TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና‼️መሳሪያ ታጥቀው ቤተ መንግስት ከገቡት ወታደሮች መካከል 66ቱ ከ5 ዓመት እስከ 14 ዓመት በሚደርስ ፅኑ #እስራት ተቀጡ። ወታደሮቹ በወታደራዊ ፍርድ ቤት #በግልፅ ችሎት #መዳኘታቸውን የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኦቦ ለማ መገርሳ!

#በመንግስት ላይ የሚያያቸውን ጉድለቶች ሕዝቡ #በግልፅ በመናገር እንዲታረሙ ማድረግ አለበት ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ለማ መገርሳ ተናገሩ፡፡

Via Sheger FM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም

Ethio-Telecom በምን ምክንያት #የቴሌግራም አገልግሎትን #ሊያግድ እንደቻለ በቂና አሳማኝ ማብራሪያ #በግልፅ ሊሰጥ ይገባል። መሰል ድርጊቶች ዜጎች በመንግስት ላይ ያላቸውን #እምነት ይሸረሽረዋል። ድርጅቱ የተቋረጠው የኢንተርኔት አገልግሎት ተመልሷል ቢልም ቴሌግራም ያለproxy server/VPN ውጪ እንደታገደ ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሳዑዲ_አረቢያ የሳዑዲ አረቢያ መንግስት በሪያድ የቀስተደመና ቀለም ያላቸውን እቃዎች ከሱቆች እና ከመደብሮች እየሰብሰበ ይገኛል። የሳዑዲ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ያስተዋውቃል በሚል የቀስተደመና ቀለም ያላቸውን አሸንጉሊቶች፣ ቲሸርቶች፣ የጸጉር ማስያዣዎች፣ ኮፊያ፣ እና የእርሳስ መያዣወችን ከየመደብሩ እንዲሰበሰቡ እያደረገ ነው። የሀገሪቱ መንግስት ህፃናትን ለመጠበቅ ሲል " መርዛማ መልዕክት…
" እኛ የሙስሊም ሀገር ነን። ባህሎች እና ወጎች አሉን እናም እስልምና እነዚህን ድርጊቶች (የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን) ይከለክላል " - አል ሃማሚ

ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንዲሆንና ከፍተኛ የሆነ ቅጣት እንዲጣል እየሰራች መሆኗን አሳውቃለች።

የኢራቅ መንግስት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት የሚከለክል ህግ ለማፅደቅ ማቀዱን አስታውቋል።

ኢራቅ በመካከለኛው ምስራቅ ከሚገኙ ሶስት ብዙ አረቦች ከሚኖሩበት ሀገር መካከል አንዷና የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን #በግልፅ ወንጀል እንደሆነ ካላወጁ ሀገራት የምትጠቀስ ናት፤ ሌሎቹ ጆርዳን እና ባህሬን ናቸው።

ምንም እንኳን በግልፅ ወንጀል ነው ተብሎ ባይገለፅም ድርጊቱ በማህበረሰቡ ዘንድ እጅግ በጣም የተወገዘ ነው።

አሁን ያለው ሁኔታ ያላማራት ኢራቅ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ወንጀል እንደሆነ በህግ ለመደንገግ እየሰራች ሲሆን ህጉ ከወጣ ኢራቅ ሌሎች ድርጊቱን በህግ ወንጀል እንደሆነ ካፀደቁ ሀገራት ተርታ ትሆናለች።

አብዛኛዎቹ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን በቀጥታ በግልፅ የሚከለክሉ እና ወንጀል ነው ያሉ ሲሆን ከገንዘብ ቅጣት እስከ እስራት ፤ ሳውዲ አረቢያ ደግሞ #የሞት_ቅጣት ትቀጣለች።

በኢራቅ ፓርላማ የህግ ኮሚቴ ውስጥ ያሉት የፓርላማ አባል አሬፍ አል ሃማሚ ለDW በሰጡት ቃላቸው ፥ " አዲሱ ህግ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ያላቸውን በወንጀል ተጠያቂ ያደርጋል ፤ በእነሱ ላይም ከባድ ቅጣት ይጥላል " ብለዋል።

ህጉ እስካሁን ድምጽ ያልተሰጠበት ሲሆን ድምፅ እንዲሰጥበት እየተሰራ ነው።

አል ሃማሚ ፤ ከሀገር ውስጥ እና ከዓለም አቀፍ #የሰብአዊ_መብት_ተሟጋች_ድርጅቶች ትችት ቢሰነዘርም ህጉ ይፀድቃል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

ያንብቡ telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-07-19

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አቶ አብዱ ሁሴን የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር ሆነው ተሹመዋል። ዶክተር አህመዲን መሐመድ  ደግሞ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ እና የከተማ እና መሰረተ ልማት ቢሮ ኅላፊ  ሆነው መሾማቸው ተን ከዚህ በተጨማሪ የባህር ዳር ከንቲባው ዶክተር ድረስ ሳህሉ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ሆነው…
" ኃላፊነቱን ከመቀበል ውጭ አማራጭ ባለመኖሩ ተቀብያለሁ " - አቶ አረጋ ከበደ

አዲሱ አማራ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ አረጋ ከበደ ፤ ከሹመቱ በኃላ ባሰሙት ንግግር ወደ ኃላፊነት የመጡበት ወቅት ፈታኝ እና የጋራ ትብብርን የሚጠይቅ መሆኑን ገልጸዋል።

" ክልሉ አሁን ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ ለሁሉም ግልጽ ነው " ያሉት አቶ አረጋ " ኃላፊነቱን ከመቀበል ውጭ አማራጭ ባለመኖሩ ተቀብያለሁ " ብለዋል።

በኃላፊነት ዘመናቸው ክልሉ አሁን ካለበት ዘርፈ ብዙ ችግሮች አውጥቶ የተሻለ እና የተረጋጋ ክልል ለማድረግ የሚችሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

አቶ አረጋ ከበደ በንግግራቸው የህዝቡ የዘመናት ጥያቄና ጥቅም ላይ ያልተገባ ንግግር የሚያደርጉ ቡድኖች ድርጊታቸው ከትንኮሳ አይለይም ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ አረጋ ፤ " በክልሉ የተፈጠረውን ወቅታዊ ችግር እንደአጋጣሚ በመውሰድ በክልሉ ሕዝብ የዘመናት ጥያቄ እና ጥቅም ላይ ተገቢ ያልሆነ ንግግር የሚሰነዝሩ ቡድኖች ድርጊታቸው ከትንኮሳ የማይለይ መሆኑን ማወቅ ይገባቸዋል " ብለዋል።

የክልሉ መንግሥት ሕጋዊ የፌዴራል መንግሥት ውሳኔ የሚጠብቅ እንጂ ሕዝብ የጠየቀውን ጥያቄ የሚዘነጋ እንዳልሆነ ሊገነዘቡ ይገባል ብለዋል።

የክልሉ ፕሬዜዳንት በንግግራቸው " የሚያደርጉትን ያልተገባ ንግግር ከትንኮሳ ለይተን አናያውም " ያሏቸው የትኞቹን ቡድኖች እንደሆነ #በግልፅ ስም ጠርተው አልተናግሩም።

@tikvahethiopia