TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Mekelle

ላለፉት ዓመታት በጦርነት ውስጥ ያሳለፈችው ትግራይ ከተደረገው የሰላም ስምምነት በኃላ አሁን ላይ በመጠኑም ቢሆን ፊቷን ወደ #ልማት ስራዎች እያዞረች ትገኛለች።

በክልሉ መዲና መቐለ በጦርነቱ ምክንያት ተስተጓግሎ የነበሩ የመቐለ የመንገድ ፕሮጆክቶች ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ ነው ተብሏል።

ትላንት መቐለ ከተማ እና ሱር ኮንስትራክሽን አንድ ውል ተፈራርመዋል። የመቐለ ከተማ እና ሱር ኮንስትራክሽን የተፈራረሙት 62 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የአስፓልት እና ጠጠር መንገድ ለመገንባት ነው።

ለዚሁ ፕሮጀክት የስድስት ነጥብ አንድ ቢልዮን ብር በጀት እንደተያዘለት ነው የተነገረው።

ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተስፋ የሚሰጥ እንዲሁም ትግራይን ደግም ለመገንባት በሚደረገው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ተስፋ ሰጪ ነው ተብሎለታል።

ፕሮጀክቱ ከሁለት እስከ ሶስት አመት ባለው ግዜ ውስጥ ገንብቶ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ በውል ስነስርዓቱ ላይ ስለመገለፁ ድምፂ ወያነ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba 🛫 #Mekelle

ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ ትግራይ መቐለ አቅንተዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመገኘት ዛሬ ወደ መቐለ አቅንተዋል።

ቅዱስነታቸው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትንና ሊቃውንትን አስከትለው ነው ወደ መቐለ የተጓዙት።

ቅዱስነታቸው ወደ ትግራይ፣ መቐለ ሲጓዙ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የኒውዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው  ከቅዱስነታቸው ቡራኬ መቀበላቸውን የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልጹ ፅ/ቤት አሳውቋል።

ምንጭ፦ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልጹ ፅ/ቤት

@tikvahethiopia
#Mekelle

የኢፌዴሪ የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የባለድርሻ እና አጋር አካላት የውይይት መድረክ #በመቐለ ለመጀመርያ ጊዜ ይካሄዳል።

ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ የባለድርሻ እና አጋር አካላት መድረክ ለመጀመርያ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን በመቐለ እንዲደረግ የተወሰነበት ምክንያት ከሰላም ስምምነቱ ብኋላ ክልሉ ላይ አንፃራዊ  መረጋጋት መፈጠሩ እና በሁለቱም ተስማሚ ወገኖች የመተማመን ጉዳዩ መጎልበቱን ማሰያ ነው ብሏል።

በመድረኩ ለመሳተፍ የተለያዮ ባለድርሻ እና አጋር  አካላት ከፌዴራል መንግስት የተላከ የልኡኳን ቡድን  በአምባሳደር ተሾመ ቶጋ መሪነት ዛሬ መቐለ ገብቷል።

የፌደራል መንግስቱ ልኡኳን ብድኑ ከጠቅላይ ሚኒስተር ፅህፈት ቤት፣ የሰላም ሚኒስቴር ፣ የመከላከያ ሰራዊት፣ የሰቪክ ማህበራት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት  እንዲሁም ከንግድ ሚኒስቴር እና የተለያዮ ክልሎች ተወካዮች ያካተተ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

#ድምፂወያነ

@tikvahethiopia
#Mekelle

በዶ/ር ሊያ ታደሰ የተመራ ልዑክ መቐለ ገባ።

በጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የተመራው የጤና ሚኒስቴር ልዑካን ቡድን ዛሬ መቐለ ገብቷል።

ልዑኩ ከክልሉ አስተዳደር ጋር በተለያዩ የጤና ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚነጋገር ይጠበቃል።

ፎቶ ፦ ድምፂ ወያነ

@tikvahethiopia
#Mekelle

የመቐለ ወደብና ተርሚናል አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አስታውቋል።

በጦርነት ተቋርጦ የቆየው የመቐለ ወደብና ተርሚናል ወደ መደበኛ አገልግሎት መመለሱ ተገልጿል።

በዚህም መዳረሻቸው መቐለ ወደብና ተርሚናል ለሆኑ ገቢ ጭነቶችን  ከዛሬ ሚያዝያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከመነሻ የባሕር ወደብ ለመቐለ ኦፕሬሽን መክፈት የሚቻል መሆኑ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሰላም ልኡካኑ መቐለ ትግራይ ሲደርሱ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካብኔ ጉዳዮች ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ አማኑኤል አሰፋ እና ሌሎች የክልሉ አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ልዑኩ በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ…
#Mekelle

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የተመራው የሰላም ልኡክ ዛሬ ከሰአት በተለምዶ " መቐለ 70 ካሬ " ተብሎ በሚጠራው የተፈናቃዮች መጠለያ ጉብኝት አድርጓል።

በጉብኝቱ ተፈናቃዮች " ቅዱስ ሲኖዶሱ ለበዳዮች ወግንዋል " በማለት በድምፅና በፅሁፍ ተቋውሞ ማሰማታቸውን በስፍራው የነበሩ የመቐለ ቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ገልጸዋል።

ቅዱስ ፓትሪያርኩ ፤ " በውስጣችሁ የሚሰማችሁን እንኳን ተናገራችሁ " ካሉ በኋላ ፤ " ሰሚ ከተገኘ ወደ ቀያችሁ እንድትመለሱ ለሚመለከተው እንናገራለን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
#Mekelle

" በመቐለ ከተማ ከ184 ሄክታር በላይ የመንግስትና የህዝብ መሬት መጭበርበሩ በጥናት ተረጋግጧል " - የከተማዋ ከንቲባ ይትባረክ ኣምሃ

በትግራይ የነበረውን ጦርነት ተከትሎ በክልሉ ከተሞች ህገ ወጥነት ተንሰራፍቶ በርካታ ወንጀሎች መፈፀማቸው የመቐለ ከንቲባ ይትባረክ ኣማሃ ገለፁ።

ከንቲባው ፤ የመንግስትና የህዝብ መሬት ዘረፋና የፀጥታ መደፍረስ ዋነኛ ተጠቃሽ ችግሮች እንደሆኑ ጠቁመዋል።

የመሬት ወረራው የተካሄደው ለምቶ ወደ ተጠቃሚዎች ለመተላለፈ በተዘጋጀ ፤ በእርሻና በመንግስት ክፍት ቦታ ፤ ከገጠር ወደ ከተማ በተካለለና በተቀሙ የኢንቨስትመንት መሬቶች መሆኑ የገለፁት አቶ ይትባረክ ፤ " በህገወጥ ተግባሩ 3337 ሰዎች ተሳትፈዋል " ብለዋል።

" በመሬት ወረራው የተሳተፉ ህገወጦች በህግ እንዲጠየቁ የህዝቡ ጥያቄ ጭምር ነው " ያሉት ከንቲባ ይትባረክ " ከእርምጃው በፊት የተወረረው መሬት ማጥናት ፣ ቦታዎቹ የሰነዱ ፋይሎች ድህንነት ማረጋገጥ ተጠናቅቆ ወደ ተግባር ተገብቷል " ሲሉ ገልጸዋል።

አሳሳቢ የሆነውን የከተማዋ የፀጥታ ጉዳይ ለመፍታት እየተሰራ  መሆኑ የገለፁት አቶ ይትባረክ በተካሄደው ጥናትና ክትትል በቡድን የሚዘርፉ ፣ ህገ-ወጥ ሕትመት የሚያካሂዱ ፣ የመሬት ፕላን ሰርተው የሚሸጡ ፣ አደንዛዥ ዕፅ የሚያዘዋውሩ የፎርጅድ ገንዘብ ማተምያ ማሽንና የተለያዩ ህገ ወጥ ገንዘቦች እጅ በፈንጅ ተይዘዋል ብለዋል።

የመሬት ወረራ ሆነ የሚፈፀሙ ህገወጥ ተግባራት ለመቆጣጠር እየተሰራ መሆኑ ያብራሩት ከንቲባው ህዝቡ መረጃና ሰነዶች ከመስጠት እስከ መመስከር ንቁና ተባባሪ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

መረጃውን የመቐለ ቲክቫህ አባል የተላከ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በመቐለ ከተማ በተወረወረ የእጅ ቦምብ የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ። ቦምብ ተወርውሮ የሞት አደጋው ያጋጠመው ነሃሴ 18 /2015 ዓ.ም ከሌሊቱ 8:00 ሰአት ነው። የአይን እማኞች ለቲክቫህ የመቐለ ቤተሰብ እንደገለፁት ፤ የቦምብ አደጋው ያጋጠመው በከተማው ቀዳማይ ወያነ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 15 " ዳዕሮ " ተብሎ በሚጠራው መጠጥ ቤት ነው።  የአይን እማኞቹ አክለው እንደገለፁት ፤ በመጠጥ ቤቱ ሰዎች በብዛት…
#Mekelle

የመቐለ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ትላንት ለሊት 8 ሰዓት ላይ ቀበሌ 15 " ዳዕሮ " በሚባለው መጥጥ ቤት ቦንብ የተወረወረው " በቀድሞ ተሰናባች ታጋይ " በነበረ ግለሰብ መሆኑን ታውቋል።

እንደ ፖሊስ መረጃ ተጠርጣሪው እስካሁን አልተያዘም።

የመቐለ ከተማ ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ኃላፊው ኮማንደር ወልዳይ ማውጫ ፤ " ከአሸንዳ በዓል ጋር በተያያዘ በከተማዋ ከፍተኛ የፀጥታ ቁጥጥር ሲደረግ ቆይቷል " ብለዋል።

" በበዓሉ መዝጊያ ቀን ትናንት ግን በከተማዋ ቀዳማይ ወያነ ክፍለከተማ አሳዛኙ የቦንብ ጥቃት ተፈፅሞ ለበርካቶች ሞት እና ጉዳት ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ጥቃቱን የፈፀመው ግለሰብ ማንነቱ ተለይቷል " ያሉት ኮማንደር ወልዳይ የተሰናበተ የቀድሞ ታጋይ መሆኑንና በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

የተወረወረው ኤፍዋን የተባለ የእጅ ቦንብ መሆኑን ፖሊስ አረግጧል። የጥቃቱ አላማም " የግለሰቦች ጠብ " መሆኑን አስረድቷል።

ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል በበኩሉ 20 በቦንብ ጥቃት የቆሰሉ ሰዎች ከሌሊቱ 8 ሰዓት ጀምሮ መቀበሉን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል ገልጿል።

ትላንት ለሊት በተወረወረው ቦንብ 5 ሰዎች መሞታቸውንና በርካቶችም መቁሰላቸውን የመቐለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የሆስፒታል ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Mekelle

በመቐለ ቀዳማይ ወያነ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 15 " ትላንት ለሊት " ዳዕሮ " ተብሎ በሚጠራ መጠጥ ቤት ቦንብ ወርውሮ የሰዎችን ህይወት የቀጠፈውና ለጉዳት የዳረገው ተጠርጣሪ ግለሰብ ስሙ ሙሉጌታ እንደሚባል ታውቋል።

ፖሊስ ግለሰቡ የተሰናበተ የቀድሞ ታጋይ መሆኑንና " በቁጥጥር ስር ለማዋል " ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልጾ ህዝቡ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።

ተጠርጣሪው በመቐለ ከተማ በተለይ ቀበሌ 14 ፣ 15 ፣ 16፣ 17 በደንብ ይታወቃል ያሉን የመቐለ ቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ፤  የቀድሞ ታጋይና የኮሌኔልነት መአርግ ያለው ጭምር ነው በማህበረ ረድኤት ትግራይ /ማረት/  ሹፌር ሆኖም ሲሰራ ነበር ብለዋል።

ተጠርጣሪው በ2013 ዓ.ም መልሶ ወደ ትጥቅ ትግል መግባቱን በኃላም ከትግል መሰናበቱን የመቐለ ቲክቫህ ቤተሰብ አባላት አመልክተዋል።

ፖሊስ ተሰናባቹን የቀድሞ ታጋይና ቦንብ ወርውሮ የሰዎችን ህይወት ያጠፋውን እንዲሁም መከፍተኛ የአካል ጉዳት የዳረገውም " ሙልጌታ "ን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሁሉም እንዲተባበር ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#Mekelle

በጦርነት የተጎዱ የትግራይ ኃይል አባላት በዛሬው ዕለት በመቐለ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል።

ሰልፈኞቹ
የ 85ቱ፣ 93 ቱ በ2015 ደገሙት፤
ድምፃችን ይሰማ ፤
ለህዝብ እንጂ ለግለሰብ አልታገልንም፤
ተጠቅመው ጥለውናል፤
መንግሰት ያየ ፍትህ ያየ ፤

የሚሉና ሌሎች መፈክሮች እያሰሙ በመቐለ ዋና ዋና መንገዶች ድምፃቸው አሰምተዋል።

ይህንን ዘገባ እስከተጠናከረበት ድረስ ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት የተሰጣቸው መልስ የለም።

ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ፓሊስ ስነ-ስርዓት በማስከበር መሳተፉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከቦታው ዘግቧል።

Via @tikvahethiopiatigrigna (መቐለ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
 #Mekelle

" መንግስት ያልፈቀደው ሰልፍ የቀሰቀሱና የተሳተፉ ከ49 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል " - ፓሊስ

" ከሰላማዊ የተቋውሞ ሰልፉ ጋር በተያያዘ ከ150 በላይ ሰዎች በፓሊስ ተደብድበው ታስሯል" - የተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲ አመራር

የመቐለ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ኮማንደር ወልዳይ መውጫ ጳጉሜን 2 / 2015 ዓ.ም በከተማው ሮማናት አደባባይ በተፎካካሪ ፓርቲዎች ሊካሄድ የተጠራው ሰላማዊ የተቋውሞ ሰልፍ በማስመልከት ዛሬ ጳጉሜን 3 ለክልሉ ሚድያዎች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ፤ መንግስት ያልፈቀድው ሰልፍ የቀሰቀሱና የተሳተፉ ከ49 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውለናል ብለዋል።

" ሁሉም ሰው ከህግ በታች እንጂ ከህግ በላይ አይደለም " ያሉት የፓሊስ አዛዡ " ፖሊስ መንግሥት ያልፈቀደውን ሰልፍ ማድረግ አትችሉም ብሎ ቢያስጠነቅቅም ፤ ለ20 ደቂቃ ያህል በአምቢተኝነት ከፓሊስ ጋር ለመጋጨት የሞከሩ ነበሩ " ብለዋል።

ፓሊስ ከጳጉሜን 1 /2015 ዓ.ም ረፋድ ጀምሮ  በመንግስት ያልተፈቀደው ሰልፍ እንዳይቀሰቅሱና እንዳይመሩ ለተፎካካሪ ፓለቲካ ፓርቲ አመራሮች ምክር መሰጡትንና ፤ ምክሩ ችላ ብለው ከሰዓት በኋላ 10:30 አከባቢ አመራሮቹ ሰልፉ እንዲካሄድ የሚቀሰቅስ ወረቀት ሲለጥፉ እጅ በፈንጅ  ተይዘው በቁጥጥር ስር ውለዋል ፤ በተጨማሪ ጳጉሜን 2 / 2015 ዓ.ም ጠዋት ሰልፉ ለማስተባበርና ለመሳተፍ የተገኙ ቀሪ አመራሮች መያዛቸው ገልፀዋል።   

ፓሊስ የተሰጠው ህግ የማስከበር ሃላፊነት መሰረት በማድረግ ግርግር ለመፍጠር የሞከሩ በደቂቃዎች በመቆጣጠር የመቐለ ከተማ እንቅስቃሴ ከወትሮ የተለየ የፀጥታ ስጋት እንዳይታይባት ማድረግ መቻሉንና ፤ ህዝቡ ያልተፈቀደውን ሰልፍ ለማደረግ የመኮሩ ጥቂቶች ሰርአት እንዲይዙ የማድረግ ሚናው በመወጣቱ አመስግነዋል። 

የውድብ ናፅነት ትግራይ (ውናት ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ አለምሰገድ አረጋይ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለምልልስ በበኩላቸው " ፓሊስ ሰልፉ ለመታደም በመጡ ድብድባ ፤ ማንገላታትና ባጠቃላይ ኢ-ሰብአዊ የሆነ ግፍ ፈፅመዋል " ብለዋል።

" ፓሊስ 50 ሊቀመናብርትና የማእከላይ ኮሚቴ አመራሮች የሚገኙባቸው ከ150 በላይ ሰዎች አስረዋል " ያሉት አቶ አለምሰገድ ፤ የዓረና ሉአላውነትና ለዴሞክራሲ ሊቀመንበር ዓምዶም ገ/ስላሴ ፣ የባይቶና ግዚያዊ አስተዳዳሪ ኪዳነ አመነ ከታሳሪዎች መካከል ናቸው ብለዋል። 

" ይህን መሰል አፈና ሊቆም የሚችለው ገዢው ፓርቲ ህወሓት ከስልጣኑ ሲነሳ ነው " ያሉት አመራሩ ህዝቡ ትግሉ አጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክት አስተላልፈዋል። 

የግዚያው አስተዳደሩ ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ጳጉሜን 1/2015 ዓ.ም ለሚድያዎች በሰጡት ሰፊ ቃለመጠይቅ "... ሰልፍ ማድረግ መብት ነው : ቢሆንም በክልሉ ካለው ከባድ የፀጥታ ስጋት አንፃር ስልፉ ማካሄድ አስቸጋሪ ነው " ማለታቸው ይታወሳል።  
                
መረጃውን የመቐለ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው ያደረሰን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የመቐለ ከተማ ፖሊስ ጳጉሜን 2 /ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጠርተውት መንግስት ሳይፈቅድ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ በማነሳሳትና በመሳተፍ ምክንያት በቁጥጥር ሰር ያዋላቸውን እፈታ መሆኑን ገልጿል። የተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮች ለቲክቫህ በሰጡት ቃል ፤ " ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ጨምሮ የፓለቲካ ፓርቲ ሊቃነ መናብርትና ጋዜጠኛ ገና አልተፈቱም " ብለዋል። ከመቐለ ከተማ ፓሊስ የተገኘ መረጃ እንደሚያስረዳው ፦…
#Mekelle

" በአምባገነን ስርአት ምክንያት መብታችን እንዲቀማ እንፈቅድም " - አቶ ዓምዶም ገ/ስላሴ

በትግራይ መቐለ ከተማ " ኪዳን ንሱር በቆስ ለውጢ " በሚል መሪ ቃል ከጳጉሜን 2/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሊካሄድ ከተጠራው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጋር በተያዘዘ በቁጥጥር ስር የነበሩ የተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲ ሊቃነመናብትና  ከፍተኛ አመራሮች በሙሉ መለቀቃቸው ታውቋል።

የዓረና ለሉአላዊነትና ለዴሞክራሲ ሊቀመንበር አቶ ዓምዶም ገ/ስላሴ ፣ የውድብ ናፅነት ትግራይ ሊቀመንበር ዶ/ር ደጀን መዝገበ ፣ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ሊቀመንበርና ከፍተኛ አመራር አቶ ሃያሉ ጎዲፋይና አቶ ዓብለሎም ገ/ሚካኤል ፣ የብሄራዊ ባይቶና ዓባይ ትግራይ አስተባባሪዎች አቶ ኪዳነ አመነና ክብሮም በርሀ ጳጉሜን 6/2015 ዓ.ም ከተለቀቁት መካከል ናቸው።

እንዲሁም ሰላማዊ ሰልፍ በተጠራበት ሮማናት አደባባይ ተገኝቶ በፓሊስ ተድብድቦ በቁጥጥር ስር የቆየው ጋዜጠኛ ተሻገር ፅጋብም ተለቋል።

የዓረና ሊቀመንበር አቶ ዓምዶም ገ/ስላሴ ለአሜሪካ ድምፅ እንዳሉት እሳቸው ጨምሮ 150 የሰልፉ ተሳታፊዎች መታሰራቸው ፤ ዓርብ ጳጉሜ 3 /2015 ዓ.ም 6 የአራት ተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች  ፍርድ ቤት ቀርበው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ቢወሰንም ፤ ፓሊስ ፍቃደኛ ባለመሆኑ እስከ ጳጉሜን 6 /2015 ዓ.ም መታሰራቸው ገልፀዋል።       

" ሰላማዊ ሰልፍ መከልከሉ ፤ ግርፋትና እስራቱ ፣ አልፎም ከፍርድ ቤትና ዳኛ በላይ መሆን የመሰለ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው የተፈፀመው " ያሉት አቶ ዓንዶም ፤ " በአምባገነን ስርአት ምክንያት መብታችን እንዲቀማ እንፈቅድም  ፤ መብታችን መስዋእትነት ጭምር በመከፈል እናረጋግጣለን ፤ ቀጣይ ሰላማዊ ሰልፎች ፣ ህዝባዊ ስብሰባዎች ሌሎች ፓለቲካዊ እንቀስቃሴዎች በማካሄድ ህዝቡ የዴሞክራሲያዊ መብት ባለቤት እስኪሆን ድረስ እንታገላለን  " ብለዋል። 

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲካሄድ አልፈቀድኩም ካለው የጳጉሜን 2 ቱ ሰልፍ ጋር በተሳሰረ ከተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር የታሰሩት 49 እንደሆኑ የጠቀሱት የመቐለ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ኮማንደር ወልዳይ መውጫ ፤ ባልተፈቀደው ሰልፍ የተፈጠረው ግርግር ፓሊስ በ20 ደቂቃ በማይሞላ ግዜ  እንደተቆጣጠረው መግለፃቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ መዘገቡ ይታወሳል።  

More - @tikvahethiopiaTigrigna
                          
@tikvahethiopia
#Mekelle #ኣሉላ_ኣባነጋ_ኤርፖርት

" በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም " - ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ግለሰብ

ተሳፋሪዎች የጫነ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ አውሮፕላን በመቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ከቀኑ 8:00 ሰዓት አከባቢ አደጋ እንደገጠመው ተሰምቷል።

ለአውሮፕላን ማረፍያው ቅርበት ያላቸውና ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ ግለሰብ ለመቐለ ኤፍኤም 104.4 በሰጡት ቃል ፤ አውሮፕላኑ መንሸራተት አጋጥሞት ከዋናው መንገድ መውጣቱንና በሰው ህይወት የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ተናግረዋል።

የአውሮፕላን የአደጋው መነሻ በመጣራት ላይ መሆኑም አስተያየት ሰጪው አክለው ገልፀዋል።

መረጃውን የመቐለ ኤፍ ኤምን ዋቢ በማድረግ ያደረሰን የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#Mekelle

መቐለ ከተማ  የነዳጅ እጥረት አጋጥሟታል።

ቤንዚን በጥቁር ገበያ እስከ 300 ብር በሊትር እየተሸጠ ነው። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በከተማዋ የሚገኙ ሁሉም የነዳጅ ማደያዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ እንዳልሆኑ አረጋግጧል።

በነዳጅ መጥፋት ምክንያት በተለይ የባጃጅ ትራንስፓርት ዋጋ ጨምረዋል።

ህዝቡ ለአንድ ሰው ኮንተራት ላጠረው መዳረሻ እስከ ሁለት መቶ ብር እየተጠየቀ በመሆኑ ባለፈው አስከፊ ጦርነት የነበረው ሁኔታ በማስታወስ ምሬቱ እየገለፀ ነው። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዳጅ እጥረቱ መነሻ ምን እንደሆነ ለማወቅ ያደረገው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። በዚሁ ዙሪያ የሚመለከተው  አካል የሚሰጠን አስቸኳይ የመፍትሄ ሃሳብ ካለ ተከታትለን እናቀርባለን።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር  በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ ፤ የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጠል መሆኑ ማስታወቁ ይታወሳል። 

በዚሁ መሰረት ፦

- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም 

ሆኖ በየካቲት ወር እንደሚቀጥል መዘገባችን ይታወሳል።

@tikvahethiopia            
#Mekelle

በመቐለ የታገተ የ9 ዓመት ህፃን ልጅ ለማስለቀቅ 4 ሚሊዮን ብር ቢጠየቅም ልጁ ከ1 ሳምንት እግታ በኃላ በፓሊስና ህብረተሰብ ትብብር ነፃ ሊወጣ ችሏል።

ለመሆኑ እግታው እንዴት ተፈፀመ ? 

ልጁ ሳሚኤል መሓሪ ከበደ ይበላል። ገና 9 ዓመቱ ነው። ነዋሪነቱ በዓይደር ክፍለ ከተማ ዓዲሓ ቀበሌ ነው።

ይኸው ልጅ አገር አማን ብሎ ቅዳሜና እሁድ በመንደሩ ከጓደኞቹ በመጫወትና በመቦረቅ ላይ እያለ በባጃጅ የመጡ ሰዎች አፍነው ወሰዱት።

ወላጆቹ ልጃችን ይመጣል ብለው ቢጠብቁም ብርሃን በጨለማ ተተክቶ የውሃ ሽታ ሆነባቸው።

ወደ ፓሊስ ቢያመለክቱም ፤ ወደ መንግስትና የግል የጤና ተቋማትና አብያተ ክርስትያናትም ጭምር ቢያፈላልጉ የሚወዱት ህፃን ልጃቸውን ማግኘት አልቻሉም።

ከቀናት ፍለጋ በኃላ የህፃኑ ቤተሰቦች ስልክ ተደወለላቸው።

አጋቾቹ ልጃቸው መታገቱንና እንዲለቀቅ ከተፈለገ 4 ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ ጠየቁ።

በዚህ መሀል ፓሊስ ብርቱ የክትትል እያደረገ ስለነበር ከሳምንት እልህ አስጨራሽ ፍለጋ በኃላ አጋቾቹ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል።

ህፃኑም ለህክምና ምርመራ ወደ ጤና ተቋም እንዲላክ ሆኗል።

በድርጊቱ እጃቸው አለበት የተባሉ 5 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

መረጃው የመቐለ ፓሊስ ዛሬ ለጋዜጠኛች የሰጠውን ጋዜጣዊ መግለጫ ዋቢ በማድረግ ያደረሰን የመቐለው የቲክቫህ ኢትዮጵይም ቤተሰብ አባል ነው።
                      
@tikvahethiopia