TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Telegram

የቴሌግራም ወርሃዊ ተጠቃሚዎች ቁጥር 400,000,000 መድረሱን ድርጅቱ አስታውቋል። በቅርቡ አሁን ባለው አገልግሎት ላይ ተጨማሪ ይዘቶችንም እንደሚያካት ይጠበቃል። ድርጅቱ በ2022 1 ቢሊዮን ተጠቃሚዎች እንዲኖሩት እየሰራ ነው።

በነገራችን ላይ በኢትዮጵያም የቴሌግራም ተጠቃሚ ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ነው። ከፍተኛ ተጠቃሚ ካለባቸው ሀገራትም አንዷ እንደሆነች ይነገርላታል፤ በሀገሪቱ ምን ያህል ተጠቃሚ እንዳለ የሚያሳይ አሁናዊ ማስረጃ ባይኖርም።

ከዚህ ቀደም በቴሌግራም ላይ እንቅስቃሴ የማያደርጉ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ፣ ሚዲያዎች ፣ ታዋቂ ሰዎችም በስፋት እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።

አሁን ደግሞ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ባመጣው ችግር ምክንያት ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸውን በቴሌግራም እያስተማሩ እንደሆነም እየሰማን ነው።

ለመሆኑ ይህን ያህል ለምን ተወደደ ?

- ከምንም በላይ ደህንነቱ የተጠበቀ ነው።

- ብዙ ወጪ አያስወጣም፤ በቀላሉ አገልግሎት ይሰጣል። ኔትዎርክ ደካማ በሆነባቸው ቦታዎች ላይም ለመጠቀም አያስቸግርም።

- ማንም ሰው የፈለገው ብቻ መልዕክት ነው የሚደርሰው ፤ ያለፍላጎቱ ምንም መልዕክት እንዳይደረሰው ማድረግ ይችላል።

- ተጠቃሚዎች እርስ በእርስ የሚሰዳደቡበት ዕድል እጅግ በጣም አነስተኛ ነው ፤ ፈልገው ወደ ግሩፖች እና ቻናሎች ካልገቡ በስተቀር።

- የምልዕክት ልውውጥ ቀልጣፋ ነው። በአነስተኛ ገንዘብ የፈለግነውን ፋይሎችን ለመላላክ አመቺ ነው።

ሌሎችም በተጠቃሚዎች በኩል የሚሰጡ ምክንያቶች ብዙ ናቸው!

ቲክቫህ ኢትዮጵያ (TIKVAH-ETH) ቴሌግራምን ብቸኛው የመልዕክት መለዋወጫ አድርጎ መስራት ከጀመረ ሃምሌ 19/2012 ዓ/ም ሶስተኛ ዓመቱን ይይዛል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Telegram

ከ10:20 ጀምሮ ቴሌግራም ተቋርጦ እንደነበረ ተጠቃሚዎች ገልፀዋል።

ችግሩ ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ አውሮፓ ሀገራት እና የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ውስጥ ነው የተከሰተው።

ድርጅቱ ከተጠቀሰው ሰዓት አንስቶ ተጠቃሚዎች አገልግሎት ማግኘት እንዳልቻሉ #አረጋግጧል ፤ የችግሩን ምክንያት ግን አላሳወቀም።

በአሁን ሰዓት የቴሌግራም አገልግሎት ተቋርጦ በነበረባቸው ሁሉም ቦታዎች ላይ መስራት ጀምሯል ፤ ድርጅቱም ይህንን አሳውቋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የ2ተኛው ቀን የ12ኛ ክፍል ፈተና ዛሬ ተሰጥቷል። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ትላንት የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ/ም መጀመሩ ይታወቃል። በዛሬው ዕለት የ2ኛው ቀን ፈተና በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ ውሏል። ከፈተናው ሂደት ጋር በተያያዘ የተለያዩ አስተያየቶች ከተማሪዎች እና ከተማሪ ወላጆች እያደረሱን ይገኛሉ። አንዳንድ ተማሪዎች ስልክ ይዞ የመገኘትም ነገር እንደነበረ ተፈታኞች ለቲክቫህ እያሳወቁ ነው።…
#Telegram

ቴሌግራም ኢትዮጵያ ውስጥ ለሰዓታት ተቋርጦ ነበር።

ዛሬ ጥዋት #ቴሌግራም ተቋርጦ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። አገልግሎቱ የ12ኛ ክፍል ፈተና ማብቃት ከታወቀ በኃላ ተመልሷል።

ምንም እንኳን ዛሬ ሙሉ በሙሉ ቢቋረጥም ከትላንት ጀምሮ ፍጥነቱ ቀንሶ ፣ ፎቶዎች እና ቪድዮችን ለመለዋወጥ አስቸጋሪ ሆኖ ነበር።

ከ12ኛ ክፍል ፈተና ጋር በተያያዘ ከቀናት በፊት የተማሪ ወላጆች እና ተፈታኝ ተማሪዎች ያነሷቸውን ቅሬታ አጋርተን ነበር።

በአንዳንድ ቦታዎች የሞባይል ስልክ ይዘው ወደ መፈተኛ ክፍሎች የሚገቡ ተማሪዎች ፈተናውን ፎቶ በማንሳት በቴሌግራም የመስራት ሁኔታ እንደነበረ በቂ ማስረጃ እንዳላቸው የቲክቫህ አባላት የሆኑ ተማሪዎች እና ወላጆች መግለፃቸው አይዘነጋም።

ምንም እንኳን ቴሌግራም ከትላንት ጀምሮ ፍጥነቱ ቢቀንስም ፥ ዛሬ ደግሞ ሙሉ በሙሉ ቢዘጋም VPN በመጠቀም የዛሬውን ፈተና ከመፈተኛ ክፍል ውስጥ ፎቶ በማንሳት በሺዎች የሚቆጠሩ አባላት ባላቸው የቴሌግራም ግሩፖች ላይ የማሰራጨት ነገር እንደነበር ተስተውሏል።

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መጠናቀቅን ተከትሎ የትምህርት ሚኒስቴር በሰጠው መግለጫ ዘንድሮ የፈተና ስርቆትን ለማስቀረት 8 ፈተናዎች በ32 ስብጥር በማድረግ ኩረጃ እንዳይኖር ለመከላከል መሰራቱን አሳውቃል።

በተጨማሪ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና በፍፁም እንዳልተሰረቀ አረጋግጣለሁ ብሏል ፤ በአንዳንድ የፈተና ጣቢያዎች ስልክ ይዘው የገቡ በጣም ጥቂት ተማሪዎች መኖራቸውን ግን ገልጿል ፤ ይህ ሁኔታ ከፈተና ኩረጃ ጋር የሚያያዝ እንጂ የፈተና ስርቆት ነው ማለት አያስችልም ብሏል የትህምርት ሚኒስቴር።

@tikvahethiopia
#Telegram

ቴሌግራም በተጠናቀቀው 2021 / እ.አ.አ. / ድንቅ የሚባል አመትን እንዳሳለፈ የድርጅቱ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቬል ዱሮቭ ዛሬ ምሽት አሳውቀዋል።

ጥር ወር ላይ በመላው ዓለም ላይ በብዛት ዳውንሎድ የተደረገ መተግበሪያ ፣ በጥቅምት ወር በአንድ ቀን ብቻ ከ70 ሚሊዮን በላይ አዳዲስ ተጠቃሚዎችን መቀበል የቻለ እንዲሁም በታህሳስ ወር በፍጥነት እያደገ ያለ መተግበሪያ ተብሎ መታወጁ ተገልጿል።

የድርጅቱ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፥ " የእድገቱ ሁሉ ባለቤቶች ተጠቃሚዎቹ እንደሆኑ እናውቃለን " ያሉ ሲሆን በተጠቃሚዎች የሚሰጡትን አስተያየቶች በጥሞና በማድመጥ አመቱን ሙሉ ቴሌግራም ለተጠቃሚዎቹ የተሻለ እንዲሆን አድርገናል ብለዋል።

ቴሌግራም በተጠቃሚዎች ጥያቄ መሰረት በቻናሎች፣ ግሩፖች እንዲሁም የአንድ ለአንድ መልዕክ ልውውጥ ወቅት ሪአክሽን መስጫ (👍👎❤️😢...) እንዲሁም የመልዕክት መተርጎሚያ የተካተተበት በዓመቱ 12ኛ ዋና ማሻሻያ ተደርጎበት ተለቋል።

አዲሱ የሪአክሽን ማሻሻያ የሚሰራው የቻናሉ ወይም የግሩፑ ባለቤቶች ክፍት ሲያደርጉ ነው። እንዴት ? (ወደ ቻናሉ /ግሩፕ በመግባት Edit የሚለውን መጫን ፣ በመቀጠል Enable Reactions የሚለውን ON ማድረግ እና የሚሰጡትን Reaction መምረጥ)

ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ዋናውን የቴሌግራም መተግበሪያችሁን (ባለ ሰማያዊ ምልክቱን) Update በማድረግ ማሻሻያዎቹን እንድትመለከቷቸው መልዕክት እናስተላልፋለን።

የቴሌግራም መተግበሪያችሁን Update ለማድረግ👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=org.telegram.messenger

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሩስያ ኢንስታግራምን ዘጋች። ሜታ ኩባንያ በኢንስታግራም ላይ በሩስያውያን ላይ የጥቃት ፣ የግጭት ቀስቃሽ ፣ እና የጥላቻ ጥሪዎች እንዲተላለፉ መፍቀዱን ተከትሎ ሀገሪቱ ከዛሬ መጋቢት 5 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ አገልግሎት እንዳይሰጥ አድርጋዋለች። ኢስታግራም ከመዘጋቱ 48 ሰዓት በፊት ተጠቃሚዎች የፎቶ እና ቪድዮ ፋይሎቻቸውን ወደሌላ የማህበራዊ ሚዲያ እንዲያዞሩ ጊዜ ተሰጥቷቸው ነበር። 2021 ላይ ኢንስታግራም…
#Telegram

በአሁን ሰዓት ቴሌግራም በሩስያ ቀዳሚው እና ተመራጩ የመልዕክት መለዋወጫ ሆኗል።

በተለይ ሩስያ ኢንስታግራም እና ፌስቡክን ማገዷን ታከትሎ ቴሌግራም በቀዳሚነት ተመራጩ የመልዕክት መለዋወጫ ሊሆን ችሏል።

የዩክሬን ፕሬዜዳንት ዜሌስንኪን ጨምሮ በርካታ የዩክሬን እና የሩስያ ባለስልጣናት ፣ ሚዲያዎች ፣ ፖለቲከኞች ፣ ተቋማት መልዕክት ለመለዋወጥ ቴሌግራምን የሚጠቀሙ ሲሆን በሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት በመረጃ ልውውጥ ትልቁን ስፍራ የያዘ የማህበራዊ ሚዲያ ሆኗል።

ቴሌግራም ከዚህ በፊት ማለትም በ2018 ላይ በሩስያ ባለስልጣናት ለሁለት ዓመታት ታግዶ እንደነበር እና እገዳው 2020 ላይ መነሳቱ ይታወሳል። በወቅቱ እገዳው የተጣለበት የተጠቃሚዎችን መረጃ እንዲሰጥ ተጠይቆ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ነበር።

በአሁን ሰዓት እየተካሄደ ካለው ጦርነት ጋር በተያያዘ ቴሌግራም የዩክሬን ተጠቃሚዎቹን መረጃ ለሩስያ ያቀብላል ተብሎ ስሙ ቢነሳም የኩባንያው መስራች በትውልድ ሩስያዊው እና በኡሁን ሰዓት በዩኤኢ #ዱባይ ነዋሪነቱን ያደረገው ፓቨል ዱሮቭ ኩባንያው የዩክሬን ተጠቃሚዎችን መረጃ አሳልፎ እንዳልሰጠ ፥ ይህንንም እንደማያደርግ በምንም ሁኔታ ለተጠቃሚዎቹ መብት እንደሚቆም ገልጿል።

የቴሌግራም መስራቹ ፤ በእናቱ በኩል ቤተሰቦቹ ከኪየቭ እንደሆኑ ጠቁሞ እስከ አሁን ድረስም በዩክሬን የሚኖሩ ብዙ ዘመዶች እንዳሉት ገልጿል። አሁን ያለው አሳዛኝ ግጭትም " ለእኔም ሆነ ለቴሌግራም ግላዊ ነው " ሲል ነው ሁኔታውን የገለፀው።

የድምፅ እና ቪድዮ ጥሪዎችን፣ የምስጥራዊ የመልዕክት ልውውጦች (ቻት) እንደማያነብ የሚናገርለት ቴሌግራም በምንም ሁኔታ የተጠቃሚዎቹን መረጃ አሳልፎ እንደማይሰጥ የገለፀ ሲሆን ለተጠቃሚዎቹ መብት እንደሚቆም አረጋግጧል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Telegram

ቴሌግራም አጫጭር የድምፅ ፋይሎችን እና የድምፅ መልዕክቶችን ለማንኛውም ቻት/መልዕክት ልውውጥ ወደ ማንቂያ ደውል መቀየር የሚቻልበትን / የራሳችንን የማሳወቂያ ድምፆችን ማዘጋጀት የምንችልበትን ገፅታ እና ሌሎችም አዳዲስ ገፅታዎች የተካከቱበት አዲስ Update ዛሬ ይፋ አድርጓል።

➡️ አዳዲስ ስለተጨመሩ ገፅታዎች ያንብቡ 👇
tx.me/s/forexzig/notifications-bots

➡️ ዋናውን የቴሌግራም መተግበሪያችሁን #Update ለማድረግ ፦

▪️ለአንድሮይድ👉 play.google.com/store/apps/details?id=org.telegram.messenger

▪️ለIOS 👉 https://apps.apple.com/ke/app/telegram-messenger/id686449807

ውድ ቤተሰቦቻችን ፤ ዋናውን የቴሌግራም መተግበሪያ (በነጭ መደብ ላይ ሰማያዊው የቴሌግራም ምልክት ያረፈበትን) እንድትተጠቀሙ እንመክራለን።

#Telegram

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ለመጀመሪያ ጊዜ በፌዴራል ተቋማት / ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እየተሰጠ የሚገኘው የ2014 ዓ/ም 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የመጀመሪያው ዙር / የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ተጠናቋል። ከጥቅምት 5/2015 ዓ/ም ጀምሮ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መግባት ይጀምራሉ። ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ፤ የተማሪዎች ጉዳይ የሀገር ጉዳይ ስለሆነ ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ፈተናዎችን ጉዳይ በንቃት…
#Telegram

በኢትዮጵያ #የቴሌግራም አገልግሎት እንዲገደብ ተደርጓል። አገልግሎቱ ከእኩለ ቀን አንስቶ ነው የተገደበው።

እስካሁን በጉዳዩ ላይ በሚመለከታቸው አካላት ማብራሪያ ባይሰጥም ከዚህ ቀደም እንደታየው የቴሌግራም መገደብ ነገ ከሚጀምረው "የተፈጥሮ ሳይንስ" የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ይታመናል።

ባለፈው ሳምንት የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በሚወስዱበት ቀናት/ወደ ክፍል ገብተው ፈተናቸውን በሚወስዱበት ሰዓት / ፈተናውን ጨርሰው እስኪወጡ ድረስ የቴሌግራም አገልግሎት እንዲገደብ ሲደረግ ነበር።

" በማህበራዊ ሳይንስ " የፈተና ወቅት ተማሪዎች ከፈተና ክፍል ሲወጡ ቴሌግራም ወደ አገልግሎት ሲመለስ የነበረ ሲሆን አሁኑ ላይ ግን ከፈተና አንድ ቀን ቀደም ብሎ አገልግሎቱ ተገድቧል።

የቴሌግራም አገልግሎት በኢትዮጵያ ባሉት ሁለቱም የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢዎች ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እንደማይሰራ ማረጋገጥ ችለናል።

ምንም እንኳን " የቴሌግራም " አገልግሎት ቢገደብም ሌሎች እንደ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም፣ ትዊተር የመሳሰሉ መተግበሪያዎች ያለ ገደብ እየሰሩ ናቸው።

የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ወቅት ወደ መፈተኛ ማዕከላት (ዩኒቨርሲቲ) ተማሪዎች ይዘው እንዳይገቡ በጥብቅ የተከለከለውን ስልክ ይዘው የገቡ ተፈታኞች ፈተናው እየተሰጠ ከመፈተኛ ክፍል እና ፈተና ሲጠናቀቅ ከማደሪያቸው የፈተና ወረቀቶችን በቴሌግራም ግሩፖች እና ቻናሎች ላይ ሲያሰራጩ ነበር።

በዚህም አንዳንድ ሰዎች " የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተሰርቋል " የሚሉ መረጃዎችን ቢያሰራጩም ፈተናው መሰጠት ከጀመረበት ሰዓት በፊት ቀድሞ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ስለመሰራጨቱ የሚያሳይ ማስረጃዎች ማግኘት አልተቻለም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Telegram

ባለፉት ቀናት ከ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ጋር በተያያዘ ሲገደብ የነበረው ቴሌግራም ዛሬ የ12ኛ ክፍል ፈተና መጠናቀቁን ተከትሎ ሙሉ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል።

የ " ቴሌግራም " መገደብ ከፈተናው ጋር በተያያዘ የሀሰተኛ መረጃዎችን ስርጭት በመግታትና ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች #እንዳይረበሹ በማድረግ በኩል ትልቅ የሆነ አስተዋጽኦ እንደነበረው መመልከት ተችሏል።

ባለፉት ዓመታት በነበሩ የብሄራዊ ፈተናዎች ላይ ከየትኛውም የማህበራዊ ሚዲያዎች በበለጠ በ " ቴሌግራም " በኩል ነበር የፈተና ወረቀቶች ከፈተና ቀን ቀደም ብሎ ሲሰራጭ የነበረው።

በአሁኑ የ2014 ዓ/ም ብሄራዊ ፈተና ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርሲቲ አስገብቶ ማስፈተኑ የፈተና ስርቆትን እና ቀድሞ ማሰራጨትን መከላከል ያስቻለ ሲሆን በአንዳንድ ተቋማት ስልክ ይዘው የገቡ ተማሪዎች ከፈተና ክፍል ሆነው የፈተና ወረቀት እያነሱ በቴሌግራም ግሩፖች እና ቻናሎች ላይ ሲያሰራጩ ነበር።

ነገር ግን በአብዛኛው ተማሪ ስልክ ይዞ እንዳይገባ በመደረጉ እና " ቴሌግራም " ም ሲገደብ ስለነበር ተፅእኖውን መቋቋም እንደተቻለ ይታመናል።

በቀጣዩ የ2015 ዓ/ም ብሄራዊ ፈተና ላይ መሰል ክፍተቶች እንዳይኖሩ ለማድረግ ከአሁኑ ፈተና ትምህርት በመውሰድ አስፈላጊ ማስተካከያ ማድረግ ይገባል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

2ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 4 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

ሊንክ፡ https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
3ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 11 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!
https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
4ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 18 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ከ4ኛ ዙር ጀምሮ ባሉት ውድድሮች አስር አስር አሸናፊዎች በየሳምንቱ ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

የገና ስጦታ!
ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
5ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 25 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ከ4ኛ ዙር ጀምሮ ባሉት ውድድሮች አስር አስር አሸናፊዎች በየሳምንቱ ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
7ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ጥር 9 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
7ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ጥር 9 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#Telegram

ቴሌግራም በሰዓታት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዳዲስ ተጠቃሚዎች አገኘ።

ዓለም ላይ ለሰዓታት ፌስቡክ እና ኢንስታግራም መቋረጣቸውን ተከትሎ " ቴሌግራም "ን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች መቀላቀላቸውን የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስፈፃሚ ፓቨል ዱሮቭ ገለጹ።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ፤ " ኢንስታግራም እና ፌስቡክ በተቋረጡበት ባለፉት ሰአታት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ቴሌግራም ላይ ሲመዘገቡ እና ይዘቶችን ሲያጋሩ ቆይተዋል " ብለዋል።

" ቴሌግራም " ከእነዚህ አገልግሎቶች የበለጠ አስተማማኝ ነው ሲሉም አክለዋል።

" ምንም እንኳን ከሜታ አንድ ሺህ ጊዜ ያነሱ ቋሚ የሆኑ ሰራተኞች ቢኖሩንም በመተግበሪያው ላይ አዳዲስ ይዘቶችን ለማሻሻል እና አዳዲስ ፈጠራዎችን ለማከል ፈጣኖች ነን " ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ፤ " በ2023 ሙሉ ከዓመቱ 525,600 ደቂቃዎች ውስጥ የቴሌግራምን አገልግሎት ማግኘት ያልተቻለው በአጠቃላይ ለ9 ደቂቃ ብቻ ነው " ያሉ ሲሆን " ይህም 99.999983% ቴሌግራም ስራ ላይ እንደነበር አመላካች ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

በቅርቡ በቴሌግራም ቻናላችን በየሳምንቱ የአንድ አመት የቴሌግራም ፕሪምየም የሚያስገኝ ውድድር የምንጀምር ሲሆን የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል እና የምንጠይቃቸውን ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ!
ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 15 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ቴሌግራም ፕሪምየምን ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#አቢሲንያ_ባንክ

የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሰኔ 22 ከረፋዱ 4:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ በየሳምንቱ አስር አስር አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ቴሌግራም ፕሪምየምን ይሸለሙ!

የቴሌግራም ሊንክ፡ https://publielectoral.lat/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ