TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዶ/ር ኣርከበ #በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ...

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዩ አማካሪ ዶ/ር #ኣርከበ_እቁባይ በጠና ታመው ሆስፒታል ገብተዋል ተብሎ በፌስቡክ እና መሰል ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ #ስህተት እንደሆነ የዶክተር ኣርከበ የቅርብ ሰውና የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባል የሆኑ ሰው ከደቂቃዎች በፊት በላኩልኝ የፅሁፍ መልዕክት አሳውቀውኛል። ዶክተር ኣርከበ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ለህዝቡ ንገርልኝ ብለዋል።

🗞ቀን ሰኔ 26/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNewsAlert

አቶ ንጉሱ ጥላሁን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው ተሾሙ በሚል የተሰራጨው መረጃ #ሀሰት መሆኑ ተገለጸ፡፡ በዛሬው እለት አቶ ንጉሱ ጥላሁን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሁነው እንደተሾሙ በማህበራዊ የትስስር ገጾች በስፋት የተሰራጨው መረጃ #ስህተት መሆኑን አሐዱ ራድዮ እና ቴሌቪዥን ከአቅርብ ምንጮቼ አረጋግጫለሁ ብሏል። አቶ ንግሱ ጥላሁን የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል ባለመሆናቸው የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የመሆን እድላቸው ጠባብ መሆኑም ተመልክቷል፡፡

ምንጭ፦ አሀዱ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን
🗞ቀን ሰኔ 27/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ይህ ስህተት ታርሟል!

ኤጀንሲው በፌስቡክ ገፁ የ12ኛ ክፍል ፈተና የተሰጠው ሰኔ 3-5 ብሎ ያወጣው መረጃ #ስህተት ነው ታርሟል። ፈተናው የተሰጠው ከሰኔ 6 ጀምሮ ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ!

በተማሪዎች ውጤት ላይ የታየው #ስህተት የተቋሙን ተዓማኒነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለጸ፡፡ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት መገለጹንና ተማሪዎችና ወላጆች ቅሬታ ማቅረባቸውን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ቢሮው በመግለጫው እንዳስታወቀውም በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል የተወሰኑት ውጤታቸው አልተለቀቀም፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጄንሲ የፈተና ውጤቱን የሚያስታካክልበትን ግልጽ መስፈርት ሊያሳውቅ እንደሚገባም ቢሮው ጠይቋል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አፈ ጉባኤዋ ይቅርታ ጠየቁ!

የደቡብ ክልል ምክር ቤት #ዋና_አፈ_ጉባኤ የምክር ቤቱ አባላት #ይቅርታ ያድርግልኝ ሲሉ በይፋ ጠየቁ። ዋና አፈ ጉባኤዋ ወይዘሮ ሄለን ደበበ ዛሬ ረፋድ ላይ የተጀመረውን የክልሉን አምስተኛ ዙር መደበኛ ጉባኤ በንግግር ሲከፍቱ ላለፉት አስራ አንድ ወራት የምክር ቤቱን መደበኛ ጉባኤዎች ባለመጥራቴ የተከበሩ የምክር ቤት አባላት ይቅርታ ያድርጉልኝ ሲሉ ተማፅነዋል።

የህዝብ ውክልና ያለው ምክር ቤት በየጊዜው ማከናወን የነበረበትን ስብሰባ አለማድረጉ በየትኛውም መመዘኛ #ትክክል አይደለም ያሉት ዋና አፈ ጉባኤዋ በቀጣይ ተመሳሳይ #ስህተት እንደማይደገም በምክር ቤቱ ፊት ቃል እገባለሁ ብለዋል። በእርግጥ እንደምክንያት ማቅረብ ባይቻልም ምክር ቤቱ ማድረግ የነበረበትን መደበኛ ጉባኤዎች ሳያካሂድ የቀረው ክልሉ አጋጥሞት ከነበረው ነባራዊ ሁኔታ የተነሳ መሆኑን አፈ ጉባኤዋ ተናግረዋል።

የደቡብ ክልል ምክር ቤት በዓመት #አራት መደበኛ ጉባኤዎችን ማድረግ የሚገባው ቢሆንም ባለፈው የጥቅምት ወር የመጀመሪያውን ስብስባ ካደረገ ወዲህ ዳግም ሳይሰበሰብ ነው የበጀት ዓመቱ የተጠናቀቀው። በዚህም ምክንያት የክልሉ ዓመታዊ በጀት እስከአሁን ባለመፅደቁ የአስፈጻሚ ቢሮዎች ከሀምሌ 1 2012 ዓም ጀምሮ መደበኛ ስራዎቻቸውን በምክር ቤት ባልጸደቀ በጀት ሲያከናውኑ ቆይተዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ዋቸሞ_ዩኒቨርሲቲ

የአዲስ ተማሪዎች መግቢያ ቀን ማስተካከያ⬆️

"በምትመለከቱት ማስታወቂያ ላይ ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥቅምት 28 እና 29 የሚለው የፅሁፍ #ስህተት ስለሆነ መስከረም 28 እና 29 ተብሎ ይስተካከል። በተጨማሪም አዲስ በዱራሜ ካምፓስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀን ጥቅምት 5 እና 6 መሆኑን እንገልፃለን።" ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

#share #ሼር

የዩኒቨርሲቲ ጉዳዮችን በስፋት በTIKVAH-MAGAZINE ታገኛላችሁ👇
https://publielectoral.lat/joinchat/AAAAAEcez-UrldBjOpa-qQ
#WeyzeroTsionTeklu

ክብርት ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ!

ክብርት ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ ከመጋቢት 28 ቀን 2012 ዓም ጀምሮ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሹመዋል።

ክብርት ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዳያስፖራና ኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዘርፍን በሚኒስትር ዴኤታነት ይመራሉ።

ክብርት ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ከመሾማቸው በፊት ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን አገልግለዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በፌስቡክ ገፁ ላይ ባሰፈረው መረጃ ወ/ሮ ፅዮን 'የኢፌዴሪ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ' በመሆን አገልግለዋል የሚለው #ስህተት ነው። ማስተካከያ ቢደረግበት መልካም ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ተደርጓል። በዚህ መሰረት ፦ • ቤንዚን ባለፈው ወር ሲሸጥበት ከነበረው ዋጋ ጭማሪ በማድረግ በሊትር 31 ብር ከ74 ሳንቲም እንዲሸጥ ተወስኗል። • ነጭ ናፍጣ 28 ብር ከ94 ሳንቲም፣ • ነጭ ጋዝ 28 ብር ከ94 ሳንቲም፣ • ቀላል ጥቁር ናፍጣ 23 ብር ከ73 ሳንቲም፣ • ከባድ ጥቁር ናፍጣ 23 ብር ከ29 ሳንቲም …
' የቤንዚን ዋጋ 31 ብር ከ74 ሳንቲም ነው '

አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች በታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች ችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ በተደረገው ማስተካከያ የቤኒዚን ዋጋ 34 ብር ከ71 ሳንቲም በማለት እያሰራጩት ያለው መረጃ #ስህተት ነው።

በተደረገው የታህሳስ ወር ማስተካከያ የቤንዚን ዋጋ 31 ብር ከ74 ሳንቲም ነው እንዲሸጥ የተወሰነው።

በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም የነበሩት ወራት የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ምን እንደሚመስል መለስ ብለን እንመልከት።

ከየካቲት 27/2013 ዓ/ም እስከ መጋቢት 30/2013 ዓ/ም በነበረው የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ (በሊትር) የነበረው ፦

• ቤንዚን 👉 25 ብር ከ86 ሳንቲም
• ኢታኖል ድብልቅ ቤንዚን 👉 25.36 ሳንቲም
• ነጭ ናፍጣ 👉 23 ብር ከ18 ሳንቲም
• ኬሮሲን 👉 23 ብር ከ18 ሳንቲም
• ቀላል ጥቁር ናፍጣ 👉 20 ብር ከ27 ሳንቲም
• ከባድ ጥቁር ናፍጣ 👉 19 ብር ከ78 ሳንቲም
• የአውሮፕላን ነዳጅ 👉 38 ብር ከ60 ሳንቲም ነበር።

ከዚህ በኃላ ፦

🗓ከመጋቢት 26 እስከ ሚያዚያ 30/2013 ዓ/ም ከአውሮፕላን ነዳጅ ውጭ ሁሉም ባለበት ቀጥሏል።

🗓ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 28/2013 ዓ/ም ከአውሮፕላን ነዳጅ ውጭ ሁሉም ባለበት ቀጥሏል።

🗓ከግንቦት 28 እስከ ሰኔ 30/2013 ዓ/ም ከአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ ውጭ ሁሉም ባለበት ቀጥሏል።

🗓ከሰኔ 30 እስከ ሀምሌ 30/2013 ዓ/ም ከአውሮፕላን ነዳጅ ውጭ ሁሉም ባለበት ቀጥሏል።

🗓ከነሃሴ 1 እስከ ነሃሴ 30/2013 ዓ/ም ከአውሮፕላን ነዳጅ ውጭ ሁሉም ባለበት ቀጥሏል።

🗓ከጳጉሜ 1 እስከ መስከረም 30/2014 ዓ/ም የአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ ጨምሮ ሁሉም ባለበት ቀጥሏል።

🗓ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 30/2014 ዓ/ም ከአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ ውጭ ሁሉም ባለበት ቀጥሏል።

🗓ከጥቅምት 30 እስከ ህዳር 30/2014 ዓ/ም ከአውሮፕላን ነዳጅ ዋጋ ውጭ ሁሉም ባለበት ቀጥሏል።

በታህሳስ ወር በተደረገው ማስተካከያ ደግሞ ፦

• ቤንዚን 👉 31 ብር ከ74 ሳንቲም
• ነጭ ናፍጣ 👉 28 ብር ከ94 ሳንቲም፣
• ነጭ ጋዝ 👉 28 ብር ከ94 ሳንቲም፣
• ቀላል ጥቁር ናፍጣ 👉 23 ብር ከ73 ሳንቲም፣
• ከባድ ጥቁር ናፍጣ 👉 23 ብር ከ29 ሳንቲም
• የአውሮፕላን ነዳጅ 👉 58 ብር ከ77 ሳንቲም እንዲሸጥ ተወስኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህን መረጃ ያሰባሰበው ከዚህ ቀደም በንግድ እና ኢንዲስትሪ ሚኒስቴር በኩል ይፋ የተደረጉትን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ወደኃላ ተመልሶ በመመልከት ነው።

NB : ከጥቅምት ወር 2014 ዓ/ም ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ በተመለከተ ይፋ እየተደረጉ ያሉት በአዲሱ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በኩል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ በከተማዋ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጳጉሜን 5 ቀን 2014 ዓ.ም የካዳስተር ምዝገባ እና እወጃ ሥራ እንደሚካሄድ አሳውቋል። ከዚህ ቀደም የመሬት ይዞታቸውን በካዳስተር ያላስመዘገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች መረጃዎቻቸውን ለሚቀጥሉት ተከታታይ 15 ቀናት ማዘጋጀት እንደሚችሉ ተነግሯል። ከተማ አስተዳደሩ ከ10 ዓመት በፊት ጀምሮ ሕጋዊ…
#AddisAbaba

" ... የመሬት አገልግሎት ከተመረጡ 25 ቀጠናዎች በስተቀር በሁሉም ክፍለ ከተሞች ላይ መደበኛ አገልግሎት ይሰጣል " - ኤጀንሲው

የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ማምሻውን ለከተማው ኮሚኒኬሽን በሰጠው መረጃ ፤ በአዲስ አበባ ከተማ የመሬት አገልግሎት ከተመረጡ 25 ቀጠናዎች በስተቀር በሁሉም ክፍለ ከተሞች ላይ መደበኛ አገልግሎት ይሰጣል አለ።

መረጃውን ይፋ ባደረገው የከተማው ኮሚኒኬሽን ገፅ ላይ ፥ የተመረጡ 25 ቀጠናዎች ይባል እንጂ በዝርዝር የተገለፀ ነገር የለም።

ኤጀንሲው በተመረጡ 25 ቀጠናዎች ላይ የይዞታ ምዝገባ የሚያከናውን በመሆኑ ምዝገባውን በሚከናወንባቸው አካባቢዎች ብቻ እስከ ጳጉሜ 5 /2014 ዓ.ም አገልግሎት የሚቋረጥ መሆኑን ገልጿል።

ዛሬ " የመሬት አገልግሎት በሁሉም አካባቢዎች ላይ እንደማይሰጥ " የተሰራጨው መረጃ #ስህተት እንደሆነ ኤጀንሲው አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም ይዞታቸውን በ " ዲጂታል ስርአት " ያስመዘገቡ ባለይዞታዎች አገልግሎት ማግኘት ይችላሉም ተብሏል።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Sidama #Hawassa #Motor

በሀዋሳ ከተማ ከሞተር ሳይክል የታርጋ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ 221 ሞተሮች መያዛቸዉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ፍሰት ቁጥጥር እና ስምሪት ክፍል ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

በአንፃሩ የሞተር ባለቤቶች ፤ " መንግስት የሞተር ሳይክል ታርጋ የለም ይለናል፤ በሌላ በኩል ደሞ ትራፊክ ፓሊስ ታርጋ የላቹም ብሎ ያሳድደናል " ሲሉ ቅሬታ አሰምተዋል።

አንዳንዶች ደግሞ የቀድሞው የደቡብ ክልል  ታርጋ ወደ ሲዳማ ታርጋ መቀየር አለበት በሚል የመያዝና የማንገላታት ነገርም አለ ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል።

የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የትራፊክ ፍሰት ቁጥጥር እና ስምሪት ምክትል ዳይሬክቶሬት ኃላፊ ኢንስፔክተር ተስፋዬ ደምሴ ፤ ህብረተሰቡ ህጋዊ  ታርጋ በማዉጣት ህጋዊ ይሆን ዘንድ 221 ሞተሮች መያዛቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ኢንስፔክተር ተስፋዬ አክለውም፤ " የደቡብ ታርጋ አየተያዘ ነዉ " የሚባለዉ #ስህተት መሆኑን በመግለጽ ማንም በነጻነት ማሽከርከር እንደሚችል ገልጸዋል።

" በዚህ ምክንያት የታሰሩ ሞተሮች ካሉ ስህተት ነው፤ ይለቀቃሉ። የደቡብ ክልል ታርጋ እስካልሸጠ እስካለወጠ ድረስ ችግር የለውም " ሲሉ አረጋግጠዋል።

ከአዲስ ታርጋ ጋር በተያያዘ በጹሑፍ ቅሬታቸውን ያቀረቡ የሀዋሳ ቲክቫህ ቤተሰብ አባል ፤ " መንግስት የሞተር ሳይክል ታርጋ የለም ይለናል፤ በሌላ በኩል ደሞ ትራፊክ ፓሊስ አባላት ታርጋ የላቹም ብለው ያሳድዱናል። እኔ በግሌ 2% ግብር ከከፈልኩ ወራቶች ተቆጥረዋል ነገር ግን ታርጋ ማግኘት አልቻልኩም የሚመለከተው አካል መፍትኤ ይስጠን፤ ትራፊክ ፓሊስ አባላት እያንገላቱን ነው " ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ይህንን አስመልክቶ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የሀዋሳ ከተማ መንገድ ትራንስፖርት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደስታ ዳንቾ ችግሩ መኖሩን በማመን ችግሩ ከሀገራዊ የዶላር ችግር ጋር ተያይዞ የመጣ (ለታርጋ ማሳተሚያ) መሆኑን አንስተዋል።

" አሁን ላይ ህትመቱ በማለቁ በሚቀጥለዉ ሳምንት ይሰጣል " ብለዋል።

ዳይሬክተሩ አክለውም፥ ታርጋ ያልደረሳቸዉ አሸከርካሪዎች ሪሲት በማሳየት እንዲንቀሳቀሱ የተያዙትም እንዲለቀቁ ከከተማዉ ትራፊክ ፖሊስ አመራሮች ጋር መግባባት ላይ ደርሰናል " ሲሉ ምላሽ  ሰጥተዉናል።

መረጃው የተዘጋጀው በሀዋሳ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia