TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የፌደራል እና የአማራ ክልል የጸጥታ አስከባሪ ተቋማት #እርምጃ እንዲወስዱ ታዘዙ‼️

በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር እና በሰሜን ሸዋ ዞን አዋሳኝ አካባቢዎች ያለውን የጸጥታ መደፍረስ ለማረጋጋት የፌደራል እና የክልል የጸጥታ አስከባሪ ተቋማት እርምጃ እንዲወስዱ ታዘዙ። የጸጥታ ኃይሎቹ “አስፈላጊውን ህጋዊ እና #ተመጣጣኝ እርምጃ እንዲወስዱ” ትዕዛዝ መተላለፉን ያስታወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ የጸጥታ ምክር ቤት ነው።

ምክር ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ በአማራ ክልል “ከሚሴ እና በአጎራባች አካባቢዎች የተከሰተው የሰው ሕይወት መጥፋት እና የንብረት ውድመት በምንም አግባብ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው” ብሏል። የምክር ቤቱ መግለጫ በአካባቢዎቹ በተፈጸመው ጥቃት ስለሞቱ ሰዎች ብዛት ከመጥቀስ ተቆጥቧል።

በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን እና የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አጣዬ፣ ማጀቴ እና ካራቆሬ በተባሉ ከተሞች በተፈጸመ ጥቃት የሰው ሕይወት መጥፋቱን የአካባቢው ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። በሰሜን ሸዋ ዞን የኤፍራታና ግድም ወረዳ መንግስት ኮሚዩንኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት “የኦነግ ታጣቂዎች” ሲል የጠራቸው ጥቃት ፈጻሚዎች በከፈቱት ተኩስ አራት ሰዎች መሞታቸውን በትላትናው ዕለት አስታውቆ ነበር። ህይወታቸው ካለፈው መካከል ሶስቱ “የከተማይቱን ሰላም ለማስጠበቅ የተሰማሩ የፀጥታ አባላት” መሆናቸውን የገለጸው የወረዳው የመንግስት ኮሚዩንኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አንደኛው በተባራሪ ጥይት ተመትቶ መሞቱን ገልጿል።

በአካባቢዎቹ የተከሰተውን ጥቃት “ብጥብጥ” ሲል የጠራው የብሔራዊ ጸጥታ ምክር ቤት “ችግሮች የሚከሰቱት የራሳቸው አጀንዳ ባላቸው ውስን የጥፋት ሃይሎች ነው” ብሏል። ምክር ቤቱ “በአካባቢዎቹ በተከሰተው ብጥብጥ ላይ “እጁ ያለበት ማንኛውም አካል በህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑ” ገልጿል። ብጥብጡን ያቀናበሩት፣ ያነሳሱትና የፈጸሙ አካላትን ለህግ ለማቅረብ እንዲቻል ጥናት የሚያደርግ፣ ከአማራ ክልል እና ከፌደራል ተቋማት የተውጣጣ ቡድን ወደ አካባቢዎቹ መሰማራቱንም አስታውቋል።

መንግስት ህግን ለማስከበርና የዜጎችን ሰላም ለማስጠበቅ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ እንደሆነ የገለጸው የብሔራዊ ጸጥታ ምክር ቤት “በሕገወጥ ተግባራት ላይ የሚሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው የማይቆጠቡ ከሆነ መንግስት ሕግን ከማስከበር ወደ ኋላ እንደማይል በድጋሚ ያረጋግጣል” ሲል አስጠንቅቋል።

ምንጭ-የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እርምጃ ተወሰደባቸው...🔝

የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት አጀንሲ የትምህርት ጥራት ችግር ያለባቸውን ከፍተኛ የግል የትምህርት ተቋማት ላይ #እርምጃ ወሰደ፡፡

አጄንሲው በአዲስ አበባና በዙሪያዋ በሚገኙ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ድንገተኛ ጉብኝት በማድረግ የህግ ጥሰት ፈፅመዋል ባላቸው ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሱዱን አስታውቋል፡፡

አጄንሲው የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት አጀንሲ በአዋጅ ቁጥር 650/2011 እና በሚኒስትሮች ም/ቤት ደንብ ቁጥር 261/2004 ያለዉን ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት በማድረግ ከላይ በተገለፁት የግል ከፍተኛ ተቋማማት ላይ ከእገዳ እስከ ፅሁፍ ቅጣት ማስተላለፉን ከኤጀንሲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

Via #EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሰበር_ዜና #ባህር_ዳር

በአማራ ክልል የተሞከረው መፈንቅለ መንግስት #መክሸፉን አቶ ንጉሱ ጥላሁን ተናግረዋል። ይህንን ድርጊት በፈፀሙት ላይ #እርምጃ እንዲወሰድ ትእዛዝ ተሰጥቷል፤ እንቅስቃሴም ተጀምሯል ሲሉ ገልፀዋል።

Via #etv/#Elias_Meseret/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባህር_ዳር

ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን በአማራ ክልል መንግስት ላይ ተሰነዘረ ያሉትን "መፈንቅለ መንግስት" አወገዙ። አሜሪካን ሀገር የሚገኙት የአዴፓ ሊቀመንበር "የፌደራል መንግስት ጉዳዩን በመከታተል አስፈላጊው #እርምጃ ይወስዳል" ብለዋል። #elu

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቁልፍ ቦታዎች በኦሮሞ ተይዟል

ቁልፍ የሚባሉ የመንግሥት የሥልጣን ቦታዎች በኦሮሞ ነው የተያዙት የሚለው አስተያየት ''ውሸት'' ነው ሲሉ አጣጥለውታል ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ በዛሬው የፓርላማ ውሏቸው። ''የተከበረው ምክር ቤት፤ በእያንዳንዱ ተቋም ኦሮሞ ያልተገባ ሥልጣን ይዞ ከሆነ አጣርቶ ከእኔ ጀምሮ #እርምጃ መውሰድ ይችላል" ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ "ኦሮሞ በአንድም ቦታ ያልተገባ ሥልጣን አልያዘም" ብለዋል።

Via #BBC
🗞ቀን ሰኔ 24/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የስዋዚላንድ መንግስት የድግምትና ጥንቆላ ውድድር በሃገሪቱ ማገዱን ኤ ኤፍ ፒን ዋቢ በማድረግ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ከጥንቆላና ጥንታዊ ከሆኑ ልማዶች ጋር የተያያዘ ድርጊት የሚከውኑ ግለሰቦች ከተገኙ በህግ ተጠያቂ እንደሚሆኑ የሃገሪቱ የመንግሰት ቃል-አቀባይ ፐርሲ ሲመላኔ መናገራቸውን በዘገባው ተመልክቷል፡፡

በሳምንቱ መጨረሻም በሃገሪቱ የሚገኙ የድግምት ፈዋሾች የእርስ በርስ የጥንቆላና ድግምት ፉክክር ለማድረግ ቀጠሮ ይዘው እንደነበር አጃንስ ፋራንስ ፕሬስ በዘገባው ጠቅሷል።

የአፍሪካ ጋማ የተሰኘው የጥንት አባቶች ባህላዊ የፈውስ ፉክክር በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሊዘጋጅ እንደነበርም ታይምስ ኦፍ ስዋዚላንድን በዋቢነት በመጥቀስ ዘገባው አመልክቷል።

ባህላዊ ፈዋሽ የነበረው ሚስተር ጋማ እኤአ በ1982 ህልፈተ ህይወታቸው በተሰማው በዳግማዊ ሶቡዛ የንግስና ዘመን ተመሳሳይ በሆነ ውድድር ላይ ተሳትፎ ያደርጉ እንደነበርም ታይምስ ኦፍ ስዋዚላንድ አክሏል።

ንጉሱ ይህን #እርምጃ ለመውሰድ የወሰኑት አንዳንድ ሃሰተኛ ፈዋሾችን ለማጥፍት ፈልገው ይሆናል፤ ነገር ግን ይህን ትክክለኛ ውድድር ባልተደራጀ ሁኔታ መከልከል ተገቢ አይደለም ሲሉሚስተር ጋማ መናገራቸውን ዘገባው አስፍሯል፡፡

Via #BBC/#ENA
🗞ቀን ሃምሌ 4/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#GRAPHIC_CONTENT ከላይ በፎቶው የምትመለከቱት ኢትዮጵያዊ ዜጋ በፖሊሶች የተያዘበት መንገድ በርካቶችን አስቆጥቷል፤ በርካቶች በማህበራዊ ሚዲያ እየተቀባበሉት ነው፤ በርካቶችም ድርጊቱን አውግዘዋል።

በዛሬው ዕለት የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ስለጉዳዩ ተጠይቆ ይህን ምላሽ ሰጥቷል፦

የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ፅህፈት ቤት ሃላፊ ኮማንደር #ታዬ_ግርማ  ባለፉት ሁለት ቀናት ውስጥ በኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ችግር እንደተፈጠረ ተደርጎ በማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተሰራጨ ስላለው ምስል በኮሚሽኑ በኩል በትክክል አለመረጋገጡን ተናግረዋል። ከዚህ ባለፈ ግን ችግሩ በማን እና እንዴት እንደተፈጠረ #እያጣራ እንደሚገኝም ነው የገለጹት። የክልሉ ፖሊስ ለኦሮሞ ህዝብ አለኝታውና መከታው ሆኖ በርካታ ችግሮችን እየተጋፈጠ ሲታገል የቆየና አሁንም በዚያው ቁርጠኝነት እያገለገለ እንዳለም አስረድተዋል፡፡ ድርጊቱ የክልሉን ፖሊስ ስም ለማጥፋት የተፈጸመ በመሆኑ የፖሊስ ኮሚሽንም ይሁን ሌላ አካል ጉዳዩን በፈጸሙ አካላት ላይ #እርምጃ እንደሚወስድ ገልጸዋል። በምስሉ ላይ የሚታዩ ግለሰቦችንም የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንን የደንብ ልብስ ከመልበሳቸው ውጭ ማንነታቸውን ማረጋገጥ እንዳልተቻለም ተናግረዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Qatar

- የኳታር አሚር በትላንትናው እለት ለበርካታ የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አድርገዋል።

- በረመዳን የፆም ወቅት የመንግስት ሰራተኞች በቀን አራት ሰዓታት ብቻ (ከ 9:00 AM - 1:00 PM) እንዲሰሩ፤ በግል ተቋማት የሚሰሩ ሰራተኞች ደግሞ በቀን ለስድስት ሰዓታት (ከ 9:00 AM - 3:00 PM) እንዲሰሩ ተወስኗል። ሆኖም ውሳኔው ምግብ ነክ ምርቶችን የሚያቀርቡ ሱቆችን፣ ፋርማሲዎችን እና በትዕዛዝ የሚሰሩ ምግብ ቤቶችን አይመለከትም።

- ማንኛውም ነዋሪ ወደ ሱቆች፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ እንዲሁም የህዝብ እና የግል ቢሮዎች ሲሄዱ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ማስክ የማድረግ ግዴታ አለባቸው። ይህን ውሳኔ ተላልፎ የሚገኝ ግለሰብ ህጋዊ #እርምጃ ይወሰድበታል።

- ከImam Muhammad ibn Abd al-Wahhab መስጅድ በስተቀር ሁሉም መስጅዶች ዝግ ሆነው ይቆያሉ።

(የኢትዮጵያ ኤምባሲ-ዶሃ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#FDREDefenseForce

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሐመድ በሕዝቦች መካከል ቁርሾ እና ግጭት በመፍጠር ፣ በሃይማኖትና በተለያዩ ምክንያቶች ሰዎችን እየፈረጁ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ አይኖራቸውም ሲሉ አስታውቀዋል።

ሕዝብን ከሕዝብ ጋር የሚያጋጩ ፤ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ ፤ ጎሳን ከጎሳ የሚያጋጩ ስራዎች ሆነ ተብለው የሚሰሩ ከሆነ ፤ አድገው ወደ ዘር ማጥፋት ፣ ወደ እልቂት የሚያመሩ በመሆኑ መንግስት #እርምጃ ይወስዳል ሲሉ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሐመድ ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቆይታ የሰራዊቱ ወታደራዊ ቁመና የአገሪቱን ሉዓላዊነት እና የሕዝቡን ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል እንደሆነም አመልክተዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopiaOfficial
የታክሲዎች አድማ በአዲስ አበባ ፦

(በአል-ዐይን - AlAIN)

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ተሳፋሪዎች ከፍተኛ የትራንስፖርት እጥረት ገጥሟቸዋል።

ተሳፋሪዋች በታክሲ እጦት ሲንገላቱ ነበር፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከወትሮው የተለዩ ረጃጅም ሰልፎች ተስተውለዋል፡፡

‘ታሪፍ አነሰን’ እንዲሁም ‘በትራንስፖርት ተቆጣጣሪዎች የተጋነነ ቅጣት እየተቀጣን ነው’ በሚሉ ምክንያቶች አድማ የመቱ ታክሲዎች መኖራቸው ተሰምቷል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ስጦታው አከለ “የተወሰኑ ባለታክሲዎች ዛሬ ወደ ስራ እንዳልገቡ እናውቃለን” ብለዋል፡፡ “የታክሲ ባለቤቶች ታሪፍ እንዲሻሻልላቸው ጠይቀውናል ፤ በዚህም የህዝብን የመክፈል አቅም እና የነዳጅ ዋጋን ታሳቢ ያደረገ ማሻሻያ ተደርጓል” ሲሉ ገልጸዋል።

ይሁንና ከላይ ከተቀመጡት ምክንያቶች ውጭ “ዝም ብለን የታሪፍ ማሻሻያ አናደርግም” ያሉት ኃላፊው “በዛሬው አድማ ላይ በተሳተፉት ላይ #እርምጃ እንወስዳለን” ሲሉ ተናግረዋል።

በአድማው የተሳተፉት “ጥቂት ታክሲዋች ናቸው” ያሉት ኃላፊው በከተማው የትራንስፖርት ችግር እንዳይፈጠር ፐብሊክ ባስ፣ ሸገር ባስ እና ድጋፍ ሰጪ አውቶቡሶችን በስፋት በመጠቀም ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በወልቂጤ ከተማና በቀቤና ልዩ ወረዳ 'በወሰን ይገባኛል' ጥያቄ የተነሳው ግጭት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ታማኝ ምንጭ፣ " ግጭቱ ወደ ገጠሩ የመዛመት ሁኔታ ነው የሚስተዋለው። ወልቂጤ ከተማ አልፎ አልፎ  ካልሆነ በቀር የከፋ ነገር የለም " ብለዋል። ወሸርቤ፣ ወልቂጤ ዙሪያ ግጭቱ መዛመት አዝማሚያ ያንዣበበባቸው የገጠር ቦታዎች…
#Update

የጊዜያዊ ኮማንድ ፓስት በወልቂጤ ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዳይገባ እና ወደ መደበኛ ስራው እንዳይመለስ እያደረጉ ነው ያላቸውን ህገ-ወጥ ግለሰቦችን አስጠነቀቀ።

ኮማንድ ፖስቱ ፤ በየቦታው የተለያዩ ትንኮሳዎችን በመፍጠር የከተማው ማህበረሰብ እንዳይረጋጋ እያደረጉ ነው ያላቸውን በስም ጠርቶ ያልገለፃቸውን አካላት በጥብቅ አስጠንቅቋል።

በተጨማሪ ፤ በተሽከርካሪና በእግር የሚንቀሳቀሱ ዜጎች ላይ ህገ-ወጥ ድርጊት እየተፈጸመ እንደሆነ ገልጾ " ይህ መቆም መቻል አለበት " ብሏል። የሚፈፀመውን ድርጊት እንዲሁም ስለፈፃሚዎች በዝርዝር ያለው ነገር የለም።

ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ ከዚህ ሰዓት ጀምሮ ይህን ማስጠንቀዊያ ሳይቀበል ወይም ተግባራዊ ሳያደርግ ቀርቶ በህገ-ወጥ ድርጊት የሚሳተፍ የየመዋቅሩ #የቀበሌ_አመራርና ግለሰብ በጸጥታው አካሉ ለሚወሰድበት #እርምጃ ኮማንድ ፖስጡ ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን በጥብቅ አስጠንቅቋል።

ከሰሞኑን በወልቃጤ ከተማ በተፈጠረ ግጭት የሰዎች ህይወት መጥፋቱ፣ ንብረትም መወደሙ የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia በአማራ ክልል በተለይ በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ትላንት በተጠናቀቀው የካቲት ወር በተፈፀሙ ጥቃቶች በርካቶች ተገድለዋል። ጉዳትም ደርሷል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወሩ ስለነበሩት ሁኔታዎች ከሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ለማግኘት እጅግ በርካታ ቀናትን የወሰደ ሙከራ ቢያደርግም ምንም ምላሽ የሚሰጠ አካል አላገኘም። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ግን ስለነበሩት ሁኔታዎች…
#AmharaRegion

° " ህዝቡ በታጠቁ ቡድኖች ነው ለጥቃት የተዳረገው በገዛ ከተማው ነው መአት ያወረደበት ... ጥቃት ፈፃሚዎቹ ከአጎራባች ' ሸኔ ' ናቸው " - የአጣዬ ከተማ ከንቲባ

° " #ሀሰት_ነው የኦሮሞ አርሶ አደሮች እንጂ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት አይደሉም " " - አባገዳ አህመድ ማህመድ

በአማራ ክልል ፤ የሰሜን ሸዋን እና የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደርን በሚያጎራብቱ አካባቢዎች ላይ ግጭት ከጀመረ ከሳምንት በላይ ሆኖታል።

በተደጋጋሚ ፦
- የሰዎች ደም በሚፈስበት፣
- ንብረት በሚወድምበት ፣
- ሰዎች ቄያቸውን ለቀው በሚፈናቀሉበት በዚህ ቀጠና ባለፈው የካቲት ወር ውስጥም በርካቶች መገደላቸው ይታወሳል።

አሁን ደግሞ #ከ8_ቀናት በፊት የተቀሰቀሰው ግጭት እጅግ መባባሱን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በመነሻው ላይ በሁለቱም በኩል እርስ በእርስ መወነጃጀል ያለ ሲሆን በኤፍራታ ግድምና ቀወት ውስጥ ግጭቱ ከፍቶ መዋሉ ነው የተሰማው።

በሁለቱም በኩል ያሉት ነዋሪዎች ፣ የአጣዬ ከንቲባ ፣ የአካባቢው አባገዳ ምን አሉ ?

በኤፍራታ ግድም ወረዳ የአላላ ከተማ ነዋሪ ፤ ጦርነት ከተጀመረ 8 ቀን መያዙን ፣  ብዙ ቤቶች መቃጠላቸውን ገልጸዋል።

ነዋሪው " የአርሶ አደሮች ዱቄት ሳይቀር ፣ በግ ፣ ፍየል ፣ ግመል ፣ አህያ፣ ከብት በሙሉ ሙልጭ አድርገው ወስደውብናል። ኃላሸት የሚባል ሰውም ገድለውብናል እኛው ክልል ላይ ገብተው " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህን ካደረጉ በኃላ ህዝቡ ተሬ እና ዘንቦ ወደሚባለው አካባቢ በለበሰው ልብስ ሸሽቶ ተጠልሎ እንደሚገኝ ገልጸዋል። " በተከታታይ 18 ሰዎችን ገድለውብናል "ም ብለዋል።

በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር የሰንበቴ ነዋሪ ፤ " እስከ ጅሌ ጥሙጋ ባርሲሳ ፣ ካራ ሌንጫ ፣ መከና ወይም አጣዬ ከተማ ዙሪያ ባሉ ቀበሌዎች ከትላንትና ጀምሮ ተኩስ ነበር። ትላንት አንዲት ሴት እንዲሁም ግመልና ከብቶችም ተመተው ነበር ግጭቱ የቀጠለው በዚህ ነው፤ አንድ ሰው ሲሞት ሁለት ሰው ቆስለዋል፤ አንዱ ወደ አዳማ ተልኳል። ዛሬ ደግሞ 4 ሰው ሲሞት 3 ሰው ቆስሏል " ብለዋል።

ዋነኛው እቅዳቸው የጅሌ ጥሙጋ ከተማ #ሰንበቴን " እንይዛለን ፣ እናጠፋለን " የሚል ነው ሲሉ ገልጸዋል።

አንድ የአጣዬ ነዋሪ ደግሞ ፤ ሰሞኑን ግጭት ተባብሶ ዛሬ አጣዬን በተኩስ ልውውጥ ሲያናውጥ መዋሉን ፣ 5 ሰው መገደሉም. ጥቃት ፈፃሚዎቹ የታጠቁ አካላት " ሸኔ " ናቸው ብለዋል።

ሌላው የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ፣ የሰንበቴ ነዋሪ " ግጭቱ የጀመረው #መጋቢት_አንድ ላይ ነው። ይህም በጅሌጥሙጋ ኮላሽ የሚባል ስፍራ 1 ሰው ገድለው 2 ሰው አቁስለው ከብቶችንም ነድተው ከሄዱ በኃላ ነው ግጭቱን የተስፋፋው " ሲሉ ተናግረዋል።

" ከባልች ቀበሌ እስከ ሰንበቴ እና መከና አጣዬ ድረስ ጦርነት ነው። የዛሬውን ለየት ያደረገው ታጣቂዎቹ #ከሰሜን_ሸዋ ተሰባስበው ፤ እራሳቸውን አደራጀትው ሌሊቱን በተሽከርካሪዎች ተጉዘው መጥተው ውጊያ መክፈታቸው ነው " ሲሉ አክለዋል።

ባለፉት 10 ቀናት 29 ሰዎች መገደላቸውን ተናግረው የተወሰዱት ከብቶችና የወደመው ንብረትም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።

ይህ አስተያየት #አልቀበልም ያሉት የአላላ ነዋሪው ፤ " አማራው ሲያጠፋ በአማራው አጥፊውን መዞ ለህግ ማቅረብ፤ ከኦሮሞውም ሲያጠፋ አጥፊውን መዞ ለህግ ማቅረብ ሰላም የሚያሰፍነው ይሄ ብቻ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" በህግ እና በሽምግልና  ነገሩ መክሰም አለበት እነሱ የሚሉት ከጨፋ ጀምሮ እስከ ሸዋሮቢት ድረስ የኦሮሞ ቦታ ነው። አጣዬም #የኛ_ነች ፤ አላላም ፣ ሞላሌም ፣ ማጀቴም ... ሁሉም የኛ ነው የሚሉት። መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ችግሩን ሊፈታው ይገባል " ብለዋል።

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን #አባገዳ አህመድ ማህመድ " መንገድ የለም። ከጅሌ ጥሙጋ እና አርጡማ ፋርሲ ወረዳዎች እንዲሁም ከዞን መገናኘት አልቻልንም " ብለዋል።

" በዚህ ምክንያት የሃይማኖት አባቶች እና አባ ገዳዎች ተሰባስበው መፍትሄው ምንድነው ? ለማለት መንገዱ ተከፍቶ ለህዝቡ ምግብ ለማድረስ ፣ የቆሰሉትንም ወደ ህክምና ቦታ ለመውሰድ ጥረት ላይ ነን። መንገድ ከተዘጋ 1 ወር ሊሆነው ነው። እኛም ሆነ መንግሥታዊ አመራሩ ሄደን ማየት አልቻልንም። የአማራ ክልልም #ታጣቂዎቹን_ስለሚፈሯቸው ቀርበው ለማነጋገር አልተቻለም። እኛ ጋር ያሉትን #ወሰናችሁን አልፋችሁ አትሂዱ እያልን እየመከርናቸው ነው ። " ገልጸዋል።

ነዋሪዎችና የአካባቢው አስተዳደሮች ጥቃቱን የከፈቱት " ሸኔ (የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) " ናቸው ቢሉም አባገዳ አህመድ " ሀሰት ነው " ብለዋል።

" ሀሰት ነው የኦሮሞ አርሶ አደሮች እንጂ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት አይደሉም። የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እዚህ አልገባም። እየተዋጋ ያለው እራሱ ነዋሪው ነው " ብለዋል።

የአጣዬ ከተማ ከንቲባው ተመስገን ተስፋ ፤ ከተማዋና ህዝቡ በታጠቁ ቡድኖች ነው ለጥቃት የተዳረጉት ብለዋል።

አጣዬ ላይ ' #ወረራ ' መፈፀሙን ገልጸው " ሰውም አልቋል፤ ሚሊሻውም የሚችለውን ያህል ሞከረ አለቀ " ብለዋል።

ይህን የሚፈፅሙት ከአጎራባች  " #ሸኔ በሏቸው " ሲሉ የጠሯቸውን የታጠቁ ኃይሎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

" ዋናው መፍትሄ መንግሥት ጠንከር ብሎ #እርምጃ መውሰድ ያለበት ላይ እርምጃ መውሰድ ፤ ይሄ ነበረ መፍትሄው  አሁን ባለው መንገድ ፣ #በእሹሩሩ ሰውም አለቀ " ብለዋል።

#የአጣዬ_ህዝብ የገዛ ከተማው ላይ እንዳለ መአት እንደወረደበት የገለጹት ከንቲባው " እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነው፤ መንግስት ቢደርስልን ጥሩ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ከኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር በኩል ለጥፋቱ ለችገሩ " የፋኖ ታጣቂዎችን " ተጠያቂ ሲያደርጉ ከሰሜን ሸዋ ዞን በኩል ደግሞ " ሸኔን (የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) " ተጠያቂ ያደርጋሉ።

NB. ባለፉት አምስት ዓመታት አጣዬ ከ10 ጊዜ በላይ የመቃጠል አደጋ አስተናግዳለች።

እስካሁን የአማራ ክልል መንግሥት ስለ ጉዳዩ ያለው ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ #ባለቤትነቱ የቪ.ኦ.ኤ. ራድዮ (ጋዜጠኛ መስፍን አራጌ) መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ቲክቶክ " ኪርጊስታን ውስጥ እንዲታገድ ተወሰነ። ኪርጊስታን " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ ለልጆች አእምሯዊ እድገት እና አጠቃላይ ደህንነት ጠንቅ እየሆነ ነው በሚል ሙሉ በሙሉ እንዲታገድ ወስናለች። ውሳኔውን ያሳለፈው የሀገሪቱ የባህል ፣ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ነው። ሚኒስቴሩ ባደረገው ግምገማ መሰረት " ቲክቶክ " ህጻናት እጅግ ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ ይዘቶችን እንዳያገኙ ለመከላከል በቂ መቆጣጠሪያ…
#Update

የ " ቲክቶክ " እገዳ በኪርጊስታን ተግባራዊ ሆነ።

ኪርጊስታን " ቲክቶክ " በመላ ሀገሪቱ  እንዲታገድ ውሳኔ ማስለፏ ይታወሳል በዚሁ ውሳኔ መሰረት የቴሌኮም አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ትዕዛዙን ወደ መፈጸም #እርምጃ ገብተዋል።

በሀገሪቱ " ቲክቶክ " መስራት እንዳቆመም ተነግሯል።

ሰዎች መተግበሪያውን ሲከፍቱን የሚያገኙት መልዕክት " Unable to load, please try again." የሚል ነው።

ውሳኔው በሀገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት መ/ቤት የተላለፈ ነው።

የኪርጊስታን ዲጂታል ሚኒስቴር ቲክቶክን የሚያስተዳድረው ' ባይት ዳንስ ' ኩባንያ ፥ " #የልጆችን
- አእምሯዊ፣
- አካላዊ፣
- መንፈሳዊ እና #ሥነምግባራዊ እድገትን ለመጠበቅ በህግ የተዘረዘሩ ህጋዊ መስፈርቶችን ማክበር አልቻለም " ብሏል።

በዚህም ምክንያት " ቲክቶክ " በሀገሪቱ እንዳይሰራ ተደርጓል።

ውሳኔው የተቃወሙ አካላት ይህ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ ገደቡ እንዲነሳ ጠይቀዋል። ከገደብ ይልቅ ቁጥጥር ይደረግበት ብለዋል።

ከዚህ ቀደም የኪርጊስታን የባህል፣ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ፥ " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ ለልጆች አእምሯዊ እድገት እና አጠቃላይ ደህንነት ጠንቅ እየሆነ ነው " ማለቱ ይታወሳል።

መተግበሪያው #ህጻናት እጅግ ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ ይዘቶችን እንዳያገኙ ለመከላከል በቂ #መቆጣጠሪያ እንደሌለው ነበር የገለጸው።

በተጨማሪም ለተጠቃሚዎቹ ትክክለኛ የዕድሜ ማረጋገጫ እርምጃዎች እንደለለው እና ተጠቃሚዎችን በአጫጭር የቪዲዮ ክሊፖች ወደ ምናባዊ ግዛት በመሳብ #ሱስ የሚያስይዝ ይዘት እንዳለው አስረድቶ ነበር።

ሚኒስቴሩ " ቲክቶክ " በወጣቱ ትውልድ ደህንነት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳለው በአጠቃላይም ለትውልዱ ጠንቅ እየሆነ እንደመጣ አሳውቆ ነበር።

በሌላ በኩል ፤ አሜሪካ ውስጥ ከመረጃ ደህንነት ጋር በተያያዘ መተግበሪያው እንዲታገድ ከፍተኛ ግፊት እየተደረገ ሲሆን  " ቲክቶክ " ከቻይናው ኩባንያ ካልተፋታ / አሜሪካ የምትቆጣጠረው አይነት ካልሆነ በመላ ሀገሪቱ መታገድ ዕጣ ፋንታ ሊገጥመው ይችላል ተብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#SouthEthiopiaRegion ➡️ " ... በረሀብ ከምንሞት መብታችን እየጠየቅን አደባባይ ላይ መሞት መርጠን ነው ወደ ርእሰ መስተዳድሩ ቢሮ የሄድነው " - የሶዶ ዙሪያ የመንግስት ሰራተኞች ➡️" ማንም መብቱን በነጻነት የመጠየቅ መብት አለው " - የደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃፊዉ አቶ ወገኔ ብዙነህ የ2 ወራት ደሞዛችን ይከፈለን ያሉ የወላይታ ዞን የመንግስት ሰራተኞች አደባባይ መውጣታቸዉን…
#ደመወዝ #ደቡብኢትዮጵያ

° " ...ድርጊቱ የደመወዝ ቅሸባ ነው ሊባል የሚችለው ፤ እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል ሰምተንም አናውቅ " - ሰራተኞች

° " ከእኛ #የሚወርደው የበጀት ሀብት እኮ የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው " - የክልል ፋይናንስ ቢሮ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የመንግስት ሰራተኞች " የደመወዝ ይከፈለን " ጥያቄ በብርቱ ከተነሳባቸው አካባቢዎች አንዱና ዋነኛው የ #ወላይታ_ዞን እንደሆነ ይታወቃል።

ሰራተኞቹ ችግር ሲብስባቸው እና ታግሰው ሲመራቸው ሰልፍ  ጭምር በመውጣት ጥያቄ አቅርበዋል።

ለ3 ወራት ያለ ደመወዝ የቆዩት የመንግስት ሰራተኞች አሁን ላይ #የ40_በመቶ እና #የ50_በመቶ ክፍያ ብቻ እየተፈጸመላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል #የፋይናንስ_ቢሮ ፤ " ደመወዝ ባለመክፈል የመንግሥት ሰራተኛውን እያስራቡ ይገኛሉ " ባላቸው የዞንና የወረዳ የስራ ሃላፊዎች ላይ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ #እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቋል።

ቢሮው ለወረዳዎቹ በቂ በጀት ማስተላለፉን ገልጿል።

" ለሰራተኛው #ግማሽ_ደመወዝ በመክፍል ቀሪውን ለሌላ የወጭ ርዕስ ይጠቀሙበታል " ሲል ወቅሷል።

አሁን በተለያዩ ወረዳዎች እየተከፈለ ይገኛል የተባለው ደመወዝ በዞኑ መንግሥት ሰራተኞች ዘንድ አጥጋቢ ምላሽ ተደርጎ አልተወሰደም።

ሰራተኞቹ ለ ' ዶቼ ቨለ ሬድዮ ' በሰጡት ቃል ፤ " ምላሹ አጥጋቢ ያልሆነ ፣ የሰራተኛውን ስነ ልቦናም የጎዳ ነው " ብለውታል።

የመንግስት ሰራተኞቹ ፥ ደመወዛቸው ባልተለመደ ሁኔታ ተቆራርጦ እየተከፈላቸው እንደሚገኝ ተናግረው ፤ " የሰራተኞች ጥያቄው ተመልሷል ለማለት እንቸገራለን " ብለዋል።

በአብዛኞቹ ወረዳዎች ላይ አሁን እየተከፈለ የሚገኘው የደመወዛቸውን ከ40 እስከ 50 ፐርሰት ያህል መሆኑን ጠቅሰዋል።

ሰራተኞቹ ፦

ደሞዛችን እንደተፈለገ ተቆረጦ እየቀረ ነው፤

አከፋፈሉ የፋይናንስንም ሆኖ የመንግሥት ሰራተኛ አስተዳደር መመሪያን የሚጻረር ነው፤

ድርጊቱ #የደመወዝ_ቅሸባ እንጂ ሌላ ምንም ሊባል አይችልም ምክንያቱም እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል በትኛውም ዓለም ሰምተን አናውቅም ብለዋል።

ሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ዎላይታ ሶዶ ላይ የፋይናንስ ባለሙያዎች ሥልጠናዊ ውይይት አካሄዶ ነበር።

በመድረኩ የደሞዝ ጉዳይ በሰራተኞች ተነስቷል፡፡

የቢሮው ሃላፊ የሆኑት አቶ ተፈሪ አባተ ፥ ፋይናንስ ቢሮ ለወረዳዎች በቂ የበጀት ሀብት እያስተላለፈ እንደሚገኝ አሳውቀዋል።

ወላይታን ጨምሮ በክልሉ አንዳንድ ወረዳዎች ውቅጥ የፋይናንስ ቁጥጥር / ኦዲት / መደረጉን ጠቅሰዋል።

" ወደ ወረዳዎች ሚወርደው የበጀት ሀብት የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው፡፡ ይሁን አንጂ አንዳንድ ወረዳዎች ከአሰራር ውጭ ደመወዝ #በፐርሰንት_እየከፈሉ ሰራተኛው እንዲራብ ፣ በክልሉ ላይም እንዲያማርር እያደረጉ ይገኛሉ " ብለዋል።

ክልሉ በቀጣይ በእነኝህ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ " #ለሽብረቃ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎችን ለመገደብ የሚያስችል የወጭ ቅነሳ መመሪያ ተግባራዊ ይደረጋል " ሲሉ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።

Credit - #ዶቼቨለሬድዮ
@tikvahethiopia