#ባምላክ_ተሰማ

ማራቶን በአንድ ርምጃ ይጀመራል እንዲሉ የዛሬው የአፍሪካ ቁንጮ ኢንተርናሽናል አርቢትር የቀድሞዎቹን የኢትዮጵያ ምርጥ ተጫዋቾች የሆኑትን እነ ሙሉጌታ ከበደን (ወለዬው) ለመዳኘት ወደ ሜዳ ሲያመራ ልዩ ስሜት ተሰምቶት ነበር። እነሆ ዛሬ ከአመታት በኋላ የአህጉራችን አፍሪካ ኮኮቦችን እየመራ የአህጉሪቱን ታላቅ ውድድር ፍፃሜ ለመዳኘት ፊት አውራሪ ዳኛ ሆኖ ተመርጧል።

ባምላክ የፊታችን አርብ በካይሮ ስታዲዬም ታላቁ ሊቨርፑልን ለአውሮፓ ሻምፒዮንነት ያበቃውን ሳዲዮ ማኔን እና የፔፕ ጋርዲዮላን ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም የክላውዲዮ ራኒዬሪን ሌስተር ሲቲን ለእንግሊዝ ሻምፒዮንነት ያበቃው ሪያድ ማህሬዝን እየመራ ወደ ሜዳ ይገባል።

በአላማና መንፈሰ ጠንካራነት የተገነባው የባምላክ ጉዞ በአለም ዋንጫ ትውልድ አህጉሩን አፍሪካን ወክሎ የወርቅ ኳስ አሸናፊዎቹን ከመዳኘት የሚያግደው እንደማይኖር መናገር ይቻላል። በአለም አቀፍ የእግር ኳስ መድረክ ጥሩ ተጫዋች አይውጣብሽ የተባለች የሚመስለው ሃገራችን አሁን ስሟን የሚያስጠራ ጥሩ አጫዋች አግኝታለች።

Via #PetrosAshenafi

@tsegabwolde @tikvahethiopia