TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ግንቦት

ታሪክን መለስ ብለን ስናይ፦

√የውጫሌ ውል የተፈረመው በግንቦት ወር ነው።

√ለንግስና ያልበቁት ልጅ እያሱ በሚኒሊክ የተሾሙት በግንቦት ወር ነው።

√በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ከዚህ አለም በሞት የተለዩት ልዑል መኮንን ኃይለስላሴ በግንቦት 1949 ነው።

√ኮ/ሌ #መንግስቱ_ኃይለማርያም የተወለዱት ግንቦት 19 ነው፤ መፈንቅለ መንግስት የተሞከረባቸው ግንቦት 8 ሆኖ ግንቦት 13/1983 ደግሞ ሀገራቸውን ጥለው የተሰደዱበት ቀን ነው።

√ግንቦት 11/1982 ዓ.ም 12 ከፍተኛ ጀኔራሎች #የተገደሉበት ቀን ነው።

√ግንቦት 20 ኢህአዴግ አዲስ አበባን የተቆጣጠረበት ቀን ነው።

√የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ #መለስ_ዜናዊ የተወለዱት ግንቦት 1 ነበር።

√ግንቦት 7/1997 በኢትዮጵያ የብዙሃን ፓርቲ ምርጫ የተካሄደበት ነበር።

√ግንቦት 18/1999 በደርግ ከፍተኛ አመራሮች ላይ ሞት የተፈረደበት ቀን ነው፤ ግንቦት 24/2003 የሞት ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ የተለወጠበት ቀን ነው።

ግንቦት ታሪካዊ ናት!

Via ሌ/ኮሎኔል ፍስሃ ደስታ/አብዮቱና ትዝታዬ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ግንቦት 20, 1983 ዓ/ም👆

ከላይ ባለው ፎቶ የሕወሓት ሊቀመንበር #መለስ_ዜናዊ እና የደኅንነቱ ሹም #ክንፈ_ገብረ_መድኅን ወደ ግዮን ሆቴል ሲገቡ ይታያሉ።

የሚሊተሪ ለብሶ የሚታየው የቀድሞው ጦር (ደርግ) መኮንን የነበረው ኮሎኔል አስራት ነው። ኮሎኔል አስራት በሕወሓት ከተማረከ በኋላ ከኢህአዴግ ጋር ተሰልፎ በብሔራዊ መረጃና ደህንነት መምሪያ ሀላፊነት ደረጃ ድረስ ሲሰራ የነበረ፤ በኋላም የግርማዊ ዐፄ ኃይለሥላሴ አስከሬን ከኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ጽ/ቤት ለማውጣት የተዋቀረውን ግብረ ኃይል ያስተባበረ ነው።

አብዮት ልጇን ትበላለችና ኮሎኔል አስራት የቀይ ሽብር ተዋናይ ነበር ተብሎ ወደ ወህኒ ቤት የወረደ ሲሆን፤ በወህኒ ቤትም እያለ "በህመም" ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት የተለየ መሆኑ ታውቋል።

ግንቦት 20 ዛሬ 28ኛ አመቱ ሲታሰብ በፎቶው ላይ የምናያቸው ሶስቱም አመራሮች በሕይወት የሉም።

Via #PetrosAshenafi
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ማስታወሻ

"... የዚህ ታላቅ ፕሮጀክት ጥቅም በኢትዮጵያ ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ሁሉንም ጎረቤቶቻችን በተለይም የታችኛው ተፋሰስ ሀገሮች የሆኑትን ሱዳን እና ግብፅን በእጅጉ የሚጠቅም ነው።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ወንዙ ተሸክሞት ይሄድ የነበረው ደለል ስለሚቀር በግብፅ እና በሱዳን ያሉ ግድቦች በተለይም በደለል እየተሞላ የሚሰጠው ጥቅም በከፍተኛ መጠን የቀነሰው የሱዳን የሮሰሪስ ግድብ ከዚህ አደጋ ነፃ ይሆናል።
.
.
ጥቅሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገሮች በተለይ ለሱዳን እና ግብፅ ጭምር በመሆኑ ፍትህ የሰፈነበት ሁኔታ ቢኖር የግድቡን ወጪ 3ቱም ሀገራት ሊሸፍኑት በተገባ ነበር።

እያንዳንዱ ሀገር ከግድቡ በሚያገኘው ጥቅም ልክ ወጪውን ይሸፍን ቢባል ሱዳን የወጪውን 30%፣ግብፅ የወጪውን 20% መሸፈን በተገባቸው ነበር።

ይሁንና በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ እንዲህ አይነቱ ገንቢና ፍትሃዊ አሰራር ሊሰፍን አልቻለም፤በመሆኑም ወጪው በሙሉ ኢትዮጵያ ለመሸፈን ተገዳለች።

ይባስ ብሎ ግድቡን ለመስራት ብድር እና እርዳታ እንዳናገኝ የተለያዩ ኃይሎች ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ምክንያት የፕሮጀክቱን ወጪ ለመሸፈን የሚተባበረን ሀገር ወይም ተቋም ማግኘት አልቻልንም።

ስለሆነም ወጪውን ብቻችንን ከመሸፈን አልፈን ከራሳችን ቁጠባ ለመሸፈን የምንገደድበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
.
.
ያለን አማራጭ አንድም ግድቡን አለመስራት ፥ አለበለዚያ እንደምንም ወጪውን በራሳችን መሸፈን ነው።

ከነዚህ ሁለት ከባድ አማራጮች መካከል የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫ የቱ እንደሚሆን ግልፅ ነው።

በተለመደው ወኔው ምንም ያህል ድሃ ብንሆንም ድህነታችንን ለማስወገድ ማንኛውም መስዋዕነት ለመክፈል ዝግጁ ነን፤ ስለዚህ ፕሮጀክቱ መሰራት አለበት እንደሚል ለአፍታም ያህል አልጠራጠርም። "

የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር አቶ #መለስ_ዜናዊ - መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ከተናገሩት የተወሰደ።

@tikvahethiopia