TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዱላ አታቀብሉ፤ አታጋግሉ!⬇️

የኦነግ አመራሮች አቀባበል #ያማረ እንዲሆን እና የኦነግ ደጋፊ የሆኑ ወንድሞች ደሥ እንዲላቸው ማገዝ #ተገቢ ነው። ከፀቡ በፊትም በሰከነ
መንገድ #ተነጋግሮ መግባባት መልመድ አለብን። አላሥፈላጊ የሆነ #ፉክክር እና #ብሽሽቅ አያሥፈልገንም።

ለወጣቱ ለባለፉት 27 ዓመታት ሲሰበክለት የኖረው #ልዩነት እንጅ ወንድማማችነት እና መተባበር አይደለም። ሥለዚህ በትንሽ ነገር ወደፀብ ለማምራት ቀላል ሆኗል። ጦር ለማወጅም ማሰላሰል አያሥፈልግም። #ሞባይልን ወጣ አድርጎ መተኮሥ ነው። ሃላፊነት የማይሰማው እና #ቢራ እየጠጣ "አትነሳም ወይ" የሚል ብዙ ነው። የእብድ ገላጋዩ እና ዱላ አቀባዩ የትየለሌ ነው። የሚመክር እና አንተም ተው፣ አንተም ተው የሚል ነው የሚያሥፈልገን። በዚህ የተነሳም ሰፊው መንገድ ይጠበናል። #የምንፈልገውን ባንዲራ ለመሥቀል ሌላውን ማውረድ ተገቢ አይደለም።

ሌሎችም የሚፈልጉትን እና #አርማየ ነው የሚሉትን ቢሰቅሉ የሌላውን #መብት እሥካልነኩ ድረሥ #መብታቸው ነው። ሥንተባበር ሁሉም #ቀላል ይሆናል። ሆደ ሰፊነት ያሥፈልጋል።

ፌሥቡክ ላይ የምታጋግሉ ሰከን በሉ!
.
.
ከዳንኤል ተፈራ (የቀድሞው የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰው ክቡር ነው! #ፈጣሪን ካከበርክ ሰውን #ታከበራለህ። ሰውን ስታከብር ብሄሩን፣ ማንነቱ፣ ቋንቋውን፣ ባህሉን እና ሀሳቡን እንዲሁም የኔ መገለጫ ነው የሚለው ነገር ሁሉ ታከብራለህ። የቱንም ያህል #ልዩነት ቢኖር #ሰውነት ሁሉንም ልዩነት ባዶ ያደርገዋል። ሰውነት #ይቅደም! ሰው እንደሰው ከተከበረ የሰውየው የሆኑ ነገሮች ሁሉ ይከበራሉ። አክቲቪስት ነን ባዮች፤ ፖለቲከኞችም ጭምር በዚህ ወቅት ከምንም ነገር በፊት ለወጣቱ ልታስተምሩት የሚገባው ስለሰው ክቡርነት መሆን አለበት። ሰው ሲከበር #ግጭት አይኖርም፤ ሰው ሲከበር ጥላቻና ክፋት አይኖርም! ሰው መሆን ይከበር!
.
.
#ETHIOPIA
ፀጋአብ ወልዴ~ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ🔝

‹‹እኛ ተማሪዎች ለህዝባችን አንድነት ምሰሶ ፤ #ለችግሮቻችን መፍቻ ቁልፍ እንጂ ለቁርሾዎች መነሻ መሆን የለብንም። ተማሪዎች ህዝባችንን #በድህነት ያስቀሩ ድክመቶቻችን የምንቀርፍ ኃይሎች እንጂ የቁርሾ መመስረቻዎች መሆን አንፈልግም፡፡›› የደብረ ማርቆስ ተማሪዎች

ተማሪዎቹ በትላንትናው ዕለት ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ #አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሀሳቦች ተነስተዋል፡፡

• የአማራ እና ኦሮሞ ህዝቦች አንድነት #ለኢትዮጵያውያን ደኅንነት እንዲሆን አሻራችንን እናሳርፋለን ። እኛ አንድ ህዝቦች ነን ። አንድ ህዝብ መሆናችን ዩኒቨርሲቲዎች ምሳሌ እንዲሆኑ እንሰራለን ።

• እኛ ተማሪዎች ህዝባችንን በድህነት ያስቀሩ ድክመቶቻችን የምንቀርፍ ሀይሎች እንጂ የቁርሾ መመስረቻዎች መሆን አንፈልግም።

• ወደ ቤተሰቦቻችን ይዘን የምንመለሰው #ፍቅር እና #መፍትሄን እንጂ #ልዩነት አይሆንም።

• የምንማረው ህዝባችንን በፍቅር ለመምራት ነው ፤ #አንድነታችንን የሚያሳጡ ሀሳቦች እንዳይተባበሩ እናድርግ።

• ደም የመተካኪያ ፍሬ እንጂ ከዛሬ በኋላ የልዮነት ሀሳብ ሁኖ #ለሚከፋፍሉን እድል ሰጥቶ ወደኋላ የሚመልሰን ሊሆን አይገባም።

በደም ተለያይተን በድህነት ውስጥ መኖር በለውጡ ትውልድ አይቀጥልም፤ የሚል ሰላማዊ ሰልፍ ግቢያቸው ላይ በማድረግ ሀሳባቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
40/60‼️

ከስድስት አመታት በፊት #ምዝገባው የተካሄደው የ40/60 የጋራ የመኖሪያ ቤት ፕሮጀክት አሁን ለባለ ዕድለኞች የሚወጣበት ቀን ተቃርቧል። ይሁንና ጉዳዩ ይመለከተናል በሚሉ ሶስት የመንግስት ተቋማት መካከል በዕጣው ማን ይካተት በሚለው ጉዳይ ዙሪያ መግባባት አልተቻለም። የአዲስ አበባ መስተዳድር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስቴር በመካከላቸው የተፈጠረው #ልዩነት ሊፈታ ባለመቻሉ ጉዳዩ ወደ ጠቅላይ ሚንስትር ፅህፈት ቤት አምርቷል።

Via wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia