የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ!

በተማሪዎች ውጤት ላይ የታየው #ስህተት የተቋሙን ተዓማኒነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ መሆኑን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለጸ፡፡ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት መገለጹንና ተማሪዎችና ወላጆች ቅሬታ ማቅረባቸውን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ቢሮው በመግለጫው እንዳስታወቀውም በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል የተወሰኑት ውጤታቸው አልተለቀቀም፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጄንሲ የፈተና ውጤቱን የሚያስታካክልበትን ግልጽ መስፈርት ሊያሳውቅ እንደሚገባም ቢሮው ጠይቋል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia