል በሚል ነው እንዲታገዱ ያዘዘችው።

@tikvahethiopia
#Kenya

የጎረቤት ኬንያ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ብሔራዊ መታወቂያ ካርድ ለማውጣት ዜጎች ክፍያ እንዲፈጽሙ መንግሥት ያወጣውን መመሪያ #አገደ

የኬንያ መንግሥት ይህን መመሪያ ማውጣቱን ተከትሎ ዜጎች ቅሬታቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ።

እንደ ቢቢሲ ዘገባ ማጋሬ ጊኬንይ የተባሉ ሐኪም ናቸው መንግሥት አዲሱን መመሪያ ያወጣው “ድንገተኛ እና ምክንያታዊ ባልሆነ መንገድ” ነው ሲሉ የሕዝብ ድምፅ በማሰባሰብ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት የወሰዱት።

የተሰበሰበው የሕዝብ ድምፅ እንደሚለው በአዲሱ መመሪያ መሠረት፤ በርካታ ዜጎች መታወቂያ ካርድ በቀላሉ ማግኘት አይችሉም።

ከዚህ ቀደም በነፃ ይሰጥ የነበረው ብሔራዊ መታወቂያ ካርድ አሁን 1 ሺህ ሺልንግ [370 ብር ገደማ] እንዲሆን መንግሥት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አዟል።

መታወቂያ ለማሳደስ ደግሞ ኬንያዊያን 2 ሺህ ሺልንግ እንዲከፍሉ ተጠይቀዋል።

ኬንያዊያን እያሻቀበ ባለው የኑሮ ግሽበት ምሬታቸውን እየገለጡ ባሉበት ወቅት ነው መንግሥት ገቢውን ለማሳደግ ሲል ዜጎች ከዚህ ቀደም በነፃ አሊያም በርካሽ የሚያገኟቸውን አገልግሎቶች በበለጠ ክፍያ እንዲሆን ያደረገው።

በርካታ ኬንያዊያን በሚከፍሉት ግብር አማካይነት ተግባራዊ እየሆኑ ላሉ የመንግሥት ግልጋሎቶች ተጨማሪ ክፍያ መጠየቃችን ተገቢ አይደለም እያሉ ናቸው።

አዲሱ መመሪያ መታወቂያ ካርድ ብቻ ሳይሆን ፓስፖርት፣ የጋብቻ ወረቀት፣ የሥራ እና የመኖሪያ ፈቃድ እንዲሁም የልደት እና ሞት ምስክር ወረቀት ለማውጣትም ክፍያ ይጠይቃል።

አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት አሊያም ለማሳደስ ይጠየቅ የነበረው ክፍያ 50 በመቶ ሲያድግ የልደት እና ሞት ወረቀት ለማውጣት የሚጠየቅ ክፍያ በአራት እጥፍ አድጎ 200 ሺልንግ ገብቷል።

መንግሥት በተጨማሪ ዜግነት አሊያም የመኖሪያ ፈቃድ ለማስጠት የሚጠይቀውን ክፍያ እጥፍ አድርጎታል።

ከኬንያዊያን ዜጎች በውጭ ሃገር የተወለዱ ልጆች የኬንያ ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ ለማግኘት የሚጠየቁት ክፍያ 1 ሚሊዮን ሺልንግ ሆኗል።

በደንገት የተጫኑት የክፍያ መመሪያዎች አቅም የሌላቸው ዜጎች የመንግሥትን ግልጋሎት ተጠቅመው አስፈላጊ ወረቀት ለማግኘት ሊቸገሩ ይችላሉ የሚል ስጋት ጭሯል።

ባለፈው ዓመት መስከረም ወደ ሥልጣን የመጡት የፕሬዝደንት ሩቶ መንግሥት በርካታ የግብር ዓይነቶችን ዜጎች ላይ የጣለ ሲሆን የነዳጅ ዋጋ ከፍ እንዲልም አድርጓል።

የብሔራዊ ፓርክ መግቢያ ዋጋን ጨምሮ በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶች ክፍያ ከፍ እንዲልም ሆኗል።

ባለፈው ሳምንት የገቢዎች መ/ቤት ባለሥልጣናት ወደ ኬንያ የሚመጡ ዜጎችም ሆኑ ጎብኝዎች ከ500 ዶላር በላይ ተመን ያለው ዕቃ ይዘው ከተገኙ ይቀረጣሉ ብሏል።

ፕሬዝደንት ሩቶ እስካሁን ስለ ዋጋው ጭማሪ ያሉት ነገር ባይኖርም ሐሙስ ዕለት ለሃገሪቱ ዜጎች ባስተላለፉት መልዕክት ኬንያዊያንን ከዕዳ ጫና ለማላቀቅ " ቀላል ያልሆኑ ግን አስፈላጊ " ውሳኔዎችን ለመውሰድ ተገድጃለሁ ብለዋል።

#BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia #Kenya

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በኬንያ እያደረጉት በሚገኘው ይፋዊ ጉብኝት በፕሬዝዳነት ዊልያም ሩቶ በስቴት ሀውስ ኬንያ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የጠ/ሚ ፅ/ቤት ፤ " የአቀባበል ስነስርዓቱ ሁለቱ መሪዎች እና ልዑካን ቡድኖቻቸው በሁለትዮሽ፣ ቀጠናዊ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ እያደርጓቸው ያሉ ጉልህ ግንኙነቶች እና ውይይቶች ጅማሮ ነው። " ብሏል።

ሁለቱ መሪዎች በድይይታቸው የሁለቱን ሀገራት ጥልቅ እና ታሪካዊ ግንኙነት ብሎም ኢኮኖሚያዊ ትስስር አንስተው ይኽንኑ በቁርጠኝነት ማጠናከር እንደሚገባ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተነግሯል።

" ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ወሳኝ አጋጣሚ ሆኖ የዲፕሎማሲያዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን የበለጠ ለማዳበር ብሩህ መፃዒ ጊዜን ያመላከተ ሆኗል " ሲል የጠ/ሚ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ትላንት ለሁለት ቀን ይፋዊ የስራ ጉብኝት ኬንያ መግባታቸውና ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ እንደተቀበሏቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር #ታንዛኒያ ለሳምንታት በዘለቀ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት 155 ሰዎች ሲሞቱ ፤ 236 ሰዎች ደግሞ የተለያየ መጠን ያለው ጉዳት እንደደረሰባቸው የሀገሪቱ ጠ/ሚ ቃሲም ማጅዋሊ ተናግረዋል። በዚህ ሳምንት በጎረቤት #ኬንያ በደረሰው የጎርፍ አደጋ በትንሹ 35 ሰዎች መሞታቸው ተነግሯል። 40,000 ሰዎች  ደግሞ ከቤታቸው እንዲፈናቀሉ ሆነዋል።…
#Kenya

በጎረቤት ኬንያ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 188 ደርሷል።

ካለፈው መጋቢት ጀምሮ በደረሰው አውዳሚ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 188 መድረሱን የሀገር አስተዳደር ሚኒስቴር አሳውቋል።

እስካሁን ያልተገኙ በርካታ ሰዎች መኖራቸውም ተገልጿል።

በኬንያና ሌሎች የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች በተከታታይ እየጣለ ባለው ከባድ ዝናብ የብዙ ሰዎች ህይወት እየጠፋ ሲሆን የከፍታ ቦታዎች መናድም ነዋሪዎችን ካለመጠጊያ አስቀርቷል፡፡

መንገዶችን ድልድዮችን እና ሌላም የመሰረተ ልማት አውታሮችን ውድሟል። #VOA

@tikvahethiopia
#Kenya #USA

የጎረቤት ኬንያ ፕሬዜዳንት በአሜሪካ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።

እ.ኤ.አ ከ2008 ወዲህ ወይም ከ16 ዓመት በኃላ ነው ዋይት ሃውስ ለመጀመሪያ ጊዜ የአፍሪካ መሪ በዚህ ደረጃ ተቀብሎ እያስተናገደ የሚገኘው።

አሜሪካን እየጎበኙ የሚገኙት ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ከፍ ያለ አቀባበል እና ከፍተኛ የቀድሞና የአሁን ባለስልጣናት በተገኙበት ልዩ እራት ግብዣ እንደተደረገላቸው ታውቋል።

ከፕሬዜዳንት ጆ ባይደንና ከሌሎች ባለልሰጣናት ጋር ተገናኝተው የሁለትዮሽ ውይይት ያደረጉም ሲሆን ሁነኛ ስምምነቶችም ከአሜሪካ መንግሥት ጋር መፈራረማቸው ተሰምቷል።

ሩቶ ከቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ባራክ ኦባማ ጋርም ተገናኝነትው መክረዋል።

በሌላ በኩል ፥ ኬንያ የሀገሪቱን የጸጥታ ስራዎች እና የሰላም ማስከበር ተልእኮዎቿን ለማሳደግ 16 በአሜሪካ የተሰሩ እጅግ ዘመናዊ ሄሊኮፕተሮች ልትቀበል እንደሆነ " ሲትዝን ቲቪ " ዘግቧል።

ይህ የፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በዋሽንግተን ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ለኬንያ ካበረከቱት መልካም ነገሮች አንዱ ነው ተብሏል።

ሂሊኮፕተሮቹ እ.ኤ.አ ከ2024 እስከ 2025 መጨረሻ ናይሮቢ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዋይት ሀውስ አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ ኬንያ በመስከረም ወር 150 " M1117 " የታጠቁ እጅግ ዘመናዊ የደህንነት ተሽከርካሪዎችን ትቀበላለች።

More ➡️ @thiqahEth

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USA #kenya

የጎረቤታችን ሀገር ኬንያን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶን ተቀብለው እያስተናገዱ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ኬንያን ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል የመጀመሪያዋ #የNATO_አባል_ያልሆነች (non-NATO) ዋና አጋር ሀገር እንደምታደርጋት ቃል መግባታቸው ተነግሯል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Kenya

ጎረቤት ኬንያ ታቃውሞ እየናጣት ነው።

መንግሥት በታክስ ላይ ጭማሪ ሊያደርግ ማቀዱን ተከትሎ በተለይም ወጣቱ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥቷል።

ከወጣቶቹ ሰልፍ ጋራ በተያያዘ ትላንት አንድ ሰው #ተገድሏል፡፡

ግድያው የተፈጸመው በፖሊስ በተተኮሰ ጥይት ነው ተብሏል።

ዛሬም በናይሮቢና የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞ ሲካሄድ ውሏል።

ተቃዋሚዎቹ በሚቀጥለው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሔድ የተቃውሞ ሰልፍ መጥራታቸው ተነግሯል።

ይህ በኬንያ ወጣቶች መሪነት የተነሳው እና ባለፈው ማክሰኞ በናይሮቢ ከተማ ተጀምሮ በመላው አገሪቱ የተሰራጨው ተቃውሞ በመጭው ማክሰኞ ብሔራዊ የሥራ ማቆም አድማ እንዲደረግ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል።

ተቃዋሚዎቹ ለምን አደባባይ ወጡ ?

ተቃዋሚዎች በሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ደስተኛ አይደሉም።

አካሄዳቸውም ለብዙ ኬንያውያን ኑሯቸውን አስቸጋሪ ማድረጉን ይገልጻሉ።

በተለይም መንግሥት አሁን ያዘጋጀው የታክስ ጭማሪ ረቂቅ አዋጅ የህዝቡን ኑሮ የሚያመሰቃቅል እንደሆነ በመግለጽ እየተቃወሙ ነው።

የታክስ ጭማሪውን በመቃወም ለወራት በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ሲደረግ ቆይቶ ነው ወደ ተቃውሞ ሰልፍ የተቀየረው።

የኬንያ መንግሥት ምን ይላል ?

መንግሥት የታክስ ጭማሪ ሊያደርግ ያቀደው ብድር ለመክፈል እና ለልማት ሥራዎች እንደሆነ ገልጿል።

ተቃውሞውን ተከትሎ ከረቂቅ አዋጁ ላይ የተወሰኑትን እንደሚተው ቢያስታውቅም ተቃውሞው ግን ዛሬም ቀጥሏል።

የታክስ ጭማሪው ምን ላይ ነው ?

መንግሥት በያዘው እቅድ የታክስ ጭማሪው በተለያዩ ሸቀጦች ላይ የሚደረግ ነው።

በነዳጅ ላይ ሊጨመር የታሰበው 9 ሺልንግ ሲሆን ጭማሪው ለፈረሱ መንገዶች መጠገኛ እንደሚሆን የአዋጁ አርቃቂዎች አስታውቀዋል።

መንግስት በተጨማሪ አካባቢን ለመጠበቅ በሚል ታክስ ለመጣል ያቀደ ሲሆን ይህም ደግሞ የፕላስቲ ውጤቶች የሚያስከትሉትን ብከላ ለመከላከል እንደሆነ አስታውቋል።

ብሔራዊ ሸንጎው ረቂቅ አዋጁን ሚቀጥለው ሳምንት እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

ለተቃውሞ የወጡት ኬንያውያን ግን በተቃውሟቸው እንደሚገፉበት አስታውቀዋል።

#AFP
#VOA
#Kenya

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kenya ጎረቤት ኬንያ ታቃውሞ እየናጣት ነው። መንግሥት በታክስ ላይ ጭማሪ ሊያደርግ ማቀዱን ተከትሎ በተለይም ወጣቱ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥቷል። ከወጣቶቹ ሰልፍ ጋራ በተያያዘ ትላንት አንድ ሰው #ተገድሏል፡፡ ግድያው የተፈጸመው በፖሊስ በተተኮሰ ጥይት ነው ተብሏል። ዛሬም በናይሮቢና የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞ ሲካሄድ ውሏል። ተቃዋሚዎቹ በሚቀጥለው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሔድ የተቃውሞ…
#Update

በነገው ዕለት በኬንያ ምድር አንቀጥቅጥ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ተብሏል።

ይህ ሰልፍ የሀገሪቱ መንግስት ያረቀቀውን የፋይናንስ ረቂቅ አዋጅን የሚቃወም ነው።

የተቃውሞ ሰልፉ አይቀሬ እንደሆነ ያወቀው የሀገሪቱ መንግሥትም በአገር ውስጥ ጉዳይ እና ብሔራዊ አስተዳደር ካቢኔ ሚኒስትር በኩል ሰልፉ በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል።

ዛሬ በሰጠው ይፋዊ መግለጫ ማንኛውም ተቃዋሚ የመንግስትም ሆነ የግል ንብረትን እንዳያወድም ወይም እንዲያወድም እንደማይፈቀድለት አፅንዖት ሰጥቷል።

የተቃውሞ ሰልፈኛው የሚሄድበትን አቅጣጫ ቀደም ብሎ ለጸጥታ ኃይል በማሳወቅ እጅባና ጥበቃ እንዲደረግለት ማድረግ አለበት ተብሏል።

ሰልፈኞቹ ሰልፉን በፍጹም ሰላማዊ መንገድ ማድረግ እንዳለባቸው ያሳሰበው የሀገሪቱ መንግስት ትጥቅ ታጥቆ ሰልፍ መውጣት እርምጃ ሊያስወስድ እንደሚችል አስጠንቅቋል።

ተቃዋሚ ሰልፈኞች ፦
- የውሃ፣
- የኃይል አቅርቦት
- ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች የሚሰጡት ወሳኝ ቦታዎች ላይ እንዳያገኙ ተከልክለዋል።

በተጨማሪ በህዝባዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንደማይችሉ ተገልጿል።

በምንም መልኩ በየብስ ፣ በባቡር፣ በባህር ፣ በአየር ትራንስፖርት ላይ ጣልቃ መግባት እንደ ሌለባቸው ምንም ይሁን ምን ለሀገሪቱ ህግ የበላይነት ሁሉም ሰው ሊታዘዝ እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ሁሉም ተቃዋሚዎች ሰልፉን ሁከት እና ብጥብጥን በማያበረታታ መንገድ እንዲያደርጉ እንዲሁም ደግሞ ፦
° ሰልፉን መሳተፍ የማይፈልጉ / ተቃውሞ ማድረግ የማይፈልጉ
° የፖሊስ አባላትን ፣
° የመንግስት አካላትን ማስፈራራት ፣ ማስጨነቅ እና መተንኮስ እንደሌለባቸው ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

#Kenya

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በኬንያ ተቃውሞ ሰዎች ተገደሉ። የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግሥት ያረቀቀውን አዲስ የታክስ ሕግ የተቃወሙ ኬንያውያን የአገሪቱን ፓርላማ ቅጥር ጊቢ ጥሰው ገብተዋል። ፖሊስ በከፍተኛ ቁጥር የወጡ ተቃዋሚ ወጣቶችን ለመበተን ጥይት እና አስቀሽ ጭስ ተኩሷል። እስካሁን ድረስ ቢያንስ 5 ሰዎች በጥይት የተመቱ ሲሆን ሁለቱ ሕይወታቸው አልፏል። ከጥቂት ሰዓታት በፊት የአገሪቱ ም/ ቤት አባላት…
ፎቶ ፦ በኬንያ ናይሮቢ የተቆጡ ተቃዋሚዎች የሀገሪቱን ፓርላማ ጥሰው በመግባታቸው በርካታ የምክር ቤቱ አባላት ምድር ቤት (ግራውንድ) ለመደበቅ ሲሯሯጡ ታይተዋል።

የተ/ምክር ቤት አባላቱ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞት የነበረውንና በተለያዩ ምርት እና አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ ታክስ የሚጥለውን ረቂቅ ሕግ አጽድቀው ነበር።

ተቃውሞ የቀሰቀሰው የፋይናንስ ሕግ በ195 የምክር ቤት አባላት ድጋፍ ፣ በ106 የም/ ቤት አባላት ተቃውሞ በአብላጫ ድምጽ ነው የጸደቀው።

በቀጣይ ወደ ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ይመራል።

#Kenya
#KenyaParliament

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
ፎቶ ፦ የሀገሪቱን ፓርላማ በኃይል ጥሰው የገቡት መንግሥት ያረቀቀውን የፋይናንስ ሕግ የሚቃወሙ የኬንያ ወጣቶች በፓርላማው ካፍቴሪያ ምግብ ሲበሉ ታይተዋል።

ወጣቶቹ ዛሬ ጨምሮ ላለፉት ተከታታይ ቀናት " ታክስ ለመጨምር ያሰበው ረቂቅ ሕግ ኖሮ ያከብድብናል ፤ ተውት ይቅር ! አንደግፈውም " በማለት እየተቃወሙ ይገኛሉ።

በዛሬው ተቃውሞ የጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት የሰው ህይወት የጠፋ ሲሆን ወጣቶቹ ግን የሀገሪቱን ፓርላማው ጥሰው ገብተዋል።

የተወሰነውን ክፍልም በእሳት አያይዘዋል።

#Kenya
#KenyaParliament

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የሀገሪቱን ፓርላማ በኃይል ጥሰው የገቡት መንግሥት ያረቀቀውን የፋይናንስ ሕግ የሚቃወሙ የኬንያ ወጣቶች በፓርላማው ካፍቴሪያ ምግብ ሲበሉ ታይተዋል። ወጣቶቹ ዛሬ ጨምሮ ላለፉት ተከታታይ ቀናት " ታክስ ለመጨምር ያሰበው ረቂቅ ሕግ ኖሮ ያከብድብናል ፤ ተውት ይቅር ! አንደግፈውም " በማለት እየተቃወሙ ይገኛሉ። በዛሬው ተቃውሞ የጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት የሰው ህይወት የጠፋ ሲሆን ወጣቶቹ ግን…
#Kenya

የኬንያ መከላከያ ሰራዊት ሰላምና የህግ ስርዓትን እንዲያስከብር ትዕዛዝ ተሰጠው።

የሀገሪቱ መንግሥት ለቀናት ከዘለቀው የፋይናንስ ህግ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ የኬንያ መከላከያ ሰራዊት የህዝቡን ደህንነት፣ ሰላምና የህግ ስርዓት እንዲያስከብር አሰማርቷል።

በሌላ በኩል ፤ የኬንያው ፕሬዜዳንት መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በመግለጫቸው የዛሬውን ታቃውሞ ፤" እንደ ሀገር ክህደት / ከሃዲነት " የሚቆጠር እንደሆነ ገልጸው ፤ የጸጥታ ኃይሎች የኬንያውያንን ደህንነት እንዲያስጠብቁ መመሪያ እንደሰጡ ተናግረዋል።

ተቃዋሚዎች የኬንያ ፓርላማን ሰብረው ስለገቡበት ክስተት ጉዳይም ምርመራ እንደሚደረግ አመልክተዋል።

የወንጀል ድርጊትና ወንጀለኞችን ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው የተቃውሞ ሰልፍ ከሚያደርጉት መለየት ይገባል ብለዋል።

ፕ/ት ሩቶ " አደገኛ ወንጀለኞች " ሲሉ የጠሯቸው አካላት ሊፈጸሙት የሚችልን ማንኛውም ሙከራ ከንቱ ሆኖ እንዲቀር የደህንነት አካላት እርምጃ እንዲወስዱ እንዳዘዙ ገልጸዋል።

ህዝቡንም " ዛሬ ማታ ተኙ ! የናተ፣ የቤተሰቦቻችሁ እና የንብረቶቻችሁ ደህንነት ከምንም በላይ ቅድሚያ ሰጥተን እንጠብቃለን " ብለዋል።

" የተቃውሞው የፋይናስ ምንጮች ላይም ምርመራ ይደረጋል " ሲሉ አክለዋል።

በኬንያ ዛሬ ማክሰኞ በነበረው ተቃውሞ እስካሁን በታወቀው ብቻ 10 ሰዎች ከጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተገድለዋል።

#Kenya
#FinanceBill2024

@tikvahethiopia