TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሩዋንዳና የፈረንሳይኛ ቋንቋ ተለያዩ‼️

የሩዋንዳ ፓርላማ በፈረንሳይኛ ቋንቋ ምትክ ስዋሂሊ የሃገሪቱ ኦፊሴላዊ ቋንቋ እንዲሆን በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።

እኤአ እስከ 1962 ድረስ በቤልጂግ ቅኝ ግዛት ስር የነበረችው ሩዋንዳ ቀደም ብሎም የፈረንሳይኛ ቋንቋ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መሰጠት እንዲያቆምና በምትኩ የእንግሊዝኛ ቋንቋ እንዲሰጥ ወስና የነበረ ቢሆንም፤ የአሁኑ የፓርላማው ውሳኔ ሁለቱንም ቋንቋዎች የገፋ ነው።

በሩዋንዳ ፓርላማ ውሳኔ ያልተደሰቱት የቀድሞዋ ገዢ ቤልጅዬምና ፈረንሳይ የካጋሜ መንግሥት ላይ የተለያዩ ማዕቀቦችን ሊጥሉና በተለይም ፈረንሳይ የካጋሜን ተቃዋሚ ኃይሎች ልትደግፍ እንደምትችል ፍንጭ እየሰጠች ነው።

በርካታ ጥቁር ፓን አፍሪካኒስቶች የሩዋንዳን ውሳኔ እያደነቁና እያወደሱ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የሩዋንዳን ፈለግ በመከተል የቀኝ ገዢዎች ቋንቋን በመተው በሀገር በቀል ቋንቋዎች ይተኩ ዘንድ በተለይ የአፍሪካ ኅብረት ትኩረት ሊሰጠው ይገባል እያሉ ነው።

Via #PetrosAshenafi
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ጀማል ....

አንጋፋው ጋዜጠኛ በኢትዮጰያ በድሮው ETV የቴሌቪዥን የመዝናኛ ክፍል 120 ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ በጀይሉ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ተዘጋጅቶ በኢቢ ኤስ ቴሌቪዘዥን ይቀርብ የነበረው ቢላል ሾው የተሰኘ ፕሮግራም አዘጋጅ እንዲሁም በአሁኑ ሰአት በአፍሪካ ቲቪ የሚቀርቡ የተለያዩ ኢስላማዊ ኘሮግራም የሚያዘጋጀው የጀይሉ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ባለቤት እና ማናጀር ጋዜጠኛ ጀማል አህመድ ባጋጠመው የልብ ህመም ምክንያት በሆስፒታል ህክምና እየተደረለት ይገኛል። ጀማል አህመድ አመለ ሸጋ፣ ትሁት ፣አይናፋር ፣እዩኝ እዩኝ የማይወድ ስትር ያለ ስብእና ያለው ድምፁ የማይሰማ የልዩ ባህሪ ባለቤት ነው።

በዚህ የሮመዳን ወር በያላችሁበት በዱአችሁ አትርሱት!

Via #PetrosAshenafi
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ግንቦት 20, 1983 ዓ/ም👆

ከላይ ባለው ፎቶ የሕወሓት ሊቀመንበር #መለስ_ዜናዊ እና የደኅንነቱ ሹም #ክንፈ_ገብረ_መድኅን ወደ ግዮን ሆቴል ሲገቡ ይታያሉ።

የሚሊተሪ ለብሶ የሚታየው የቀድሞው ጦር (ደርግ) መኮንን የነበረው ኮሎኔል አስራት ነው። ኮሎኔል አስራት በሕወሓት ከተማረከ በኋላ ከኢህአዴግ ጋር ተሰልፎ በብሔራዊ መረጃና ደህንነት መምሪያ ሀላፊነት ደረጃ ድረስ ሲሰራ የነበረ፤ በኋላም የግርማዊ ዐፄ ኃይለሥላሴ አስከሬን ከኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ጽ/ቤት ለማውጣት የተዋቀረውን ግብረ ኃይል ያስተባበረ ነው።

አብዮት ልጇን ትበላለችና ኮሎኔል አስራት የቀይ ሽብር ተዋናይ ነበር ተብሎ ወደ ወህኒ ቤት የወረደ ሲሆን፤ በወህኒ ቤትም እያለ "በህመም" ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት የተለየ መሆኑ ታውቋል።

ግንቦት 20 ዛሬ 28ኛ አመቱ ሲታሰብ በፎቶው ላይ የምናያቸው ሶስቱም አመራሮች በሕይወት የሉም።

Via #PetrosAshenafi
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የሊቨርፑል እና የቶተናም ደጋፊዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ...

በነገው ዕለት በእንግሊዞቹ ሊቨርፑልና ቶተንሃም ክለቦች መካከል በስፔኗ መዲና ማድሪድ ለሚካሄደው የአውሮፓ ቻምፒዬንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ ለመታደም የሁለቱ ክለቦች ደጋፊዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ሲጓዙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ

UEFA Champions League
Liverpool FC Totenham #UCLfinal #Madrid #UCL #ChampionsLeague #LIVTOT

Via #PetrosAshenafi
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የ2019 የዩኔስኮ ፌሊክስ ሁፉዌ ብዋኚ (Félix Houphouët-Boigny) የሰላም ሽልማት አሸናፊ መሆናቸው ይታወቃል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በተለይ በኢትዮ ኤርትራ የሰላም ስምምነት ላይ በነበራቸው ከፍተኛ ሚና ለሽልማቱ የታጩ መሆናቸውንም ዩኔስኮ አሳውቋል።

መቀመጫውን ፈረንሳይ ፓሪ ያደረገው የመንግስታቱ ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ተቋም ዩኔስኮ አስቀድሞ ሽልማቱን ለመስጠት የፊታችን ጁላይ 9 ቀን መርሐ ግብር ተይዞለት የነበረ ቢሆንም ተቋሙ የሽልማቱን መስጫ ቀን ላልተወሰነ ቀን ማራዘሙን አሳውቋል። https://en.unesco.org/news/ceremony-award-felix-houphouet-boigny-unesco-peace-prize-ethiopian-pm-abiy-ahmed-ali

Via #PetrosAshenafi
🗞ቀን ሰኔ 24/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር አርከበ ሆስፒታል ናቸው...

"በሚንስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚንስትሩ ልዩ አማካሪ የሆኑት ዶ/ር #አርከበ_እቁባይ ታመው ቤልጅዬም በሚገኝ ሆስፒታል ህክምና በመከታተል ላይ ይገኛሉ።" ይህ መረጃ #PetrosAshenafi እና ethiopiaobserver.com ናቸው ያወጡት።

🗞ቀን ሰኔ 26/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጋዜጦች በዚህ ሳምንት፦

የኬንያው ዘ ኢስት አፍሪካን ጋዜጣ በፊት ገፁ "የዐቢይ አህመድ የጫጉላ ሽርሽር አበቃ" በሚል ሰፊ ዘገባ ይዞ ወጥቷል። ኢስት አፍሪካን በኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያና ሩዋንዳ የሚሰራጭ በምስራቅ አፍሪካ ብዙ አንባብያን ያለው ጋዜጣ ነው። ቢሆንም አንዳንድ ጊዜ የዞኑን መንግሥታት ጠንከር ባለ ሁኔታም ስለሚተች በቅርቡ ታንዛኒያ ወደ ሃገሬ አይግባብኝ እያለች ነው። #PetrosAshenafi

🗞ቀን ሰኔ 29/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ...

በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ የሹመት ደብዳቤያቸው ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ም/ፕሬዝዳንት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የዱባይ ገዥ ለሆኑት ልዑል ሼህ መሀመድ ቢን ራሺድ አል መክቱም በአዲሱ ቤተመንግስት አቅርበዋል፡፡

Via #PetrosAshenafi
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-SPORT
ሞሮኳዊው የዳኛ ባምላክ ደብዳቢ ተቀጡ!

ኢትዮጵያዊውን ኢንተርናሽናል አርቢትር ባምላክ ተሰማን የደበደቡት የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት፣ የካፍ ምክትል ፕሬዚዳንትና የሞሮኮው ቤርካን ክለብ የክብር ፕሬዚዳንት ፉዚ ሌክጃ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን የዲስፕሊን ኮሚቴ ለአንድ አመት ከማንኛውም ስፖርታዊ አመራር ታግደዋል።

Via #PetrosAshenafi
@tikvahethsport
#ባምላክ_ተሰማ

ማራቶን በአንድ ርምጃ ይጀመራል እንዲሉ የዛሬው የአፍሪካ ቁንጮ ኢንተርናሽናል አርቢትር የቀድሞዎቹን የኢትዮጵያ ምርጥ ተጫዋቾች የሆኑትን እነ ሙሉጌታ ከበደን (ወለዬው) ለመዳኘት ወደ ሜዳ ሲያመራ ልዩ ስሜት ተሰምቶት ነበር። እነሆ ዛሬ ከአመታት በኋላ የአህጉራችን አፍሪካ ኮኮቦችን እየመራ የአህጉሪቱን ታላቅ ውድድር ፍፃሜ ለመዳኘት ፊት አውራሪ ዳኛ ሆኖ ተመርጧል።

ባምላክ የፊታችን አርብ በካይሮ ስታዲዬም ታላቁ ሊቨርፑልን ለአውሮፓ ሻምፒዮንነት ያበቃውን ሳዲዮ ማኔን እና የፔፕ ጋርዲዮላን ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም የክላውዲዮ ራኒዬሪን ሌስተር ሲቲን ለእንግሊዝ ሻምፒዮንነት ያበቃው ሪያድ ማህሬዝን እየመራ ወደ ሜዳ ይገባል።

በአላማና መንፈሰ ጠንካራነት የተገነባው የባምላክ ጉዞ በአለም ዋንጫ ትውልድ አህጉሩን አፍሪካን ወክሎ የወርቅ ኳስ አሸናፊዎቹን ከመዳኘት የሚያግደው እንደማይኖር መናገር ይቻላል። በአለም አቀፍ የእግር ኳስ መድረክ ጥሩ ተጫዋች አይውጣብሽ የተባለች የሚመስለው ሃገራችን አሁን ስሟን የሚያስጠራ ጥሩ አጫዋች አግኝታለች።

Via #PetrosAshenafi

@tsegabwolde @tikvahethiopia