TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#NBE በትግራይ ክልል "የባንክ ሂሳብ የከፈቱ" እጅግ በጣም በርካታ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ላለፉት ቀናት ገንዘብ ለማውጣታ ተቸግረዋል። ለምን ይህ ሊሆን እንደቻለም እጅግ በጣም ግራ ተጋብተው ነበር። በሀገራችን የተለያዩ ከተሞች በትምህርት ላይ የሚገኙ እና ቋሚ ኑሯቸውን ያደረጉ አባላቶቻችን #እየተቸገሩ መሆናቸው እየገለፁ ነው። በዚህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ለአዲስ ፎርቹን ጋዜጣ እንደገለፀው…
#NBE

ከነገ ጀምሮ በትግራይ ክልል ባሉ ባንኮች አካውንት የከፈቱና ከትግራይ ክልል ውጭ ያሉ ደንበኞች በያሉበት የሀገሪቱ አካባቢዎች ሂሳባቸውን ማንቀሳቀስ እንዲችሉ መፈቀዱ እና ለባንኮችም ይህ መመሪያ መተላለፉን NBE ዛሬ አሳውቋል።

ይህ በፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በወንጀል ተጠርጥረው ሂሳባቸው እንዳይንቀሳቀስ የተደረጉ ደንበኞችን የሚመለከት አይደለም።

በሌላ በኩል ፦

የፀጥታ ሁኔታ ለባንኮች አመቺ በሆነባቸው የትግራይ ክልል ከተሞች ባንኮች ተከፍተው ስራ እንዲጀምሩ ብሄራዊ ባንክ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየሰራ መሆኑን አስታውቋል። የፀጥታ ሁኔታ አመቺ ባልሆነባቸው የክልሉ ከተሞች ባንኮች ተዘግተው እንደሚቆዩ NBE ለኢቲቪ ገልጿል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#NBE : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለተለያየ የቢዝነስ ዘርፎች ባንኮች ይሰጡ የነበረውን ብድር ላልተወሰነ ጊዜ እንዲያቆሙ የተላለፈው መመርያ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከ4 ሳምንታት በላይ አስቆጥሯል፡፡

ባንኮች በዚህ መመርያ መሠረት የተፈቀዱ ብድሮች ሳይቀሩ እንዳይለቀቁ ተደርገው ቆይተዋል፡፡

በዚህ መመርያ መሠረት የተለያዩ ቢዝነሶች ከባንክ ሊያገኙ የሚችሉትን ብድር ባለማግኘታቸው በሥራዎቻቸው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል።

የማይንቀሳቀስ ንብረት አስይዞ መበደር እንደማይችል ጭምር የሚደነግገው ይህ መመርያ ተግባራዊ ከሆነ በኋላ ግን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ‹‹ብድር ሊለቀቅላቸው ይገባል›› ያላቸውን የቢዝነስ ዘርፎችና ሁኔታዎች እየፈተሸ፣ ባንኮች ብድር መስጠት እንዲችሉ በተከታታይ እያስታወቀ ነው፡፡

ጥቅምት 1 ቀን 2014 ዓ.ም. የአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ምርት ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ኩባንያዎች የተቋረጠው የብድር አቅርቦት እንዲለቀቅላቸው ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሰኞ ዕለት ለባንኮች ባስተላለፈው መልዕክት መሠረት በአበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ በማምረትና ለውጭ ገበያ በማቅረብ ላይ ለሚገኙ ኢንቨስተሮች ብድር መስጠት የሚችሉ በመሆኑ፣ በዚሁ መሠረት ደንበኞቻቸውን ማስተናገድ እንደሚችሉ አሳውቋቸዋል፡፡

የአበባ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ኢንቨስተሮች ብድር እንዲሰጥ የተፈቀደበት አንዱ ምክንያት፣ በአብዛኛው ሥራቸው ከባንክ ብድር ጋር የተገናኘ በመሆኑ፣ ብድር እንዲቋረጥ መደረጉ ሥራዎቻቸው ላይ ተፅዕኖ ፈጥሯል በሚል የኢትዮጵያ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ አምራችና ላኪዎች ማኅበር ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አቤቱታ በማቅረቡ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

Credit : ሪፖርተር ጋዜጣ

@tikvahethiopia
#NBE

ባንኮች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሚያስቀምጡት መጠባበቂያ ገንዘብ ላይ ለቡና ላኪዎችና አቅራቢዎች ብድር እንዲሰጡ በብሔራዊ ባንክ የተላለፈው መመርያ ከታኅሳስ 13/2014 ዓ.ም. ጀምሮ መተግበር መጀመሩን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

በኢንዱስትሪው ውስጥ እስካሁን ባልተለመደ ሁኔታ ተግባራዊ እንዲሆን ከብሔራዊ ባንክ በተላለፈው መመርያ መሠረት ባንኮች በብሔራዊ ባንክ ከሚያስቀምጡት የአሥር በመቶ መጠባበቂያ ገንዘብ ላይ ሁለት በመቶውን ወጪ በማድረግ ለዚሁ ዘርፍ ብድር እንደተጠቀሙበት አስታውቋል፡፡

በተለይ የቡና የወጪ ንግድ እንዳይስተጓጎል ባንኮችም የጥሬ ገንዘብ  ችግር እንዳይገጥማቸው ታሳቢ ተደርጎ ተግባራዊ እንዲሆን በተላለፈው መመርያ መሠረት፣ ለቡና ላኪዎችና አቅራቢዎች ብድር ማቅረብ ይችላሉ፡፡

ባንኮቹ ለነዚህ ዘርፎች የሚሰጡት ብድር እያንዳንዱ ባንክ ባለው መጠባበቂያ ገንዘብ ልክ መጠን የሚወሰን ነው፡፡

የተሰጠው ብድር የመመለሻ ጊዜ ገደብ የተቀመጠለት ሲሆን፣ ባንኮቹ ለነዚህ ዘርፎች የሰጡትን ብድር እስከ ነሐሴ 2014 ዓ.ም. መልሰው ወደ ብሔራዊ ባንክ  ማስገባት እንደሚኖርባቸው ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ማስታወሻ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመርያ መሠረት ባንኮች የደንበኞቻቸውን የተሟለ መረጃ እንዲያጠናክሩ የተሰጣቸው የጊዜ ገደብ በዚህ ሳምንት ይጠናቀቃል። ከተሰጠው ቀነ ገደብ በኋላ መረጃዎችን ያልሰጡ ደንበኞች አካውንታቸውን #ማንቀሳቀስ አይችሉም። ባንኮች ባለፉት 6 ወራት መመርያው በሚጠይቀው መሥፈርት መሠረት የደንበኞቻቸውን መረጃ እየሰበሰቡ ነው፡፡  ይህንኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመርያ ተከትለው…
#NBE

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመርያ መሠረት ባንኮች የደንበኞቻቸውን የተሟለ መረጃ እንዲያጠናክሩ የተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ባለፈው የካቲት 20 ቀን 2014 ተጠናቋል።

መረጃዎችን ያልሰጡ የባንክ ደንበኞች አካውንታቸውን #ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ ሆነዋል (በሚሊዮን ሊቆጠሩ ናቸው ተብሎ ይታመናል) ፤ አካውንታቸውን ማንቀሳቀስ የሚችሉትም በመመሪያው መሰረት መረጃ ሲሰጡ ብቻ ነው።

የ " መታወቂያ እድሳት " ግን እንቅፋት የሆነባቸው ብዙ ናቸው ለእነሱ የታሰበ ነገር ስለመኖሩ የታወቀ ነገር የለም።

ባንኮች ደንበኞቻቸው መረጃ እንዲሞሉ ላለፉት 6 ወራት ያህል በዋና ዋና ሚዲያዎች፣ በማህበራዊ ሚዲያ ፣ በአጭር የፅሁፍ መልዕክት ፣ በባንኮች የማስታወቂያ ቦርድ ላይ ጥሪ ሲያቀርቡ የነበረ ሲሆን አንዳንድ ባንኮች በመጨረሻው ሳምንት በስልክ እየደወሉ ለመቀበል ጥረት አድርገዋል።

ከቀነገደቡ መጨረሻ በፊት የባንክ ኃላፊዎች በመመርያ የተደነገገውን ማስፈጸም ከባድ ሥራ በመሆኑ መረጃ የማሰባሰቡ ሥራ ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገዋል የሚል አስተያየት ቢሰጡም ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምላሽ ሳይሰጥ ጊዜው አልቋል።

በዚሁ አጋጣሚ በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ የግጭት ፣ የጥላቻ መልዕክቶች፣ ፌዝ ፣ ስድብ እና አሉታዊ ነገሮች ለብዙሃን በፍጥነት እና በብዛት ሼር ከማድረግ ይልቅ ወሳኝ ጠቃሚ መልዕክቶች የማጋራት ልምድና ኃላፊነት ሊጨምር ይገባል።

ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ጠቃሚ መልዕክቶችን በአግባቡ ብናጋራ መረጃ ላልሰማው ወገናች እንዲሰማ እንዲሁም ደግሞ በመጨረሻ ቀናት ከሚፈጠር ወከባ ብዙ ሰዎችን መካከል ይቻላል።

@tikvahethiopia
#NBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በአገሪቱ ድንበር ውስጥ መያዝ የሚቻለውን የውጭ ምንዛሪ መጠን የሚደነግገውን መመርያ በማሻሻል በአገሪቱ ድንበር ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ምንም ዓይነት ግብይት እንዳይደረግ ክልከላ ማድረጉን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

በብሔራዊ ባንክ " ልዩ ፈቃድ " ካልሆነ በስተቀር የውጭ ምንዛሪ ይዞ መገኘት የተከለከለ ሲሆን፣ በስጦታና በረድዔት መልክ ለሦስተኛ ወገን በጥሬ ገንዘብ ማስተላለፍም ተከልክሏል፡፡

ከ6 ዓመታት በፊት በወጣው ነባሩ መመርያ ውስጥ እነዚህ ክልከላዎች አልነበሩም፡፡

በአዲሱ መመርያ " በልዩ ፈቃድ " የተባለው ምናልባት ለአስጎብኚ ድርጅቶች፣ ለሆቴሎችና ለቀረጥ ነፃ መደብሮች ይሆናል የሚል ግምት ቢኖርም በመመርያው ላይ ግን አልተገለጸም፡፡

በብሔራዊ ባንክ ገዥ በሆኑት ዶ/ር ይናገር ደሴ ተፈርሞ የወጣውና ከሰኞ ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ በሆነው አዲሱ መመርያ መሠረት ፦

👉 ማንኛውም የውጭ ምንዛሪ ይዞ ከውጭ አገር የሚመጣ ሰው በብር መመንዘር እንዳለበት ተገልጾ፣ ይህም ከተፈቀደው መጠን በላይ ከሆነና የውጭ ዜጋ ከሆነ ገንዘቡ በከፈተው ሒሳብ (አካውንት) ውስጥ እንደሚቀመጥ ተገልጿል፡፡

👉 በአዲሱ መመሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚመጡና ለአጭር ጊዜ ለሚቆዩ ዜጎች የሚፈቀደው የገንዘብ መጠን ግን ከፍ ተደርጓል፡፡ ብሔራዊ ባንክ ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡና ለሚወጡ ሰዎች መያዝ የሚፈቀድላቸውን የገንዘብ መጠን የሚደነግገውን መመርያ ከ6 ዓመት በኋላ በማሻሻል፣ የገንዘቡን መጠን ከእጥፍ በላይ ከፍ አድርጓል፡፡

• ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ ዜጎችም፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን 10 ሺሕ ዶላር ወይም በሌሎች የውጭ ምንዛሪዎች ተመጣጣኝ ይዘው ሲመጡ፣ በኢትዮጵያ ብር መንዝረው መጠቀም ይችላሉ፡፡ ከ10 ሺሕ ዶላር የበለጠ ይዘው ከመጡ ግን፣ ለጉምሩክ በማሳወቅ በግላቸው የውጭ ምንዛሪ አካውንት ውስጥ ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡ በነባሩ መመርያ ነዋሪ ላልሆኑ የውጭ ዜጎች መያዝ ይፈቀድ የነበረው 4 ሺሕ ዶላር ብቻ ነበር፡፡

• ነዋሪነታቸው ኢትዮጵያ ውስጥ የሆኑ ሰዎች ከውጭ ሲመጡ እስከ 4 ሺሕ ዶላር ወይም በሌሎች የውጭ ምንዛሪዎች ተመጣጣኙን ይዘው መምጣት የተፈቀደላቸው ሲሆን፣ ይህ በነባሩ መመርያ አንድ ሺሕ ዶላር ብቻ ነበር፡፡

👉 የኤምባሲ ሠራተኞች፣ ጊዜያዊ ሠራተኞች፣ እንዲሁም ለስብሰባና ለተለያዩ ጊዜያዊ ጉዳዮች ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ ዜጎች የድጋፍ ደብዳቤ ማምጣት ከቻሉ ከአሥር ሺሕ ዶላር በላይ ይዘው እንዲገቡ ይፈቀድላቸዋል፡፡

👉 ማንኛውም ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣም ሆነ ከኢትዮጵያ የሚወጣ ሰው ከ3 ሺሕ በላይ መያዝ አይፈቀድለትም፡፡ ይህም በነባሩ መመርያ 1 ሺሕ ነበር፡፡ ነገር ግን ወደ ጂቡቲ የሚሄዱ ሰዎች በተለየ ሁኔታ እስከ 10 ሺሕ ብር መያዝ የሚችሉ ሲሆን፣ ከዚህ በፊት 4 ሺሕ ብር ብቻ ነበር፡፡

👉 በአዲሱ መመርያ ሁሉም የውጭ ምንዛሪ ይዘው የሚመጡ ሰዎች በሕጋዊ የምንዛሪ ቢሮዎች ወደ ብር መቀየር ሲኖርባቸው፣ ይህም ኢትዮጵያ ውስጥ ከብር ውጪ ለመገበያያ ሌላ ገንዘብ መጠቀም ስለማይፈቀድ ነው። ምንዛሪ ማድረግ የሚችለውም ግለሰቡ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር መግባቱን የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠሩ 30 ቀናት ውስጥ ነው፡፡

👉 በድንበር በኩል የሚገቡ ሰዎች 500 ዶላር ወይም በሌሎች ምንዛሪ ተመጣጣኙን ይዘው መግባት የሚችሉ ሲሆን ነገር ግን በድንበር አካባቢ ለሚገኙ የኢትዮጵያ የጉምሩክ ጣቢያዎች ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡

ያንብቡ : https://telegra.ph/Reporter-09-07
#NBE

በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ አስቀማጮች ዋስትና ለመስጠት የተቋቋመው የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ እስከ 200 ሺሕ ብር ተቀማጭ ገንዘብ ላላቸው ዋስትና እንደሚሰጥ ተገለጸ፡፡

ባንኮች እና የማክሮ ፋይናንስ ተቋማት በየዓመቱ ከተቀማጭ ገንዘባቸው 0.2 በመቶ ለፈንዱ ገቢ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተከታዩን ብለዋል ፦

" በየባንኩ ለእያንዳንዱ አስቀማጭ እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆን ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋን ይሰጣል፡፡

የመድን ሽፋኑ መጠን እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆነው ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋኑ እንዲሰጥ የተወሰነው፣ 96 በመቶ ያህል አስቀማጮች የተቀማጭ ገንዘባቸው መጠን የተጠቀሰውን ያህል ስለሆነ ነው።

በዚህ መሠረት የመድን ሽፋኑ ይሰጣል። ይህ ውሳኔ አብዛኞቹን አስቀማጮች የሚሸፍን ነው።

ባንኮች ለዚህ ዋስትና ሽፋን ተቀማጭ የሚያደርጉት በየዓመቱ ከጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘባቸው 0.2 በመቶ የሚሆነውን በማስላት ለፈንዱ ገቢ በማድረግ ተፈጻሚ ይሆናል።

የተቀማጭ ገንዘብ ዋስትና ፈንድ አገልግሎት ሲጀመር ባንኮቹ የሚከፍሉት ክፍያ ይኖራል። የገንዘቡ መጠን ግን ገና አልተወሰነም ። "

More : https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-05-07

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#NBE

የኢንሹራንስ ዘርፉ ፤ ከ " ብሔራዊ ባንክ " ውጪ በሆነ ተቆጣጣሪ ተቋም እንዲመራ ለማስቻል ተፈላጊ የሆነው ጥናት በዓለም ባንክ አማካይነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡

በዓለም ባንክ በኩል የሚደረገው ጥናት በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ሰፊ የሆኑ ተግባራትን እንደሚሸፍን ተጠቅሷል።

የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ይህ በተመለከተ ለሪፖርተር ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

አቶ ሰለሞን ደስታ ፦

" የኢንሹራንስ ዘርፉን የሚቆጣጠር ከብሔራዊ ባንክ ውጪ የሆነ ተቆጣጣሪ እንዲቋቋም ጥናት ተጀምሯል።

Terms of Reference እና ሌሎችም ጉዳዮች እየተሠሩ ነው።

በጥናቱ የመጀመርያ ሥራ ተብሎ የተያዘው ጉዳይ ገለልተኛ ተቋም ‹እንዴት ይዋቀር ? የሚለው ሲሆን ከዚያም ተጠሪነቱ ለማን ይሁን ? ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ነው ? ለፓርላማው ነው ? የሚለውን ጨምሮ ሌሎችም ጉዳዮች ናቸው።

ይህ ብቻም ሳይሆን የኢንሹራንስ ዘርፉን ለውጭ ክፍት ለማድረግ ሪፎርም መደረግ እንዳለበትና ብዙ የሕግ ማዕቀፎች ጎን ለጎን መሠራት ስላለበት ሥራው በአሁኑ ወቅት ተጀምሯል። "

በሌላ በኩል ፦

የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ " ለውጭ ተወዳዳሪዎች " ክፍት እንዲሆን ከተወሰነ በኋላ በ2009 ዓ/ም የወጣው የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅ የማሻሻል ሥራ እየተጠናቀቀ እንደሆነ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል፡፡

የብሔራዊ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ፦

" ከአንዳንድ የድጋፍ ሰጪዎች ግብዓቶች ካሉ እየጠየቅን ነው፡፡

የብሔራዊ ባንክ ገዥው ከዚህ በፊት ባሉት መሠረት በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ለፓርላማ እናቀርባለን ተብሏል፡፡ ስለዚህ እየተፋጠነ ነው።

አዋጁ እንደወጣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ከሦስት እስከ አምስት ለሚጠጉ የውጭ ባንኮች ፈቃድ ይሰጣል ተብሎ ታቅዷል።

ቁጥሩ ከዚያ በላይ ከፍ የማድረግ ዕቅድ የለም፤ ይህም ከአቅም በላይ እንዳይሆን ከሚል ዕሳቤ ነው። " ሲሉ ተናግረዋል።

Credit - Ethiopian Reporter

@tikvahethiopia
#NBE

የውጭ ምንዛሬ ክፍፍል ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ የብሄራዊ ባንክ ቦርድ መወሰኑን " ካፒታል " ጋዜጣ ዘግቧል።

በዚህም ውሳኔ መሰረት የውጭ ምንዛሬ ክፍፍሉ ቀደም ሲል ከነበረው 70/30 ወደ 50/50 እንዲስተካከል ተደርጓል።

በውሳኔው መሰረት ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግኝታቸው 50 በመቶ ለብሄራዊ ባንክ 40 በመቶውን የውጭ ምነዛሬውን ላመነጨው አካል እንዲሁም ቀሪውን 10 በመቶ ለባንኮች እንዲከፋፈል ተወስኗል።

የብሄራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ፤ ቦርዱ የዋጋ ግሽበትን ለመግታት በርካታ የገንዘብ እና የፊሲካል ውሰኔዎችን ማሳለፉን እንዳሳወቁ " ካፒታል " ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NBE የውጭ ምንዛሬ ክፍፍል ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ የብሄራዊ ባንክ ቦርድ መወሰኑን " ካፒታል " ጋዜጣ ዘግቧል። በዚህም ውሳኔ መሰረት የውጭ ምንዛሬ ክፍፍሉ ቀደም ሲል ከነበረው 70/30 ወደ 50/50 እንዲስተካከል ተደርጓል። በውሳኔው መሰረት ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግኝታቸው 50 በመቶ ለብሄራዊ ባንክ 40 በመቶውን የውጭ ምነዛሬውን ላመነጨው አካል እንዲሁም ቀሪውን 10 በመቶ ለባንኮች እንዲከፋፈል…
#NBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፤ የዋጋ ንረትን ለማርገብ የሚያስችል የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያ ለማድረግ ወስኗል።

ይህ በተመለከተ የባንኩ ገዥ ማሞ ምህረቱ ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በመግለጫው ምን ምን ነጥቦችን አነሱ ?

- ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እያየለ የመጣውን የዋጋ ንረት ትርጉም ባለው መልኩ ለመቆጣጠር የብሔራዊ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ውሳኔ አሳልፏል።

- ከውሳኔዎቹ መካከል ለመንግስት የሚሰጠው የቀጥታ ብድር ባለፈው አመት ከተሰጠው ከ1/3ኛ እንዳይበልጥ ይደረጋል።

- መንግስት ቅድሚያ የግምጃ ቤት ሰነድ አማራጭን አሟጦ እንዲጠቀምና አማራጭ ሳይኖር ሲቀር ብቻ የቀጥታ ብድር ይጠቀማል።

- በ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት ሰኔ መጨረሻ የሃገር ውስጥ ብድር ዕድገት በ14 በመቶ ጣሪያ ይገደባል። ሁሉም ንግድ ባንኮች የብድር ዕድገት ዕቅዳቸውን በዚህ የብድር ጣሪያ መሰረት እንዲያስተካክሉ ይደረጋል።

- ባንኮች የገንዘብ እጥረት ሲገጥማቸው ከብሄራዊ ባንክ ከሚወስዱት ብድር የብድር ፋሲሊቲ ላይ የሚከፍሉት ወለድ ከ16 በመቶ ወደ 18 በመቶ ከፍ እንዲል ይደረጋል።

- ቁልፍ የሆኑ የወጪ ንግድ ላይ የተሰማሩ ዘርፎች በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ላኪዎችን ለማበረታታት ከዚህ ቀደም የነበረው የውጭ ምንዛሬ የማስተላለፍ ግዴታ ከ70/30 ወደ 50/50 እንዲሻሻል ይደረጋል። ላኪዎች 50 በመቶውን ለብሄራዊ ባንክ እንዲያስገቡ፣ 10 በመቶውን አብረው ለሚሰሩት ባንክ እንዲሰጡ እና 40 በመቶውን ለራሳቸው እንዲጠቀሙ ተወስኗል።

- በ2016 በጀት ዓመት መጨረሻ የዋጋ ንረቱ ከ20 በመቶ በታች እንዲሆንና በ2017 በጀት ዓመት ደግሞ ከ10 በመቶ በታች ለማውረድ ይሰራል።

ህብረተሰቡ ውሳኔውን በመደገፍ የዋጋ ንረቱን ለመቆጣጠር የሚደረገውን እርምጃ እንዲደግፍ ጥሪ ቀርቧል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#የብድር_ገደብ

ብሔራዊ ባንክ የጣለው የብድር ገደብ በባንኮች እና ተበዳሪዎች ላይ ተግዳሮት መፍጠሩ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ / #NBE ከጥቂት ወራት በፊት ያወጣው የገንዘብ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡

የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ዋነኛ ዓላማ ያደረገው ይህ ፖሊሲ ፣ የባንኮች የብድር ምጣኔ ካለፈው ዓመት ከ14 በመቶ በላይ እንዳይበልጥ ገደብ የጣለ ነው፡፡

በተለይ ባንኮች የሚሰጡት ብድር በገንዘብ ፖሊሲው ከተጣለባቸው ገደብ ጋር ለማጣጣም በማሰብ ቀደም ብለው የፈቀዷቸውን ብድሮች ጭምር ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ ወይም መሰል አሠራርን እንዲከተሉ እያደረጋቸው ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

ከመመርያው መውጣት ቀደም ብለው የተፈቀዱ ብድሮች ሊለቀቅላቸው እንዳልቻለ የተለያዩ ባለሀብቶችና የንግድ አንቀሳቃሾች ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ገልጸዋል።

በዚህም የተፈቀደላቸውን ብድር ታሳቢ በማድረግ የገቧቸው የቢዝነስ ስምምነቶች እየተፋረሱባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ቤትና ተሽከርካሪ ግዥ ውሎች ሳይቀሩ በእንጥልጥል እንዲቆዩ ማድረጉንም ከተበዳሪዎች መገንዘብ ተችሏል፡፡ 

ብድር እንዲለቀቅላቸው #ማረጋገጫ አግኝተው የነበሩት ተበዳሪዎች አሁን ላይ ብድሩን ማግኘት ለምን እንዳልቻሉ ለሚያቀርቡት ጥያቄ የሚያገኙት ምላሽ " አዲሱ የገንዘብ ፖሊሲ የጣለው የብድር ዕቀባ " መሆኑን ያስረዳሉ።

አንዳንዶቹም የተፈቀደላቸውን ብድር በትዕግሥት እንዲጠብቁ እንደተነገራቸው ያመለክታሉ፡፡

ቤት ለመግዛት ተዋውለው ከሚገለገሉበት ባንክ የፈቀደላቸውን ብድር እየተጠባበቁ የነበሩ አንድ ተበዳሪ ብድሩ እንደሚያገኙት በተገለጸላቸው ወቅት ሊለቀቅላቸው ባለመቻሉ የቤት ሽያጭ ውላቸው ሊፈርስባቸው እንደሆነ ገልጸዋል። እንዲህ ያለው ችግር በአብዛኛው በግል ባንኮች አካባቢ የሚስተዋል ነው፡፡

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-10-17

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#NBE

በቅርቡ በብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥና ዋና ኢኮኖሚሰት አቶ ፈቃዱ ደግፌ ተፈርሞ ለሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት በተላከ ደብዳቤ አገልግሎቱ የወለድ ክፍያ ያለበትን የብድር ውል ማዋዋል እንደማይችል ተገልጿል።

" የወለድ ክፍያ ያለበትን ብድር ማበደር የሚችለውና ገንዘብ መሰብሰብ የሚችለው ባንክና ማይክሮ ፋይናንስ ብቻ በመሆኑ፣ ግለሰቦች ወለድ በማስከፈል ማበደር አይችሉም " ሲሉ አቶ ፈቃዱ ደግፌ አስረድተዋል፡፡

በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ግለሰቦች ወይም ከፋይናንስ ተቋማት ውጪ ያሉ የንግድ ድርጅቶች፣ በመካከላቸው የሚያደርጉትን የወለድ ክፍያ ያለበትን ብድር ማዋዋል እንደሚቻልና እንደማይቻል ብሔራዊ ባንክን ጠይቆ እንደነበር ገልጸዋል፡፡

በዚህም መሠረት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰጠ የባንክ ወይም የአነስተኛ የፋይናንስ ሥራ ፈቃድ ካልተያዘ በስተቀር፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የባንክ ወይም አነስተኛ የፋይናንስ ሥራ መሥራት በሕግ የተከለከለ ተግባር ነው ሲል በደብዳቤው ተገልጿል፡፡

የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 እንደሚገልጸው፣ ብሔራዊ ባንክ ዕውቅና ከሰጣቸው የፋይናንስ ተቋማት ውጪ፣ ቁጠባ እንዲሰበስቡና ብድር እንዲሰጡ በልዩ ሕግ የተፈቀደላቸው የኅብረት ሥራ ማኅበራት ናቸው፡፡

ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች ፈቃድ በተሰጣቸው የፋይናንስ ተቋማት ሥራ በሕገወጥ መንገድ እንዲሰማሩና ሕገወጥ የፋይናንስ ሥርዓት ለመፍጠር የወጣ ሕግ አለመሆኑን፣ አገልግሎቱ ለብሔራዊ ባንክ የላከው ደብዳቤው ይገልጻል፡፡

ብሔራዊ ባንክም ከሕግ ድንጋጌዎች ውጭ በብድር መልክ ገንዘብ መሰብሰብና የብድር ተመን አውጥቶ በወለድ ማበደር፣ በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ የተሰጣቸው የፋይናንስ ተቋማት ሥራ ብቻ መሆኑን አስታውቋል፡፡

በተመሳሳይ መንገድ ገንዘብ የሚያበድሩ ግለሰቦች በወንጀል የሚያስቀጣቸው ተግባር በመሆኑ፣ በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ማንኛውም የወለድ ክፍያ ያለበት የብድር ውል ማዋዋል እንደሌለበት ብሔራዊ ባንክ ገልጿል፡፡

ከዚህ በፊት በወለድ ሲያበድሩ የነበሩ ግለሰቦች በምን ዓይነት መንገድ ሊጠየቁ እንደሚችሉ አቶ ፈቃዱ መረጃ እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡

የዚህ መረጃ ባለቤት " ሪፖርተር ጋዜጣ " ነው።

@tikvahethiopia
#NBE #CustomsCommission #LC

የኢትዮጵያ ብሔራዊ  ባንክ፣ በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጥያቄ መሠረት አስመጪና ላኪዎች በአንድ የባንክ ፈቃድ ከአንድ ጊዜ በላይ ምርት ወደ አገር ቤት እንዳያስገቡም ሆነ ወደ ውጪ እንዳይልኩ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ብሔራዊ ባንክ ጥቅምት 19 ቀን 2015 ዓ.ም. ለሁሉም ባንኮች የጻፈው ደብዳቤ እንደሚለው ፤ ኮሚሽኑ በወሰነው ውሳኔ አንዳንድ ላኪዎችና አስመጪዎች በአንድ የባንክ ፈቃድ በተለያየ ጊዜ ምርቶችን መላክና ማስመጣት የሚፈቅደውን ሕግ፣ የአገርን ጥቅም በሚያሳጣና በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀሙበት በመሆኑ አንድ LC (LETTER OF CREDIT) ለአንድ ምርት ብቻ እንዲሆን ሊያደረግ ነው።

ትዕዛዙ ተግባራዊ የሚሆነው ኅዳር 10 ቀን 2016 ዓ.ም. እነድሆነ ተገልጿል።

አስመጪና ላኪዎች ትዕዛዙ በአሁኑ ሰዓት በክፍልፋይ (Partial Shipment) መሠረት ስምምነት ያደረጉ ድርጅቶችን ያካተተ መሆን የለበትም ሲሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

እኚሁ አስመጪና ላኪዎች አንዳንድ ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር ያሰሩትን ስምምነት መቀየር እንደማይችሉና ትዕዛዙ ተግባራዊ መሆን ያለበት አዲስ ስምምነት ለሚያደርጉ ድርጅቶች መሆን እንደሚገባ ለብሔራዊ ባንክ ደብዳቤ እየላኩ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በባንኮች በኩል የሚከፈተው LC (LETTER OF CREDIT) በገዥና በአቅራቢ ድርጅት መካከል የሚደረግ ጠንካራ ስምምነት መሆኑ ይታወቃል፡፡

የክፍልፋይ ስምምነት (Partial Shipment) ማለት ገዥውና አቅራቢ በስምምነታቸው መሠረት በአንድ ጊዜ ሁሉንም ምርት በተለያየ ምክንያት መላክ ስለማይቻል ከሥር ከሥር እየተመረተ ለመላክ የሚስማሙበት አካሄድ ነው፡፡

አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በኮንቴይነር እጥረት፣ ገዥው በቂ ማከማቻ ቦታ ከሌለው፣ የክፍልፋይ ስምምነት ይደረጋል፡፡ ይህ ስምምነት ጥሬ ዕቃዎቹ በወቅቱ እንዲገቡ ያደርጋል እንጂ አገርን የሚጎዳ አይደለም ሲሉ አስመጪ ድርጅቶች ተናግረዋል፡፡

የአስመጪዎች ትልቅ ሥጋት የሆነው የክፍልፋይ ስምምነት (Partial Shipment) መሠረት የታዘዙት ዕቃዎች ጂቡቲ የሚደርሱት የጉምሩክ ኮሚሽን ውሳኔ ከሚጀመርበት ቀን በኋላ ነው፡፡

በአዲሱ ትዕዛዝ ቀድሞ ስምምነት የነበራቸውን በማካተቱ ምርቶቹ መጥተው ወደብ ላይ መዘግየት፣ የባንክ  ብድር መክፈል አለመቻል፣ የቀረጥ ክፍያ አለመስተናገድና ለተጨማሪ " ዴሜሬጅ " ክፍያ እንደሚያወጡ ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም ዕገዳው ቀድሞ ስምምነት የተደረገባቸውን ሳያካትት ከኅዳር 10 ቀን በኋላ ለሚደረግ አዲስ ስምምነት ፈቃድ መከልከል አለበት ብለዋል፡፡

በክፍልፋይ ጊዜ በአንድ የባንክ ፈቃድ በተለያዩ ወቅቶች ምርቶችን ማስገባት መፈቀዱ፣ አስመጪዎቹ ባንክ ከፈቀደላቸው የውጭ ምንዛሪ በላይ የሚያወጡ ምርቶችን የማስገባት ዕድሎችን እንደመፍጠሩ፣ በዚህም ባንኩ ከፈቀደላቸው ውጪ ጥቅም ላይ ያዋሉት ገንዘብ ከጥቁር ገበያ የተገኘ ነው የሚለውን ጥርጣሬ ከማሳደጉ ባለፈ፣ አሠራሩም ሕገወጥ ገበያን አበረታቷል በሚል የተላለፈ ትዕዛዝ ነው፡፡

በጉዳዩ ላይ  ማብራሪያ የሰጡት የዘርፉ ባለሙያ እንደሚሉት ከሆነ የክፍልፋይ ስምምነት (Partial Shipment) አገርን ችግር ውስጥ የሚከት አይደለም ብለዋል፡፡

ጉምሩክ ኮሚሽን ሕገወጥ ተግባርን ለመከላከል የሚፈልግ ከሆነ በቀላሉ ሕገወጦቹን በመለየት በሕግ መጠየቅ እንጂ በትክክለኛ አካሄድ የሚሠሩትንም በአንድ ላይ በማገድ መፍትሔ አይመጣም ሲሉ ገልጸዋል፡፡

የዚህ መረጃ ባለቤት ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia
#NBE

ብሔራዊ ባንክ " ሪፖርተር ጋዜጣ " ላይ ወጥቷል ባለው አሳሳች ዘገባና አሉባልታ ምክንያት በዋጋ ላይ የሚፈጠር ማንኛውም ሰው ሠራሽ #ጭማሪ ተቀባይነት የለውም፤ ጥብቅ ክትትልም ይደረጋል ብሏል።

ብሔራዊ ባንክ ምን አለ ?

-  በጋዜጣዊ በህዳር 23/2016 እትም ብሔራዊ ባንክ ባለፈው ሳምንት የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለፓርላማ የፕላን፤ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ከአንድ የፓርላማ አባል ቀረበ ከተባለ አስተያየት ላይ ተነሥቶ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ተመን ላይ በቅርብ ጊዜና በከፍተኛ ደረጃ ለውጥ ለማድረግ ማቀዱን በማስመልከት የወጣው ዘገባ ፈጽሞ ሐሰተኛና አሳሳች፣ ከጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ያፈነገጠ ድርጊት ነው ብሏል።

- " ለፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ ጉዳዮን በተመለከተ የቀረበ ዕቅድ የለም " ሲል ገልጿል።

- እስከ 4 ስዓት በፈጀው ውይይት ወቅት በብሔራዊ ባንክ የተነገረ ነገር እንደሌለ ህብራተሰቡ መረዳት አለበት ብሏል።

- በዚህ አሳሳች ዘገባና አሉባልታ ምክንያት በዋጋ ላይ የሚፈጠር ማንኛውም ሰው ሠራሽ ጭማሪ ተቀባይነት የለውም ጥብቅ ክትትልም ይደረጋል ብሏል።

በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ የወጣው ዘገባ ምን ይላል ?

- ብሔራዊ ባንክ በሕጋዊውና በጥቁር ገበያው መካከል ያለውን ሰፊ የውጭ ምንዛሪ ተመን ልዩነት #በ95_በመቶ ለማጥበብ ዕቅድ መያዙ መታወቁ ፤ ይህ ዕቅድ ግን መቼና እንዴት እንደሚፈጸም የታወቀ ነገር እንደሌለ ያስረዳል።

- ይህ ባንኩ ዕቅድ የተሰማውም ኅዳር 19 ቀን 2016 ዓ/ም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የብሔራዊ ባንክን የ2016 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመርያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም በገመገመበት ወቅት ነው ብሏል።

- ብሔራዊ ባንክ ይህንን ዕቅዱን በቋሚ ኮሚቴው የግምገማ መድረክ ላይ #በይፋ_ባያቀርብም፣ ለቋሚ ኮሚቴው የቀረበን #ሰነድ የተመለከቱ አንድ የም/ ቤት አባል፤ ዕቅዱን ከሪፖርቱ ላይ እንደተመለከቱ ጠቅሰው ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

የም/ቤቱ አባሉ ምን አሉ ?

" ብሔራዊ ባንክ በሕጋዊው የውጭ ምንዛሪ ተመንና በጥቁር ገበያው መካከል ያለውን ልዩነት በ95 በመቶ የማቀራረብ ዕቅድ ይዟል።

ነገር ግን በአሁኑ ወቅት በሕጋዊው የምንዛሪ ተመንና በጥቁር ገበያው መካከል ያለው ልዩነት እጥፍ ነው።

ስለዚህ ልዩነቱን በ95% ለማጥበብ የተያዘው ዕቅድ በተጨባጭ የሚቻል ነው ወይ ? ወይስ ዲቫሉዌሽን ለማድረግ (የብርን የመግዛት አቅም ለማዳከም) አስባችኋል? " ሲሉ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

- የብሔራዊ ባንክ ዋና ገዥ አቶ ማሞ ምሕረቱ፤ "እንደየ ሁኔታው እየተመዘኑ የሚወሰዱ ዕርምጃዎች ይኖራሉ እንጂ በዚህ ወቅት ይህ ዕርምጃ ይወሰዳል ብሎ ብሔራዊ ባንክ ሊናገር አይችልም "  የሚል ምላሽ መስጠታቸው በጋዜጣው ላይ ሰፍሯል።

- አቶ ማሞ " የውጭ ምንዛሪ ጉዳይን በተመለከተ ሁሉን ነገር እዚህ መናገር አልችልም። ብሔራዊ ባንክን በሚመለከቱ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ የምናደርገው ውይይት ተገቢ ላልሆነ ስፔኩሌሽን (ግምት) የሚያጋልጥ መሆን የለበትም። ገና ጥናት ያልተደረገበት ጉዳይ ላይ ብንወያይም ትርጉም የለውም። ዋናው ቁልፍ ነገር ዓላማችን ላይ መወያየት ሊሆን ይገባል። የባንኩ ዋና ዓላማ የተረጋጋ የዋጋ ሁኔታና የተረጋጋ የውጭ ምንዛሪ ሥርዓት እንዲኖር ማስቻል ነው " ማለታቸውንም ጋዜጣው አስፍሯል።

ብሔራዊ ባንክ ይህን ዘገባ ነው #አሳሳችና #አሉባልታ ነው ያለው።

$ በአሁኑ ወቅት የዶላር ሕጋዊው የውጭ ምንዛሪ ተመን 55.5 ብር የደረሰ ሲሆን፣ በጥቁር ገበያው ግን አንድ ዶላር እስከ 110 ብር እየተመነዘረ ይገኛል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ የዲጂታል ባንክ አግልግሎት ሙሉ በሙሉ መጀመሩን ገለጸ። ባንኩ ፤ በሲስተም ችግር ምክንያት ፦ - በቅርንጫፎች፥ - በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ - በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሞ እንደነበር አስውሷል። በቅርንጫፍ እና በኤቲኤም የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀደም ብለው መጀመራቸውን ገልጾ አሁን ደግሞ በዲጂታል የሚሰጡ የባንክ አገልግሎቶች…
#Update #CBE #NBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ትላንት ባጋጠመው ችግር የደንበኞች መጉላላትን ጨምሮ የደረሱ #ጉዳቶች ስለመኖራቸው ተነግሯል።

ጉዳቶቹ ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ለህብረተሰቡ ይገለጻሉ ነው የተባለው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መጋቢት 7 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ  ስርዓት ላይ ያጋጠመውን ችግርና የአገልግሎት መቋረጥ በተመለከተ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።

" ባንኮች በሥርዓቶቻቸዉ ላይ በየጊዜዉ የደህንነት ፍተሻ እንዲሁም የማሻሻያ ሥራዎችን ያከናዉናሉ " ያለው ብሔራዊ ባንክ ፤ " በሥርዓቶቹ ላይ በሚከናወን ለዉጦችና ፍተሻዎች የባንኮች አገልግሎት አልፎ አልፎ ሊቋረጥ ይችላል " ብሏል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትናንትና ዕለት የተከሰተዉ የአገልግሎት መቋረጥ ከዚሁ ጋር የተያያዘ መሆኑን #አረጋግጫለሁ ሲል ገልጿል።

ችግሩ ከተከሰተበት ሰዓት አንስቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የባንኩን እና የደንበኞቹን ደህንነት ለማረጋገጥ ከፍተኛ ክትትል ሲያደርግ እንደቆየና በተደረገው ርብርብ አገልግሎቶች እንዲመለሱ መደረጉን ጠቁሟል።

ብሔራዊ ባንክ በዚሁ መግለጫ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባጋጠመው ችግር #ጉዳቶች እንደደረሱ ጠቁሟል።

ስለ ጉዳቶቹ በዝርዝር ያለው ነገር ባይኖርም አስፈላጊው ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ለህዝብ ይገለጻል ብሏል።

በተፈጠረው ችግር የደንበኞች መጉላላትም መከሰቱን አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፋይናንስ ተቋማት ላይ በየጊዜዉ ክትትልና ቁጥጥር እንደሚያደርግ አመልክቶ በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ ያሉ በሁሉም የፋይናንስ ተቋማት የሚገኙ የፋይናንስ ሥርዓቶች ደህንነቸዉ የተጠበቀ ነው ብሏል።

" ህብረተሰቡ ያለምንም ስጋት የፋይናንስ አገልግሎቶችን መጠቀም መቀጠል ይችላል " ሲል አሳውቋል።

የፋይናንስ ተቋማትም የሥርዓቶቻቸዉን ደህንነትና ቀልጣፋነት ይበልጥ ለማሳደግ የቴክኖሎጂ ተለዋዋጭ ባህርይ በማየት በቀጣይነት መሥራት እንደሚኖርባቸዉ #ጥብቅ_ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

@tikvahethiopia
#NationalBankofEthiopia

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት የባንክ ስራን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ 5 መመሪያዎችን እንዳሻሻለ አሳውቋል።

እነዚህ መመሪያዎች በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች የተመደቡ ናቸው።

በመጀመሪያው ምድብ የሚካተቱት ፦

- “ የብድር ተጋላጭነት ጣሪያ ስለመወሰን”፤
- “ከባንኩ ጋር ዝምድና/ግንኙነት ባላቸው ወገኖች አማካኝነት ስለሚኖር የብድር ተጋላጭነት”
- “ስለንብረት ምደባ እና ለተዛማጅ ስጋቶች ስለሚያዝ የመጠባበቂያ ፕሮቪዥን ” የተመለከቱ መመሪያዎች ናቸው።

በ2ኛው ምድብ የሚካተቱት መመሪያዎች በባንክ ውስጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አካላት ሊያሟሏቸው ስለሚገቡ መስፈርቶች እና የኩባንያ አስተዳደርን የሚመለከቱ ናቸው።

ከተደረጉ ማሻሻያዎች አንዱ ...

በከፍተኛ የብድር ተጋላጭነት ገደብ መመሪያ ላይ ማሻሻያ ተደርጓል።

የመመሪያው ዓላማ አንድ ተበዳሪ (ተያያዥነት ያላቸው ወገኖችን ጨምሮ ) ከባንኩ ጋር በገባው ውል መሠረት ግዴታውን መወጣት ባለመቻሉ ምክንያት በባንኩ ላይ ሊደርስ የሚችለውን ኪሳራ ለመቀነስ እና የባንኮች የተጋላጭነት መጠንን በወቅቱ ለመቆጣጠር የሚያስችል በቂ ፖሊሲ እና አሠራር እንዲኖራቸው ለማድረግ እንደሆነ ተገልጿል።

መመሪያው በባዝል መርህ መሠረት ማንኛውም ባንክ ለአንድ ወይም ተያያዥነት ላላቸው ደንበኞች የሚኖረው አጠቃላይ የብድር ተጋላጭነት ከባንኩ ጠቅላላ ካፒታል ከሀያ አምስት በመቶ (25%) እንዳይበልጥ ገድቧል፡፡

ይህ መመሪያ ተያያዥነት ያላቸው አካላት እንደ አንድ የባንክ ተበዳሪ ሆነው እንዲቆጠሩ ይደነግጋል።

(ተጨማሪ ማሻሻያዎችን ከላይ በተያያዘው ምስል ያንብቡ)

#NBE #TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalBankofEthiopia የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዛሬው ዕለት የባንክ ስራን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ 5 መመሪያዎችን እንዳሻሻለ አሳውቋል። እነዚህ መመሪያዎች በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች የተመደቡ ናቸው። በመጀመሪያው ምድብ የሚካተቱት ፦ - “ የብድር ተጋላጭነት ጣሪያ ስለመወሰን”፤ - “ከባንኩ ጋር ዝምድና/ግንኙነት ባላቸው ወገኖች አማካኝነት ስለሚኖር የብድር ተጋላጭነት” - “ስለንብረት…
#NBE #Ethiopia

የብሔራዊ ባንክ የሕግ ማሻሻያ ፦

ከባንክ ጋር #ተዛማጅነት_ላላቸው_አካላት የሚሰጥ የብድር ተጋላጭነት ገደብ መመሪያ ላይ የሕግ ማሻሻያ ተደርጓል።

የዚህ መመሪያ ዓላማ አንድ ባንክ ተዛማጅነት ካላቸው አካላት ጋር በሚያደርገው ግንኑነት ብድር አግባብነት በሌለው መንገድ እንዳይሰጥ ለማድረግ ፣ የጥቅም ግጭት ለመቀነስ እንዲሁም ደግሞ ተዛማጅነት ካላቸው አካላት ጋር ባንኮች የሚያደርጉትን ማንኛውም ግብይት በተመለከተ በቂ የሆነ ክትትል ለማድረግ እና ያለ አድልዎ በተገቢው መንገድ የተሰጠ መሆኑን ለማረጋገጥ ነው።

ይህ መመሪያ በዋነኛነት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን #ገደቦች_ጥሏል

ሀ) በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከባንክ ጋር ተዛማጅነት ላላቸው አካላት በማንኛውም ጊዜ የሚኖረው አጠቃላይ የብድር ተጋላጭነት ከባንኩ ጠቅላላ ከፒታል ከ15% እንዳይበልጥ፤

ለ) በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከባንክ ጋር ተዛማጅነት ላላቸው አካላት በሙሉ በማንኛውም ጊዜ የሚኖር አጠቃላይ የብድር ተጋላጭነት ከባንክ ጠቅላላ ካፒታል ከ35% እንዳይበልጥ፤

ሐ) አንድ ባንክ ተዛማጅ ከሆኑ ወገኖች ጋር ግብይት ሲፈጽም ከማናቸውም ተዛማጅ ካልሆኑ ወገኖች ጋር ግብይት ሲፈጽም ተግባራዊ በሚደረግ ሁኔታዎች ጋር ተመሳሳይ በሆነ መልክ እንዲሆን እና ከዚህ በተለየ ሁኔታ እንዳይፈጸም ይደነግጋል።

https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/88218?single

#የኢትዮጵያ_ብሔራዊ_ባንክ

@tikvahethiopia
#Ethiopia የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ ይፋ አድርጓል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

#NBE

@tikavhethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ ይፋ አድርጓል። (ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል) #NBE @tikavhethiopia
#Ethiopia

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ካደረገው አዲሱ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ ፦

" የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለባንኮች የአንድ ቀን የብድር አገልግሎት (overnight lending facility) እና የአንድ ቀን የተቀማጭ ገንዘብ አገልግሎት (overnight deposit facility) ይስጣል፡፡

እነዚህ የአንድ ቀን የብድር ወይም የተቀማጭ አገልግሎቶች የሚሰጡበት ምክንያት ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ፍሰት አቋማቸውን ለማስተካከል እንዲረዳቸው ነው፡፡

እነዚህ ቋሚ አገልግሎቶች የሚሰጡት ከብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን 3 በመቶ በማስበለጥ ወይም በማሳነስ ይሆናል፡፡ "

#NBE #Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አሳውቋል። (ሙሉ መግላጫው ከላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
" 10.7 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ተገኝቷል " - ብሔራዊ ባንክ

ብሔራዊ ባንክ ፥ 10.7 ቢሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ከውጭ አጋሮች መገኘቱን አሳውቋል።

ባንኩ " የሽግግር ወቅት ወጪዎችንና የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ የሚያስከትላቸውን ጫናዎችን ለመቀነስ የሚረዳ 10.7 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ትልቅ የገንዘብ ድጋፍ ከውጭ አጋሮች ተገኝቷል " ብሏል።

የገንዘብ ድጋፉ ከዓለም የገንዘብ ድርጅት (#IMF) ፣ ከዓለም ባንክ (WB) እና ከአበዳሪዎች የሚገኘውን እንደሚጨምር አመልክቷል።

ነገር ግን፣ በሁለትዮሽ የማዕከላዊ ባንክ ተቀማጭ (central bank deposits) እና በከረንሲ ልውውጥ (currency swap) መልክ የሚመጣውን 2.8 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንዲሁም ከዓለም ባንክ፣ ከዓለም አቀፍ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) እና ከሌሎች ባለብዙ ወገኖች (multilaterals) ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀውንና በሃደት ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካላት ይፋ የሚደረገውን ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ አያካትትም ብሏል።

ብሔራዊ ባንክ " በዓለም የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የሚለገሰው ልዩ የገንዘብ እርዳታ የመንግሥትን የሪፎርም ሥራዎችን ጥንካሬ ያገናዘበና በአፍሪካ አህጉር ትልቁ ከሚባሉት የገንዘብ እርዳታዎች አንዱ ነው " ብሎታል።

#NBE #Ethiopia

@tikvahethiopia
FXD012024-FOREIGN-EXCHANGE-1-1.pdf
22.8 MB
NATIONAL BANK OF ETHIOPIA FOREIGN EXCHANGE DIRECTIVE NO. FXD/01/2024

በዚህ መመሪያ መሰረት የውጭ ምንዛሪ ማግኘት የሚችሉት እነማን ናቸው ?

➡️ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት የተፈቀደላቸው የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ከኢትዮጵያ ውጭ የሚጓዙ ኢትዮጵያዊውያን ወይም በአገሪቱ ውስጥ የሚኖር የውጭ ዜጎች ናቸው።

➡️ ምንዛሪ ለማግኘት የሚፈልጉ ግለሰቦች ለበዓል ፣ ለትምህርት ፣ ለህክምና ጉዞዎች እና ሌሎች የግል ጉዳዮች እንደሚጓዙ የሚያሳይ ፓስፖርት፣ ሕጋዊ የመግቢያ ቪዛ እና የአየር ትኬት የማቅረብ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

➡️ ተጓዦች ከምንዛሪ ቢሮዎች እስከ 5 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ወይም የዚህ አቻ የሆነ የሌላ አገር ገንዘብ በጥሬ ወይም በክፍያ መፈጸሚያ ካርድ (debit card) አማካኝነት ማግኘት ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ የባንክ ሂሳብ ያላቸው ተጓዦች እስከ 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ድረስ ማግኘት ተፈቅዶላቸዋል።

በብሔራዊ ባንክ ካልተፈቀደ በስተቀር ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነዋሪ በአንድ ጉዞ ላይ ከ10,000 የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ ገንዘብ በካሽ መያዝ አይችልም።

➡️ ለንግድ የሚጓዙ ግለሰቦችም የውጭ ምንዛሪ ማግኘት ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ፣ ፓስፖርት እና የአየር ትኬት ለሚያቀርቡ ለንግድ ድርጅት ተወካዮች የውጭ ምንዛሪ መሸጥ እንዲችሉ ተፈቅዷል። እነዚሁ ቢሮዎች ፦
- ለንግድ ድርጅቶች፣
- ለበጎ አድራጎት ተቋማት
- ለሃይማኖት ማኅበራት፣
- ለንግድ ትርኢቶች፣
- ለቱሪዝም
- ለባህል እና ለስፖርቶች አዘጋጆች የውጭ ምንዛሪ መሸጥ ይችላሉ።

➡️ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ለመንግሥት ተጓዦች ለምግብ፣ ለማረፊያ እና ሌሎች ተያያዥ ወጪዎች ከ10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ ገንዘብ የማይበልጥ የውጭ ምንዛሬ ሊሸጡ ይችላሉ።

➡️ ነዋሪ ላልሆኑ የውጭ አገር ዜጎች እና ቱሪስቶች ብርን ወደ ውጭ ምንዛሬ ሊለውጡ የሚችሉበት አሠራርም አለ። ፓስፖርት፣ ትክክለኛ ቪዛ እና የአየር ትኬት የሚያቀርቡ ሰዎች ያለማስረጃ እስከ 500 የአሜሪካን ዶላር መለወጥ ይችላሉ። ከ500 ዶላር በላይ መለወጥ የሚፈልጉ ከሆነ ፓስፖርት፣ ሕጋዊ ቪዛ፣ የአየር ትኬት እና ተመጣጣኝ የሆነው የውጭ ምንዛሪ በሕጋዊ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ገንዘብ መቀየሩን የሚያሳይ የተረጋገጠ የባንክ ማስረጃ ማቅርብ ይጠበቅባቸዋል።

ተጨማሪ ከላይ ተያያዘውን ፋይል ከፍተው ያንብቡ !

#NBE #BBC #Ethiopia

@tikvahethiopia