TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ማስታወሻ

የ2014 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ ዛሬ አርብ ጥር 26/2015 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ያበቃል።

@tikvahethiopia
#ሃይላንድ

በኢትዮጵያ  የታሽገ ውሃ  ፈርቀዳጅ እና ታዋቂ የሆነው  ሃይላንድ በአውሮፓ ስታንዳርድ ማሽኖች ታግዞ ሲጠጡት ቀለል ብሎ አንጀት እንዲያርስ ተደርጎ  ለየት ባለ አስተሻሽግ እና በነጭ ክዳን በ0.3ሊ፣ በ0.6ሊ፣ በ 1ሊ እና በ2ሊ ለገበያ ቀርቧል።

ለማከፋፈል ወይም ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን 0911233552 ይደውሉ  " ሃይላንድ የህይወት ስንቅ "

የሃይላንድ ውሃ ትክክለኛ ማህበራዊ ትስስር ገጾችን ይከተሉ፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100087976315526

https://www.tiktok.com/@highlandwaterethiopia?_t=8ZVmAJPFkfd&_r=1

https://instagram.com/highlandwater_?igshid=OGQ2MjdiOTE=

https://www.linkedin.com/company/highland-%E1%8B%89%E1%88%83/

#ማስታወሻ፡ አስኩ ኃ/የተ/የግ/ማ ሃይላንድ የታሸገ ውኃን ከተረከበ በኋላ የንግድ ምልክቱን በ2013 በባለቤትነት አስመዝግቧል።
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስዳችሁ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያመጣችሁ እና በመንግስት ተቋማት ገብታችሁ መማር የምትፈልጉ ተማሪዎች የተቋም ምርጫችሁን  በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ የካቲት 02/2015 ዓ.ም ድረስ እንድታስተካክሉ የትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። በልዩ ሁኔታ በአዳማ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርሲቲዎች መማር የምትፈልጉ…
#ማስታወሻ

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ያመጡ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን የማስተካከያ ጊዜ ዛሬ የካቲት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ያበቃል።                        

በ2014 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያመጡና በመንግስት ተቋማት ገብተው መማር የሚፈልጉ ተማሪዎች የተቋም ምርጫቸውን በየት/ ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እንዲያስተካክሉ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተቀመጠው የጊዜ ገደብ ዛሬ ያበቃል።

በምደባ ወቅት አዎንታዊ ድጋፍ የሚሹ ተማሪዎች ማመልከቻቸውና እና ደጋፊ ሰነዶቻቸውን በቀጣዩ ሊንክ ብቻ መላክ ይችላሉ 👇

https://student.ethernet.edu.et

More : @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#አዲስ_አበባ #የሚዘጉ_መንገዶች የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ/ም የሚከበረው 127ኛው የአድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓሉ ስነ ስርዓት በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ በዕለቱ በ #ምኒሊክ_አደባባይ በመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ለበዓሉ መታሰቢያ ጉንጉን አበባ በማስቀመጥ የአከባበር…
#ማስታወሻ

ነገ የካቲት 23/2015 ዓ/ም የሚከበረው 127ኛው የአድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓሉ ስነ ስርዓት በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

👉 በምኒሊክ አደባባይ በሚከናወነን የአከባበር ስነ ስርዓት ምክንያት  ፦

• ከሰሜን ሆቴል ትራፊክ መብራት ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከዮሀንስ መብራት ወደ አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ
• ከአፍንጮ በር ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከጊዮርጊስ ቴሌ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ደጎል አደባባይ
• ከሀገር ፍቅር መታጠፊያ ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከብሪቲሽ ካውንስል ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከሲኒማ አምፒር ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከእሪ በከንቱ ( እሪ በስራ) ወደ ጊዮርጊስ አደባባይ
• ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከአራዳ ህንፃ ወደ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከአቡነ ጴጥሮስ አደባባይ ወደ ወደ ምኒሊክ አደባባይ
• ከሰባራ ባቡር ቶታል ወደ ጊዮርጊስ ቴሌ መስቀለኛ
• ከዳትሰን ሰፈር መገንጠያ ወደ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ስነ ስርዓቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚደረጉ ይሆናል ፡፡

👉 ከምኒሊክ አደባባይ ወደ አደዋ ድልድይ የእግር ጉዞ በማድረግ በአድዋ ድልድይ የሚከናወነውን ስነ ስርኣት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ  ፦

• ከእንግሊዝ ኤምባሲ ትራፊክ መብራት ወደ አድዋ ድልድይ
• ከፈረስ ቤት ኮንደሚኒየም መታጠፊያ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከምስራቅ መገንጠያ ወደ ምስራቅ አጠቃላይ
• ከሴፍቲ መብራት ወደ ምስራቅ አጠቃላይ
• ከ22 አደባባይ ወደ ዘሪሁን ህንፃ
• ከዘሪሁን ህንፃ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከቺቺኒያ ወደ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከካዛንቺስ ቶታል ወደ አቧሬ
• ከድሮው ሰንደይ ማርኬት ወደ ሴቶች አደባባይ
• ከሴቶች አደባባይ ወደ አድዋ ድልድይ
• ከአቧሬ ጀርመን አደባባይ ወደ ሴቶች አደባባይ ያሉት መንገዶችን ከንጋቱ 11 ጀምሮ ለተሽከርካሪ #ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

👉 በመስቀል አደባባይ የሚከናወነው የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ፦

• ከመገናኛ  ወደ መስቀል አደባባይ
• ከዘሪሁን ህንፃ ወደ መስቀል አደባባይ
• ከአትላስ መብራት ወደ ኡራኤል
• ከፒኮክ ትራፊክ መብራት ወደ ኡራኤል
• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ ኡራኤል
• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ ባምቢስ
• ከጥላሁን አደባባይ( መሿለኪያ) ወደ ሴንጆሴፍ ት/ቤት
• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ 
• በቂርቆስ አዲሱ መንገድ  ወደ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መስቀለኛ
• ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ለገሀር
• አልሳምጨለለቅ ህንፃ ወደ ለገሀር
• ከገነት መብራት ወደ ለገሀር
• ከጠማማ ፎቅ (ገነት ሆቴል) ወደ ሜክሲኮ
• ከሱዳን ኤምባሲ (ጠማማ ፎቅ) ወደ ሜክሲኮ
• ከአፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት ወደ ሜክሲኮ
• ከዲአፍሪክ ሆቴል ወደ ሜክሲኮ
• ከሰንጋ ተራ 40/60 ኮንዶሚኒየም ወደ ለገሐር
• ከጎማ ቁጠባ ወደ ብሔራዊ ቲያትር
• ከሜትሮሎጂ ወደ ፖስታ ቤት መብራት
• ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ኢምግሬሽን መብራት
•  ከጎላ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢምግሬሽን
• ከቴዎድሮስ አደባባይ ወደ ኢምግሬሽን መብራት(ፖስታ ቤት)
• ከንግድ ማተሚያ ወደ ኦርማ ጋራዥ
• ከሚያዚያ 27 አደባባይ (4 ኪሎ) ወደ ፓርላማ መብራት
• ከጥይት ቤት ወደ ግቢ ገብርኤል
• ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ ቶታል  የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11 ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ ፖሊስ ገልጿል።

ፖሊስ አሽከርካሪዎች #ሌሎች_አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተላልፏል።

ከዛሬ ረቡዕ የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት ጀምሮ በተገለጹት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓታት ተሸከርካሪን #አቁሞ_መሄድ የተከለከለ ነው ተብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
በኢትዮጵያ ምን ያህል መስማት የተሳናቸው ዜጎች ይኖራሉ?

በወቅታዊ ጥናት ላይ ተሞርክዞ የቀረበ መረጃ ባይኖርም እንደማሳያ የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ፣ የዓለም የጤና ድርጅትና የዩኒሴፍ ጥናቶችን መመልከት ይቻላል፡፡

የማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ በ2005 ዓ.ም በሰራው ዳሰሳ ኢትዮጲያ ከህዝብ ቁጥሯ 3 በመቶ የሚሆነው አካል ጉዳተኛ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ከዚህ ውስጥም 20 በመቶ ሚሆኑት (720 ሺ) መስማት የተሳናቸው መሆናቸውን ይጠቅሳል፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት ከዓለም ባንክ ጋር በጋራ በ2003 ዓ.ም ባወጡት ሪፖርት ከኢትዮጲያ ከህዝብ ቁጥሯ 15 ሚሊዮን ዜጎቿ (17.6 በመቶ) አካል ጉዳተኛ መሆናቸውን ገልጾ፤ ከዚህ ውስጥም 20 በመቶ ሚሆኑት (3.5 ሚሊዮን በላይ) መስማት የተሳናቸው ይላል፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት በ2013 ዓ.ም ባወጣው ቁጥራዊ ማስረጃ (Fact Sheet on Deafness and Hearing loss) ላይ ደግሞ በኢትዮጵያ ከ5 ሚሊዮን በላይ መስማት የመስማት ችግር ያለባቸው ዜጎች መኖራቸውን ይጠቅሳል።

ዩኒሴፍ ከሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር በ2008 ዓ.ም በሰራው ዳሰሳ የአካል ጉዳተኛ ዜጎች ከአጠቃላይ የህዝብ ቁጥሩ 9.3 በመቶ (7.8 ሚሊዮን) መሆኑን ያስቀምጣል፡፡ ከላይ በሁለቱም ጥናቶች የተወሰደውን ስሌት ተጠቅመን 20 በመቶዎቹ መስማት የተሳናቸው ናቸው ብንል ከ1.5 ሚሊዮን በላይ መስማት የተሳናቸው ዜጎች ይኖራሉ።

#ማስታወሻ፡ በተለያየ ጊዜያት የተሰሩትና ማግኘት የቻልናቸው የጥናት ውጤቶች ግኝት በጣም የተራራቁ ቢሆንም ለማሳያ ያክል የቀረቡ ናቸው። ቁጥራዊ መረጃዎቹ ወቅታዊ መረጃን ገላጭ አይደሉም፡፡ ተጨማሪ መረጃዎች ካሎት @RWethiopia ላይ ያካፍሉን

#HandsSpeakEyesListen
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ማስታወሻ

"... የዚህ ታላቅ ፕሮጀክት ጥቅም በኢትዮጵያ ብቻ የተወሰነ አይደለም፤ሁሉንም ጎረቤቶቻችን በተለይም የታችኛው ተፋሰስ ሀገሮች የሆኑትን ሱዳን እና ግብፅን በእጅጉ የሚጠቅም ነው።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ወንዙ ተሸክሞት ይሄድ የነበረው ደለል ስለሚቀር በግብፅ እና በሱዳን ያሉ ግድቦች በተለይም በደለል እየተሞላ የሚሰጠው ጥቅም በከፍተኛ መጠን የቀነሰው የሱዳን የሮሰሪስ ግድብ ከዚህ አደጋ ነፃ ይሆናል።
.
.
ጥቅሙ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገሮች በተለይ ለሱዳን እና ግብፅ ጭምር በመሆኑ ፍትህ የሰፈነበት ሁኔታ ቢኖር የግድቡን ወጪ 3ቱም ሀገራት ሊሸፍኑት በተገባ ነበር።

እያንዳንዱ ሀገር ከግድቡ በሚያገኘው ጥቅም ልክ ወጪውን ይሸፍን ቢባል ሱዳን የወጪውን 30%፣ግብፅ የወጪውን 20% መሸፈን በተገባቸው ነበር።

ይሁንና በአባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ እንዲህ አይነቱ ገንቢና ፍትሃዊ አሰራር ሊሰፍን አልቻለም፤በመሆኑም ወጪው በሙሉ ኢትዮጵያ ለመሸፈን ተገዳለች።

ይባስ ብሎ ግድቡን ለመስራት ብድር እና እርዳታ እንዳናገኝ የተለያዩ ኃይሎች ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ምክንያት የፕሮጀክቱን ወጪ ለመሸፈን የሚተባበረን ሀገር ወይም ተቋም ማግኘት አልቻልንም።

ስለሆነም ወጪውን ብቻችንን ከመሸፈን አልፈን ከራሳችን ቁጠባ ለመሸፈን የምንገደድበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
.
.
ያለን አማራጭ አንድም ግድቡን አለመስራት ፥ አለበለዚያ እንደምንም ወጪውን በራሳችን መሸፈን ነው።

ከነዚህ ሁለት ከባድ አማራጮች መካከል የኢትዮጵያ ህዝብ ምርጫ የቱ እንደሚሆን ግልፅ ነው።

በተለመደው ወኔው ምንም ያህል ድሃ ብንሆንም ድህነታችንን ለማስወገድ ማንኛውም መስዋዕነት ለመክፈል ዝግጁ ነን፤ ስለዚህ ፕሮጀክቱ መሰራት አለበት እንደሚል ለአፍታም ያህል አልጠራጠርም። "

የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር አቶ #መለስ_ዜናዊ - መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ከተናገሩት የተወሰደ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ማስታወሻ

ዛሬ በአዲስ አበባ " ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በኢትዮጵያ-3 ' ይካሄዳል።

ምዕመናን ስትመጡ የሚከተሉትን እንዳትዘነጉ ፦

- ለጸጥታ አካላት እና ለበጎ ፍቃድ አስተባባሪዎች #ፍተሻ ትብብር ማድረግ።

- የሰላት መስገጃ ይዞ መምጣት።

- ለማፍጠሪያ የሚሆንና ከሙስሊም እህትና ወንድሞች በማካፈል ኢፍጣርን ለሌሎች በማጋርት የሚገኘውን አጅር ተቋዳሽ እንዲሆኑ ጥሪ ተደርጓል። ምግቦቹ እንደ ቴምር፣ ውሃ እና የታሸጉ ምግቦች መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

- የዝግጅቱ ዋና ዓላማ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከሌሎች ጋር ኢፍጣርን በማጋራት የሚገኘውን አጅር እና ደስታ እንዲያጣጥም ከማስቻል ባሻገር ሙስሊሙ ህብረተሰብ ምንም ዓይንት ልዩነት ሳይገድበው ህብር ብሄራዊ አንድነነቱን በማሳየት ለሃገር #ሰላም እና #ዕድገት በጋራ አላህን የሚማፀንበት ዝግጅት ስለሆነ ከዝግጅቱ ዓላማ ውጪ ከሆኑ ድርጊቶች በመቆጠብ ኢስላማዊ ስነምግባርን ለሌሎች ዓርኣያ በመሆን ማሳየት ይገባል።

- ማንኛውም ለደህንንት አጠራጣሪ ሁኔታዎች ከተመለከቱ ለበጎ ፍቃደኛ አስተባባሪዎች እና ለጸጥታ አካላት በአፋጣኝ አሳውቁ።

- በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በመጠለያ ካምፕ ውስጥ ለሚገኙ ገንዘብ ስለሚሰበሰብ ከወዲሁ በረመዳን ለተቸገሩ ድጋፍ በማድረግ የሚገኘውን ታላቅ አጅር እንዲሸመቱ የአቅሞን ገንዘብ ይዘው ወደ ዝግጅቱ እንዲመጡ።

(ከአዘጋጆቹ)

@tikvahethiopia
Threads_an_Instagram_app_289.0.0.68.109_.apk
74.1 MB
#Threads_an_Instagram_App

#ማስታወሻ ፦ ከፕሌይ ስቶር / አፕ ስቶር ላይ ለማውረድ VPN አማራጮቻችሁን USA ወደሚል ወይም አፕሊኬሽኑ ወደ ተለቀቀባቸው አከባቢዎች ቀይረው ማውረድ ይችላሉ።

#META

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የመውጫ ፈተና ውጤት እየታየ ይገኛል።

በ2015 ዓ/ም የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተመራቂ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከእሁድ ረፋድ ጀምሮ እየተመለከቱ ይገኛሉ።

ውጤቱ መታየት ከጀመረበት ሰዓት አንስቶ ለረጅም ሰዓታት በመንግስት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎች ብቻ ውጤታቸውን ማየት የቻሉ ሲሆን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ደግሞ #ከምሽት አንስቶ ውጤታቸውን ማየት ጀምረዋል።

ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች መካከል አንዳንዶቹ " ውጤት መመልከቻው ድረገፅ ላይ ገብተው username ሲያስገቡ የሚያገኙት ምላሽ የተቋማቸው " የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ አልተደረገም " የሚል እንዲሁም የአንዳንዶቹ " ያስገቡት ስም የማይሰራ " መሆኑን የሚገልፅ ነው።

ውጤታቸውን የተመለከቱ በርካታ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ደግሞ 50 እና ከዚያ በላይ የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ቢሆንም " fail / ወድቀዋል " የሚል ምላሽ እያገኙ መሆኑን በመግላፅ ትምህርት ሚኒስቴር በሲስተሙ ላይ ያለውን ችግር #እንዲያስተካክል ጠይቀዋል።

ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ፤ የመውጫ ፈተና የተቀመጡት 72,203 ተማሪዎች ሲሆኑ 50 እና ከዚያ በላይ ውጤት አምጥተው ያለፉት 12,422 ተማሪዎች ወይም 17.2 በመቶ መሆናቸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

በሌላ በኩል ፤ በመውጫ ፈተና አመርቂ ውጤት ካልተመዘገበባቸው / እጅግ በርካታ ተማሪዎች ከወደቁባቸው የትምህርት ክፍሎች አንዱ የ " Accounting and Finance " ሲሆን በፈተናው ላይ  ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች የፈተናው ምዘና ድጋሚ እንዲፈተሽ ጠይቀዋል።

በተመሳሳይ የ " Information Technology " ተማሪዎችም መሰል አቤቱታ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ተማሪዎቹ የተሰጠው ፈተናው ከነበረው ዝግጅት ጋር የሚራራቅ እንዲሁም ደግሞ ከ ተሰጣቸው ' ብሉለሪንት ' ጋር የማይቀራረብ በመሆኑ ሚኒስቴሩ እንዲያይላቸው አቤቱታ አቅርበዋል።

ከዚህ ቀደም የ ' መካኒካል ምህንድስና ' ተመራቂ ተማሪዎች ከፈተናው ጋር በተያያዘ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው የሚዘነጋ አይደለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የትምህርት ሚኒስቴር ፤ ወይም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ተማሪዎችን #ቅሬታ የሚያስተናግዱበት መንገድ ካለ ጠይቆ የሚያሳውቅ ይሆናል።

#ማስታወሻ ፦ የመውጫ ፈተና ውጤት የሚታየው በ result.ethernet.edu.et ላይ Username በማስገባት ነው።

More : @tikvahuniversity

@tikvahethiopia
" ችግር አላየሁበትም " - ትምህርት ሚኒስቴር

የትምህርት ሚኒስቴር ከአካውንቲንግ እና ፋይናንስ የመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ ሲነሳ ለነበረው ቅሬታ " ገምግሜዋለሁ ምንም ችግር አላገኘሁበትም " ሲል ምላሽ ሰጠ።

የአካውንቲንግ እና የፋይናንስ የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ተፈታኞች እንዲሁም የትምህርት ክፍላቸው እንዲሁም ኮሌጆች ፈተናው ዳግም እንዲገመገም ጥያቄ ሲያቀርቡ እንደነበር አይዘነጋም።

የቀረበው ቅሬታ ፈተናው ከተዘጋጀው ብሉፕሪንት ጋር ተያያዥነት እንደሌለው፣ ይሸፍናል ከተባለው 15 ኮርስ የሸፈነው ከ4 የሚበልጥ እንዳልሆነ ፣ የመጡት ጥያቄዎችም በዲግሪ ደረጀ ለመረዳት የማይቻሉ ፣ ለፈተናው የተሰጠው ሰዓትም ከጥያቄው ጋር የማይገናኛ መሆኑ ይጠቀሳሉ።

ለዚህም ትምህርት ሚኒስቴር አስፈላጊውን ማስተካከያ እንዲያደርግ እና ፈተናውን እንዲገመግመው ተማሪውን የሚመጥን ፈተና ድጋሚ አዘጋጅቶ በፍጥነት እንዲፈትን ተደጋጋሚ ጥያቄ ቀርቧል።

የትምህርት ሚኒስቴር ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ በሰጠው ቃል ፤ ስለተነሳው ቅሬታ እንደሚያውቅ ገልጾ ፈተናውን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን መገምገሙን ነገር ግን በፈተናው ይዘት ላይም ሆነ አቀራረብ ላይ ችግር እንዳላየበት አሳውቋል።

#ማስታወሻ፦ ከፈተናው ጋር በተያያዘ በተማሪዎች እንዲሁም በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ ትምህርት ክፍሎች / ኮሌጆች የቀረቡ ቅሬታዎች ፦
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/79870?single
https://publielectoral.lat/TikvahUniversity/7740?single
https://publielectoral.lat/TikvahUniversity/7739?single

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ የሥራ መደቦች ሰልጣኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ✓ ሰልጣኝ አብራሪ/ፓይለት (Trainee Pilot) ✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ቴክኒሽያን (Trainee Aircraft Maintenance Technician) ✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ሜካኒክ (Trainee Aircraft Mechanic) ✓ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጅ (Trainee Cabin Cors) …
#ማስታወሻ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተለያዩ የሥራ መደቦች ሰልጣኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ምዝገባው ዛሬ ይጀምራል።

የስልጠና መጠሪያዎች ፦
✓ ሰልጣኝ አብራሪ/ፓይለት (Trainee Pilot)
✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ቴክኒሽያን
(Trainee Aircraft Maintenance Technician)
✓ ሰልጣኝ የአውሮፕላን ሜካኒክ (Trainee Aircraft Mechanic)
✓ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጅ (Trainee Cabin Cors)
✓ ሰልጣኝ የመንገደኛ አገልግሎት ኢጀንት (Trainee Customer Service Agent) ናቸው።

አመልካቾች ለምዝገባ ፤ የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውንና ኮፒው፣ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ካርድ፣ የልደት ካርድ፣ የታደሰ የቀበሌ የነዋሪነት ማረጋገጫ ካርድ እና አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ ማሟላት አለባቸው።

አመልካቾች ከተዘረዘሩት የሥራ መደቦች ውስጥ ማመልከት የሚችሉት በአንዱ ብቻ ነው።

ምዝገባእ ከነሐሴ 15 ጀምሮ እስከ 19/2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ ነው የሚቆየው።

የምዝገባ ቦታ፡-
- አዲስ አበባ በኦንላይን (አዲስ አበባ)
- አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ (አምቦ)
- አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ (አርባምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ (አሶሳ)
- ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ (ባህርዳር)
- ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ (ደ/ብርሃን)
- ደብረ ማርቆስኦኒቨርሲቲ፣ (ደ/ማርቆስ)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ (ድሬዳዋ)
- ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ፣ (ፍቼ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ (ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ (ጎንደር)
- ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ (ሀረር ካምፓስ ሀረር)
- ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ (ነቀምቴ)
- ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ፣ (ሚዛን ቴፒ)
- ሮቤ ቲቺንግ ኮሌጅ፣ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ)

ዕድሜ ፣ ቁመት ፣ ክብደትና ሌሎች መረጀዎችን ከላይ በተያያዘው የተቋሙ ይፋዊ ማስታወቂያ ይመልከቱ።

More ፦ https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies?fbclid=IwAR1ZLHg_fw9VhghmXo-oOL9ykrsCmq3vcUISCzYl8QtRPPg5fnW4VW_Yfig

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ የኣሸንዳ በዓል መቼ ይከበራል ? የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፤ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2015 ዓ.ም የአሸንዳ በአል አከባበር መርሃ ግብር ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሰረት፤ በዓሉን #ነሃሴ_28 ቀን 2015 ዓ/ም በአዲስ አበባ ለማክበር እቅድ መያዙ ገልጿል። የሚደረግ የጊዜ ለውጥ ካለ አስቀድሞ የሚገለፅ መሆኑንም አስተዳደሩ አሳውቋል። የበዓሉ መርሀግብር ምን ይመስላል ? - ነሃሴ 13…
ፎቶ ፦ ዛሬ ነሃሴ 15 ቀን 2015 ዓ/ም የ #ኣሸንዳ በዓልን ምክንያት በማድረግ በመቐለ ከተማ የጎደና የካርኒቫል ትርኢትና ሰማእታት የሚያስታውስ የሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት ተከናውኗል።

#ማስታወሻ ፦ ከ " ኣሸንዳ " አከባበር ጋር በተያያዘ በክልሉ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ የወጣው መርሀ ግብር ከላይ ተያይዟል። በቢሮው ከተገለፀው ውጭ የሚካሄደ የአሸንዳ በዓል ዝግጅት እውቅና እንደሌለው ተነግሯል።

Photo Credit : Demtsi Weyane

@tikvahethiopia
#ማስታወሻ

ዛሬ በቡዳፔስት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ ልጆች የሚካፈሉባቸው የፍፃሜ ውድድሮች ይደረጋሉ።

ዛሬ የሚደረጉት ውድድሮች የ1500ሜ ሴቶች ፍፃሜ እና የ3000ሜ መሰናክል ወንዶች ፍፃሜ ናቸው።

ውድድሮቹ ምሽት 4:30 እና ምሽት 4:42 ላይ ነው የሚደረጉት።

ሀገራችን የሚወክሉ አትሌቶች እነማን ናቸው ?

- በ1500ሜ ሴቶች ፍፃሜ (አትሌት ድርቤ ወልተጂ እና ብርቄ ሀየሎም)

- የ3000ሜ መሰናክል ወንዶች ፍፃሜ (አትሌት ጌትነት ዋለ እና ለሜቻ ግርማ)

በ1500ሜ ሴቶች ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ለኔዘርላንድ ከምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፋን ሀሰን ጋር ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethsport 
TIKVAH-ETHIOPIA
ኢትዮጵያ በልዑል ገብረስላሴ የነሃስ ሜዳሊያ አገኘች❤️ 🥇የኡጋንዳው አትሌት ኪፕላንጋት በአንደኛ ደረጃ አጠናቋል። 🇺🇬 🥈አትሌት ማሩ ተፈሪ ከእስራኤል ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ጨርሷል። 🇮🇱 🥉የሀገራችን ልጅ ልዑል ገብረ ስላሴ ሶስተኛ ደረጃ ይዞ አጠናቋል። 🇪🇹 @tikvahethiopia
ፎቶ፦ በወንዶች ማራቶን ውድድር አትሌት ልዑል ገብረ ስላሴ 3ኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ ለሀገሩ የነሃስ ሜዳሊያ አስገኝቷል።

ሌሎች ኢትዮጵያውያን ፤ አትሌት ሚልኬሳ መንገሻ 6ኛ ፣ አትሌት ፀጋዬ ጌታቸው 17ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።

የባለፈው አመት የዓለም ሻምፒዮን ኢትዮጵያዊው አትሌት ታምራት ቶላ ውድድሩን አቋርጧል።

አትሌት ታምራት ውድድሩን ለማቋረጥ የተገደደው ባጋጠመው ከባድ የጨጓራ ህመም ምክንያት እንደሆነ ለ " ልዩ ስፖርት " ተናግሯል።

በስፍራው የሚገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ስፖርት ባልደረባ አትሌቶች በቡዳፔስት ያለውን ከፍተኛ ሙቀት መቋቋም አቅቷቸው ሲወድቁ እንደነበር ገልጿል።

ከውድድሩ ፍፃሜ በኃላ የተነሱ ፎቶዎችን ከላይ ይመልከቱ።

#ማስታወሻ ፦ ዛሬ ምሽት 3000ሜ መሰናክል ሴቶች ፍፃሜ እና 5000 ወንዶች ፍፃሜ ይካሄዳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
መንግሥት የከለከለው ሰልፍ ... በሳምንቱ መጀመሪያ ሰኞ በአደባባይ ሊከበር የነበረው የሰራተኞች በዓል (ሜይዴይ) በመንግስት መከልከሉ ይታወሳል። በዚህ ዙርያ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌደሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ምን አሉ ? አቶ ካሳሁን ፎሎ ፦ " የእኛ አላማ የነበረው የሰራተኛውን ጥያቄ ይዘን በመላው ከተማ ሳይሆን በመስቀል አደባባይ ብቻ ማክበር እና ጥያቄዎቻችንን በሰላም ማቅረብ…
#Update

ዛሬ ከሰዓት የኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚዎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጋር ተገናኝተው ተነጋገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያ የሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር " መልካም የሥራ ግንኙነት ስለመፍጠር " መወያየታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ውይይቱን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ይፋ አልተደረገም።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) አንገብጋቢ ባላቸው የሠራተኞች ጥያቄዎች ላይ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድን አግኝቶ ማነጋገር #ግድ እና #ብቸኛ አማራጭ መሆኑን ገልጾ ነበር።

ኮንፌዴሬሽኑ ዘንድሮ የሜይ ዴይ በዓል ላይ በአዲስ አበባ ከተማ በአደባባይ ሊያነሳቸው የነበሩ ጥቄያዎች ሰልፍ እንዳያደርግ በመከልከሉ ጥያቄዎቹን ሳያቀርብ እንደቀረ ይታወሳል።

በኃላ ሊያነሳቸው የነበረውን ጥያቄዎችን በማካተት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በጻፈው ደብዳቤ፣ እሳቸውን ማነጋገር ለሠራተኞች ጥያቄዎች ምላሽ ለማግኘት እንደሚረዳ ገልጾ ነበር።

በወቅቱ በፃፈው ደብዳቤ በየጊዜው እያሻቀበ በመጣው የኑሮ ውድነት፣ የኢትዮጵያ ሠራተኞችና ቤተሰቦቻቸው መኖር የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን ገልጾ ለዚህ ብቸኛው መፍትሄው ጠቅላይ ሚኒስትሩን  አግኝቶ ማነጋገር እንደሆነ ገልጿል።

ኢሠማኮ የሠራተኞች አንገብጋቢ የሚባሉ ጥያቄዎችን አስመልክቶ በተለያዩ መንገዶች ለሚመለከታቸው መንግሥታዊ አካላት ጥያቄ ቢያቀርብም፣ ምላሽ ሊያገኝ እንዳልቻለ በዛው ደብዳቤ ተመላክቷል።

ከዚህ ቀደም የሠራተኞች ጥያቄ የቀረበላቸው መንግሥታዊ አካላት ጥያቄውን ወደ ጎን የመግፋት አዝማሚያ እያሳዩ በመምጣታቸው፣ የኢሠማኮ አመራር " ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአነጋግሩን " ጥያቄ ለማቅረብ መገደዱን በወቅቱ በፃፈላቸው ደብዳቤው አስረድቶ ነበር።

#ማስታወሻ

ከዚህ ቀደም ኢሠማኮ ከሰራተኛው ጥያቄ ጋር በተያያዘ እንዳያደርግ በተከለከለው ሰልፍ ሊጠይቃቸው የነበሩ ጥያቄዎች ምን ነበሩ ?

1. በከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሰራተኛው እየተቸገረ ነው፣ በተለይ ደግሞ ደሞዝ ተከፋዩ። መንግስት መፍትሄ ይስጠን። አብዛኛው ሰራተኛ በቀን አንዴም ለመብላት እየተቸገረ ነዉ።

2. የስራ ግብር ይቀነስልን።

3. የዛሬ አራት አመት ወጥቶ የነበረው የዝቅተኛ ደሞዝ ማስተካከያ አዋጅ እስካሁን ደንብ ሳይወጣለት ቆይቷል። ይህም ትኩረት ይሰጠው፣ በ600 ብር እየኖረ ያለ ሰው አለ፣ ኢንደስትሪ ፓርኮች ውስጥ ደሞዝ በአማካኝ ከ800 - 1,200 ብር ነው።

4. የአሰሪና ሰራተኛ ኤጀንሲዎች ከደምበኛቸው ከሚቀበሉት ክፍያ ለሰራተኛው 80 ፐርሰንት ከፍለዉ ቀሪውን 20 ፐርሰንት እንዲወስዱ በሚል የወጣዉ መመሪያ አለመከበር በኤጀንሲ በተቀጠሩ  ሰራተኞች ላይ ተመልካች ያጣ የጉልበት ብዝበዛ እየተካሄደ ነው፣ መንግስት ትኩረት ያርግበት የሚል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ማስታወሻ

ብሔራዊ የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና / Graduate Admission Test ከመስከረም 28 እስከ 30/2016 ዓ.ም በበይነ-መረብ ይሰጣል።

ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምርምር ኢንስቲትዩት- የፈተና ማዕከል ጋር በመተባበር የሚሰጠው ፈተና በተጠቀሱት ቀናት በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ይከናወናል።

ለፈተናው የተመረጡ ተፈታኞች ከመስከረም 21 እስከ 25/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው የGAT መመዝገቢያ ፖርታል https://portal.aau.edu.et ላይ ምዝገባ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

ከመስከረም 23 እስከ 25/2016 ዓ.ም ባሉት ቀናት የሙከራ ፈተና ይሰጣል።

(ለመመዝገብ እና ፈተናውን ለመውሰድ የይለፍ ቲኬት ለማግኘት ሊከተሏቸው የሚገቡ ቅደም-ተከተሎች ከላይ ተያይዟል።)

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የሬሜዲያል ተማሪዎች ምደባ በቀጣይ ይካሄዳል " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትላንት ይፋ በተደረገው የማካካሻ ትምህርት / ሬሜዲያል መቁረጫ ነጥብ መሰረት ወደ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ገብተው ለሚማሩ ተማሪዎች በቀጣይ የዩኒቨርሲቲ ምደባ እንደሚካሄድ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

የመቁረጫ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ ከተደረገላቸው በኃላ ለ4 ወራት የማካካሻ ትምህርት የሚወስዱ ሲሆን ይህንን ተከታትለው በተቋማቸው እና በማዕከል የሚሰጣቸውን ፈተና ማለፍ ሲችሉ በቀጣይ መደበኛ ተማሪ ሆነው ወደ ፌሽማን ይቀላቀላሉ።

ትምህርት ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው የመቁረጫ ነጥብ በሁሉም አማራጮች ማለትም #በግል እና #በመንግስት ተቋማት የሬሜዲያል ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል፤ ይህም ማለት 210 ከ700፣ 180 ከ600 እና 150 ከ500 ማስመዝገብ አለባቸው።

በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) በዩኒቨርሲቲ ተመድበው የሬሜዲያል ፕሮግራም የሚከታተሉ በ #ተፈጥሮ_ሳይንስ የመደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች መቁረጫው 255 ከ700 ነው። የሴት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች መቁረጫው ደግሞ 234 ከ700 ነው።

በዩኒቨርሲቲ ተመድበው ለሚማሩ የማህበራዊ ሳይንስ መደበኛና የማታ ወንድ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡ 218 ከ600 ሲሆን ፤ የሴት ተማሪዎች መቁረጫው 200 ከ600 ነው።

እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ከሆነ ዘንድሮ 164,242 የሬሜዲያል ተማሪዎች በግል እና በመንግሥት ተቋማት ገብተው ይማራሉ።

#ማስታወሻ ፦ የሬሜዲያል መቁረጫ ነጥብ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

በሌላ በኩል ፤ በ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈትነው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ምደባ ከትላንት ጀምሮ ይፋ የተደረገ ሲሆን የምደባ መመልከቻው ፦በድረገፅ https://result.ethernet.edu.et/
የቴሌግራም ቦት @moestudentbot መሆኑን ለማስታወስ እንወዳለን።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia