TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ፓርላማ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 6ኛውን፣ 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 28ኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡

ምክር ቤቱ በስብሰባው የ27ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ-ጉባዔን መርምሮ አጽድቋል፡፡

የምክር ቤት አባላትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌደራል መንግስት የ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

Via HoPR

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓርላማ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 6ኛውን፣ 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 28ኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡ ምክር ቤቱ በስብሰባው የ27ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ-ጉባዔን መርምሮ አጽድቋል፡፡ የምክር ቤት አባላትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌደራል መንግስት…
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣናቸውን ለቀው ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክቡ ፓርላማውም እንዲበተን ጠየቁ።

ዶ/ር ደሳለኝ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ቀውስ ውስጥ መሆኗን እና ለዚህም የዳረጋት " የብልፅግና መራሹ መንግስት እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወደቀ አመራር " ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ሀገሪቱን ከዚህ ችግር ለማውጣት የሀገራዊ ቀውስ መፍትሄ አፈላላጊ ጉባኤ እንዲዘጋጅ ጠይቀዋል።

ብልፅግናም ሆነ ፓርላማው ሀገሪቱን ከቀውስ ማውጣት ስለማይችሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣናቸውን ለጊዜያዊ የሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክቡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም በኢፌዴሪ ህገመንግስት አንቀፅ 60 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት በምክር ቤቱ ፍቃድ ምክር ቤቱን እንዲበትኑ እና ለአዲስ ምርጫ መንገዱን እንዲጠርጉ ጠይቀዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣናቸውን ለቀው ለሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክቡ ፓርላማውም እንዲበተን ጠየቁ። ዶ/ር ደሳለኝ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ቀውስ ውስጥ መሆኗን እና ለዚህም የዳረጋት " የብልፅግና መራሹ መንግስት እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወደቀ አመራር " ነው ሲሉ ተናግረዋል። ሀገሪቱን ከዚህ ችግር ለማውጣት የሀገራዊ ቀውስ መፍትሄ አፈላላጊ ጉባኤ እንዲዘጋጅ…
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ምን አሉ ?

የተ/ም/ቤት አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፦

" ጠ/ሚ ዐቢይ ወደ መንበረ ስልጣን ከወጡበት ከመጋቢት 2010 ዓ/ም ጀምሮ እየተወሳሰቡ የሄዱት የሀገራችን ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች አሁን ላይ ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ መሸጋገራቸውን ማሸፋፈን ወደማይቻልበት ደረጃ ደርሰዋል።

ብልፅግና መራሹ መንግስትዎ ፦
- የኢትዮጵያ ህዝብ በሰላም ወጥቶ የሚገባበት ፣
- ነጋዴው ከቦታ ወደ ቦታ ተንቀሳቅሶ ሰርቶ እና ነግዶ የሚኖርበት
- ገበሬው ምርጥ ዘር እና ማዳበሪያ አግኝቶ አርሶ የሚበላበት እንዲሁም ከተሜውን የሚቀልብበት ሁኔታ መፍጠር አልቻለም።

የኢትዮጵያ ህዝብ በችጋር እየተጠበሰ፣ በረሃብ እየተሰቃየ ነው።

የኑሮ ውድነቱ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘውን ወገናችንን ከእጅ ወደ አፍ የነበረውን ኑሮ እንኳን መግፋት ወደማይችልበት ደረጃ ደርሷል።

ኢኮኖሚው ታሟል፣ መካከለኛ ነዋሪ የነበረውም ተመቶ ወደ ድህነት ወለል ወርዷል።

ስራ አጥነት ተስፋፍቷል፣ የሀገራችን የነገ ተስፋ የሆኑ ወጣቶችም ሀገራቸው ውስጥ ተስፋ በማጣታቸው ስደትን ብቸኛ ምርጫ አድርገውታል።

ዜጎች በጠራራ ፀሀይ ይታገታሉ በሚሊዮን ብር ይጠየቅቸዋል፣ የመንግስት የፀጥታ መዋቅር በተለይም ፖሊስ ደግሞ አማራዎችንን እና የአማራ ልሂቃንን የአማራ ህዝብ ጥያቄዎችን በማንሳታቸውና መንግሥትን በተለያየ ማንገድ በመተቸታቸው ብቻ የፈጠራ ወንጀል እየተሰጣቸው በማንነታቸው በጅምላ ይታሰራሉ ፣ በጅምላ ይከሰሳሉ ፍርድ ቤት ነፃ ሲላቸው ፖሊስ ግለሰቦችን አስሮ ያቆያል።

የኢትዮጵያ መልካፖለቲካ በሙሉ ያዳረሰ በሚባል ደረጃ ሀገራችን ሁሉም አካባቢዎች የደም ምድር ሆነዋል።

ሙሉ አማራ ክልል አዲስ የጦርነት ቀጠና ተደርጓል፣ ከፊል ኦሮሚያ ክልል የጦርነት ቀጠና ሆኖ ባጅቷል፣ ትግራይ አማራ እና አፋር ፋይዳ ባልነበረው የብልፅግናና የህወሓት የስልጣን ጦርነት ምክንያት ደቋል። ቤኒሻንጉል ፣ጋምቤላ፣ አብዛኛው የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎችም ከሌሎች የተለየ አይደለም።

በማህበራዊ ዘርፍም ወንጀል ተበራክቷል፣ ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች / ዜጎች በመንግስት ቤታቸው ፈርሶ ጎዳና ላይ ወድቀዋል ፤ እንደ ብልፅግና ሹማምንት አባባል ' ህጋዊ ድሃ ተደርገዋል ' ።

በሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች በሰሜኑና በምዕራቡ ሀገራችን ክፍሎች በነበረው ጦርነት እና ማንነት ተኮር ጥቃቶች የውስጥ ተፈናቃይ ሆነው የሰቆቃ ኑሮን ይገፋሉ።

ባለፉት 5 ዓመታት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወታቸውን ተነጥቀዋል። ለዚህ ሁለንተናዊ ሀገራዊ ምስቅልቅል ቀውስ እና ውድመት ወይም ሀገራዊ መክሸፍ ዋነኛው ተጠያቂው የብልፅግና መራሹ መንግስት እና የእርሶ የወደቀ አመራር  / failed leadership ነው።

ገዢው ፓርቲ ብልፅግናን አመጣለሁ እያለ ቢምል ቢገዘትም በተግባር ለኢትዮጵያ ህዝብ ያመጣለት ግን ጉስቅልና ሆኗል።

ብልፅግና ሀገርን ከቀውስ ማውጣት ካልቻለ እና ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም የብልፅግና / የአገዛዙ አገልጋይ በመሆናቸው እና የችግሩም አካል በመሆናቸው ከፓርቲዎቹ የሚጠበው መፍትሄ አይኖርም።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ለወደቀው የእርሶ እና የብልፅግና ፓርቲዎ አመራር መፍትሄው ምንድነው ? የሀገራዊ ቀውስ መፍትሄ አፈላላጊ ጉባኤ እንዲዘጋጅ አድርገው ስይረፍድ ለሀገራዊ ቀውሱ መላ ቢበጅ አይሻልም ወይ ? እንደእኔ እንደ አንድ የህዝብ ተወካይነቴ ብልፅግና ፓርቲ መራሹም ሆነ ፓርላማው ሀገራችን ከገባችበት የፖለቲካ ቅርቃር ማውጣት ስለማይችሉ ስልጣኖን ለጊዜያዊ ሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክቡ ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም በኢፌዴሪ ህገመንግስት አንቀፅ 60 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት በምክር ቤቱ ፍቃድ ምክር ቤቱን እንዲበትኑ እና ለአዲስ ምርጫ መንገዱን እንዲጠርጉ መጠየቅ እፈልጋለሁ።

አመሰግናለሁ ! "

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓርላማ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት 6ኛውን፣ 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 28ኛ ስብሰባውን እያካሄደ ነው፡፡ ምክር ቤቱ በስብሰባው የ27ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ-ጉባዔን መርምሮ አጽድቋል፡፡ የምክር ቤት አባላትም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በ2015 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌደራል መንግስት…
" ዘንድሮ 6 ነጥብ 1 የኢኮኖሚ ዕድገት ተመዝግቧል " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

በዚህ ዓመት የኢትዮጵያ ምጣኔ ኃብት 6 ነጥብ 1 ዕድገት ማስመዝገብ መቻሉን እና በቀጣዩ ዓመት ደግሞ 6 ነጥብ 4 የምጣኔ ኃብት ዕድገት ሊኖር እንደሚችል ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) መተንበይ መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ 2ኛው የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ-ግብር በመተግበር ላይ መሆኑን ጠቁመዋል።

የኢኮኖሚው ማሻሻያ ዋናው ግብ የግሉን ዘርፍ ለማነቃቃትና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን ኑሮ ለማሻሻል ነው ብለዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ በዚህ ዓመት የኑሮ ውድነቱ 37 በመቶ ደርሶ የነበረ ሲሆን፤ በርካታ ስራዎች በመሰራታቸው ምክንያት ቁጥሩን ወደ 30 በመቶ መቀነስ መቻሉን እና እንደ ሀገር ያጋጠመውን የኑሮ ውድነት ለመግታት ወደ ገበያ የተረጨውን ገንዘብ ለመቆጣጠር መንግስት በትኩረት እንደሚሰራ አብራርተዋል፡፡

Via HoPR

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ምን አሉ ? የተ/ም/ቤት አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፦ " ጠ/ሚ ዐቢይ ወደ መንበረ ስልጣን ከወጡበት ከመጋቢት 2010 ዓ/ም ጀምሮ እየተወሳሰቡ የሄዱት የሀገራችን ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች አሁን ላይ ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ መሸጋገራቸውን ማሸፋፈን ወደማይቻልበት ደረጃ ደርሰዋል። ብልፅግና መራሹ መንግስትዎ ፦ - የኢትዮጵያ ህዝብ በሰላም ወጥቶ የሚገባበት ፣ - ነጋዴው…
" አብኖች የት ነበራችሁ ? " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

የህ/ተ/ም/ቤት አባሉ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በሰሜኑ ክፍል ትግራይ ፣ አማራና አፋር ፋይዳ ባልነበረው ጦርነቱ መድቀቃቸውን ተናግረዋል።

ይህ ጦርነትም " #የብልፅግና እና #የህወሓት #የስልጣን ጦርነት " መሆኑን ገልጸው ነበር።

ይህ በተመለከተ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አጭር አስተያየት ሰጥተው አልፈዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " እንደተባለው የTPLF እና የብልፅግና ችግር ከነበረ አብኖች (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ) የት ነበራችሁ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

እዚህ ላይ " ለምን አታስታርቁም ነበር የሚል ጥያቄም ይነሳል። " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " አስታራቂ ሲጠፋ ነው ግጭት የሚበዛው " ብለዋል።

" ድግሱን #ስናፋፋም ቆይተን አሁን ጉዳዩን ለተወሰነ ወገን መስጠት ተገቢ አይደለም " ያሉት ጠቅይላይ ሚኒስትሩ " ግጭቱን ማንም ይጀምረው ማንም ጥሩ አይደለም፤ ጥፋት ነው " ብሎ መቀበል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው ልዩ ስብሰባ በኦሮሚያ እና በደቡብ ክልሎች በተደራቢነት ተይዘው ለቆዩ ክፍት በኾኑና አንገብጋቢ ችግር ባለባቸው ዘጠኝ አህጉረ ስብከት ላይ የሚመደቡ ዘጠኝ ኤጲስ ቆጰሳትን ምርጫ አካሂዷል። ለኦሮሚያ ክልል 7 አህጉረ ስብከት ፦ 1. አባ ሣህለ ማርያም ቶላ - ምዕራብ አርሲ - (ሻሸመኔ) ሀገረ ስብከት 2. አባ ወልደ…
#Update

የተመረጡት ኤጲስ ቆጶሳት የተሾሙ ሲሆን በዓለ ሢመታቸው ሐምሌ 9 ቀን 2015 ዓ.ም. እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አስተላልፏል።

ይህ የተሰማው ዛሬ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የእጩ ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ በተመለከተ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው።

ዝርዝር መግለጫውን ከላይ ያንብቡ።

#ETOTCTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ይጓዛል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራ 13 አባላት ያሉት የልዑካን ቡድን ሐምሌ…
#Update

ቅዱስ ሲኖዶስ የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀ።

በክልል ትግራይ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን ፦

- ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመስጠቷ፣

- በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ክልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንንና መላው #ሕዝበ_ትግራይን በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ፣

- ጦርነቱ ቁሞ በአገር አቀፍ ደረጃ እርቀ ሰላም ከወረደበት ጊዜ ጀምሮ ለደረሰው ጉዳት በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነውን ሰብአዊ ድጋፍ በውሳኔው መሠረት በወቅቱ ማድረስ ባለመቻሏ፣ በዚሁም የተነሣ በቤተ ክርስቲያኗና በመላው ሕዝበ ትግራይ መካከል ለተፈጠረው ቅሬታና አለመግባባት ቅዱስ ሲኖዶስ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።

@tikvahethiopia
#Update

የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግሥት የ2016 ዓ/ም በጀት 801 ቢልዮን ብር ሆኖ ፀደቀ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 28ኛ መደበኛ ስብሰባው የ2016 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀትን 801 ነጥብ 6 ቢልዮን ብር አድርጎ በአንድ ድምፀ-ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል።

Via HoPR

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ምን አሉ ? የተ/ም/ቤት አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፦ " ጠ/ሚ ዐቢይ ወደ መንበረ ስልጣን ከወጡበት ከመጋቢት 2010 ዓ/ም ጀምሮ እየተወሳሰቡ የሄዱት የሀገራችን ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች አሁን ላይ ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ መሸጋገራቸውን ማሸፋፈን ወደማይቻልበት ደረጃ ደርሰዋል። ብልፅግና መራሹ መንግስትዎ ፦ - የኢትዮጵያ ህዝብ በሰላም ወጥቶ የሚገባበት ፣ - ነጋዴው…
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዶ/ር ደሳለኝ ምን ምላሽ ሰጡ ?

ኢትዮጵያ ቀውስ ውስጥ መሆኗና ለዚህም ተጠያቂው ገዢው ብልፅግና ፓርቲና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወደቀ አመራር በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣናቸውን #እንዲለቁና ስልጣናቸውን ለሚቋቋም ጊዜያዊ ሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክቡ ፤ ፓርላማውም ተበትኖ ለምርጫ መንገድ እንዲጠርግ በሚል በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለተጠየቀው ጥያቄ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምላሽ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርቲያቸውና መንግሥታቸው ላይ ከታቃዋሚ ፓርቲ በኩል የቀረበውን ክስ በተመለከተ " እንዲህ ያለው ንግግር ለዛሬ #ፌስቡክ፣ ለዛሬ #ዩትዩብ ጥሩ ነው ፤ አቶ እንትና እንትና እንዲህ አደረጉ ለሚለው ለፌስቡክ ፍጆታ ጥሩ ነው ለትውልድ እና ሀገር ግን አይጠቅምም " ብለዋል።

" ቆም ብለን እኛ ማናየውን በማሳየት ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠቅመውን ሃሳብ ብናቀርብ ጠቃሚ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

" በኢኮኖሚ፣ በሰላም እና በአንዳንድ ጉዳዮች የቀረቡትን የምንወስዳቸውና የምንሰራባቸው እንደሆነ ምንም ጥያቄ የለውም " ያሉት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በጥቅሉ ኢትዮጵያ ጨለማ ውስጥ ናት ከተባለ ግን ከሰሀራ በታች ካሉ ሀገራት በኢኮኖሚ 3ኛ ናት፣ ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ናት ፣ ትላልቅ ተቋማትን እየገነባች ያለች ሀገርናት የሚል መልስ ሆኖ ያልቃል " ሲሉ ተናግረዋል።

ምርጫን በተመለከተ ፤ " ምርጫ ይካሄድ የሚለውን ሃሳብ በጣም አደንቃለሁ ፤ ብዙ ጊዜ የተቃዋሚዎች ችግር ምርጫ አይፈልጉም ዝም ብላችሁ ልቀቁና እኛ እንያዝ ነው የሚሉት ፤ አሁን ምርጫ ይደረግ የሚለው በጣም ጠቃሚ ነው ግን ሶስት ዓመት #መታገስ አለብን " ብለዋል።

" በየሳምንቱ ምርጫ ስለማይደረግ ፤ ሶስት አመት ታግሰን ያለንን ሃሳብ ይዘን ቀርበን እኛም ይዘን ቀርበን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈርደውን ፍርድ በፀጋ መቀበል ነው ፤ የዛሬ ሁለት ዓመት የፈረደውን ፍርድ አልተቀበልኩምና አሁን ፓርላማው ፈርሶ ምርጫ ካልተካሄደ አሁንም ፈርሶ ቢካሄድና ቢመረጥ ካልተመረጥን ይቀጥላል ጉዳዩ በየሁለት አመቱ ምርጫ ለማካሄድ አቅም ስለሚያንሰን በተቀመጠው መንገድ በ5 ዓመት እናደርጋለን " ብለዋል።

" ምርጫ ሲደረግ ያሉ ሀሳቦች ለህዝብ ቀርበው እኛ ህዝቡ በሚፈልገው ልክ ካላገለገልንና ካልጠቀምን ህዝቡ በምርጫው ሲቀጣን እጅ ስመን፣ ባንስምም እጅ ነስተን እናስረክባለን ፤ እስከዛ መታገስ ጥሩ ነው ፤ ፍርዱን ለህዝብ እንተወው " ሲሉ መልሰዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቱ ከገባችበት ቀውስ ጋር በተያያዘ ስልጣናቸውን እንዲለቁ በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ህዝብ በመረጣቸው የምክር ቤት አባላት ሲጠየቁ የዛሬው ሁለተኛ ነው።

የምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ከወራት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን በመልቀቅ " ላለው ችግር የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? " የሚል ጥያቄ አቅርበው የነበረ።

በወቅቱ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ኃላፊነት መውሰድ ካለብን በጋራ ቢሆን መልካም ስለሆነ " ስልጣን ብንለቅ " ነው የሚባለው ምክንያቱም መንግስት ማለት አስፈፃሚ ብቻ አይደለም የሚል ምላሽ ሰጥተዋቸው ነበር።

የዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ንግግር : https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/79527

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያዎን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት እና በሲቢኢ ብር ባሉበት፣ በየትኛውም ሰዓት፣ በማንኛውም የስልክ አይነት መቾትዎ እንደተጠበቀ
በቀላሉ ይክፈሉ!

አሊያም በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የሲቢኢ ብር ወኪል ዘንድ በመሄድ መክፈል ይችላሉ፡፡

******
የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ተጠቃሚ ካልሆኑ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመቅረብ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን የሚችሉ ሲሆን፣ የሲቢኢ ብር አገልግሎት መጠቀም ካልጀመሩ ደግሞ

• ወደ *847# በመደወል፣ ወይም
• የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ተመዝግበው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡

ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ነጻ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ።

የሲቢኢ ብር መተግበሪን ለማውረድ የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr

• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
#PropertyTax

ኢትዮጵያ ውስጥ " ፕሮፐርቲ ታክስ " እስካሁን እንዳልተጀመረ ነገር ግን ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ይፋ አደረጉ።

ዶ/ር ዐቢይ ፤ ፕሮፐርቲ ታክስ መላው ኢትዮጵያ ውስጥ በአዲስ አበባ ጨምሮ እንዳልተጀመረ ገልጸው በአ/አ እየተከናወነ ያለው ከዚህ ቀደም የነበረውን የጣሪያ እና ግርግዳ ግብር ህግ በማሻሻል እየተሰበሰበ ያለ ግብር ነው ሲሉ ጠቁመዋል።

" ይህ የተሻሻለው የጣሪያ እና የግድግዳ ግብር ማለት ፕሮፐርቲ ታክስ ማለት አይደለም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ወደፊት የፕሮፐርቲ ታክስ አዋጅ በዝርዝር የሚታይ ጉዳይ ነው ብለዋል።

" ፕሮፐርቲ ታክስ " ካቢኔው አፅድቆ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ አዋጁ ፀድቆ ተግባራዊ እንደሚደረግም ጠቁመዋል።

ከጣሪያና ግድግዳ ግብር ጋር በተያያዘ ያለው የታክስ ምንጭ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት አምጥቶ ያልተገባ ሀብት ወስዶ ከሆነ ቅሬታ የሚሰማበት ስርአት ስላለ በዚያው ስርአት ቅሬታ ቀርቦ ሊታይ እንደሚችልም አስገንዝበዋል።

በአዲስ አበባ እየተሰበሰበ ያለው የጣራ እና የግድግዳ ግብር መሆኑንና ይህም ከ1937ዓ.ም ጀምሮ የመጣ እና ማሻሻያ የተደረገበት ነው ብለዋል፡፡

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia