TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#መልዕክት

ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦቻችን ፤ ከዚህ ቀደም ይህ @tikvahethiopiaBOT መልዕክት መቀበያ አስቻገረ እንደሆነ መልዕክት ልከንላችሁ ነበር።

ይህ ችግር እስኪስተካከልም መልክት ለመለዋወጥ አማራጭ ይህን @OfficialTikvahethiopiaBOT እንድትጠቀሙ ገልፀንላችሁ ነበር።

አንዳንድ ቤተሰቦቻችን በ @tikvahethiopiaBOT ላይ መልዕክቶቻችን እየታዩ እና እየተመለሱ አይደለም የሚል ቅሬት አቅርበዋል ችግሩ እስኪስተካከል በ @officialtikvahethiopiaBOT ላይ መልዕክት እንድንለዋወጥ ከትልቅ ይቅርታ ጋር በድጋሚ እንገልፃለን።

ከዚህ ቀደም (ከሶስት ወር ወዲህ) ልካችሁ ያልታየም በድጋሚ መላክ ትችላላችሁ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የቤተሰቦቹ መልዕክት መለዋወጫ ነውና ከጥላቻ ንግግር፣ ከሀሰተኛ መረጃ፣ የሰዎችን እና የሀገርን ክብር ዝቅ ከሚያደርጉ መልዕክቶች ውጭ ማንኛውም ጥቆማ፣ ጠቃሚ መልዕክት ማጋራት እና መለዋወጥ ይቻላል።

#TikvahFamily

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መልዕክት

የ " መስቀል ደመራ በዓል " አከባበርን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት

- ሁከት ቀስሰቃሽ መልዕክቶችን በቲሸረሰቶች ላይም ሆነ በባነሮች ላይ በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ ይዞ መገኘት በፍፁም አይፈቀድም።

- በበዓሉ ላይ ህገ መንግስቱ የደነገገውን የኢትዮጵያን የፌዴራል ሰንደቅ ዓላማ #ወይም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የፀደቀውን የቤተክርስቲያን ዓርማን ብቻ መጠቀም ይገባል። ከዚህ ውጪ የሆነ ምንም ዓይነት አርማም ሆነ ሰንደቅ አላማ መያዝ በጥብቅ የተከለከለ ነው። የምንጠቀመው ሰንደቅ ዓላማ ሆነ የቤተክርስቲያን አርማ በግልፅ የሚታዩ በሁለቱም ፊት ዓርማዎቹ በትክክል የተቀመጡ መሆን አለባቸው።

- በቲሸርቶች ፣ በባነሮች እንዲሁም በትርኢቶች ላይ ሁሉ ሌሎች ወገኖችን የሚያስከፉ፣ መብትን የሚጋፉ ሁከት ቀስቃሽ የሆኑ ጥቅሶችን መጠቀም ከሥነ ምግባር ውጪ ከመሆኑም በላይ ለሁከትና ግርግር መፈጠር ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

- ወደ መስቀል አደባባይ በሚደረግ ጉዞ #ተደጋጋሚ ፍተሻ ይደረጋል፤ የሚደረገው ፍተሻ ለደህንነታችን ተብሎ የሚደረግ ፍተሻ መሆኑን በመገንዘብ መላው ህዝበ ክርሰቲያን ራሱን ለፍተሻ ዝግጁ ማድረግና ፍጹም በሆነ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ለፍተሻ መተባበር እንደሚገባው በመረዳት የጸጥታ አካላትን መተባበር አለበት።

- በመስቀል አደባባይ እንዲሁም ደብረ ዕንቁ ቅድስት ልደታ ማርያም ጉዳይ የሚመለከተውን አካል በሕግ አግባብ መጠየቅ የሚገባና እና በጉዳዩ ዙሪያ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ ሁሉም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ችግሩ የሚፈታበትን መንገድ ያከናውናሉ ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሱ ጥያቄዎች በዓሉ በሚከበርበት ወቅት ሊደረግ አይገባም።

- በቤተክርስቲያን ማዕከላዊ አስተዳደርና በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ተዘጋጅቶ ከሚሰራጨው መጽሔት እና ብሮሸር ውጪ ምንም ዓይነት የህትመት ውጤት ስለማይሰራጭ ከእነዚህ ውጪ የሆኑ የህትመት ውጤቶችንና በራሪ ወረቀቶችን ይዞ መገኘት በጥብቅ የተከለከለ ነው። ይዞ የተገኘም በህግ ተጠያቂ ይሆናል።

- ከመስቀል አደባባይ ውጪ በአድባራትና ገዳማት በሚከበሩ የመስቀል ደመራ በዓላት ሁሉም ህዝበ ክርስቲያን ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር እና በመረዳዳት መሥራት የሚገባ ሲሆን ሁከት ቀስቃሽ ከሆኑ መልዕክቶች በመታቀብና ህጋዊ ያልሆኑ ሰንደቅ ዓላማዎችን ባለመጠቀም የበዓሉን ሰላማዊነትና የመስቀሉን ዓላማ መሰረት ያደረጉ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባርን የተላበሱ እንቅስቃሴዎች ሊደረጉ ይገባል።

- ማንኛውም አጠራጣሪ እና ለጸጥታ ስጋት የሚሆኑ ነገሮች ሲያጋጥም በቦታው ለተመደቡ የሥነሥርዓትና የጸጥታ አስከባሪ አባላት / ለፖሊስ አካላት መጠቆም ይገባል።

(የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን)

@tikvahethiopia
#መልዕክት🕊

አገራችን የደረሰችበትን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤ/ክርስቲያን መግለጫ የተላከልን ሲሆን ቤተክርስቲያኗ ለሰላም ስምምነቱ ተፈፃሚነት ምእመናን አጥብቀው እንዲፀልዩ ጥሪ አቅርባለች።

ከተላከልን መግለጫ የተወሰደ ፦

" የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤ/ክርስቲያን በሁለቱ ወገኖች የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አጥብቃ ትደግፋለች።

የስምምነቱ መተግበር የዜጎችን ሞትና እንግልት የሚያስቀር፣ ጥላቻን ከወንድማማቾች መካከል የሚያርቅ እና በአምላክ አምሳል ለተፈጥሩ የሰው ልጆች ሰብአዊ ክብር ዋስትና የሚሰጥ በመሆኑ ለተፈጻሚነቱ የበኩሏን አስተዋጻኦ ታበረክታልች።

በመላ አገሪቷ የሚገኙ የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤ/ክርስቲያን ምዕመናንም ለሰላም ስምምነቱ ተፈጻሚነት አጥብቀው እንዲጸልዩ እና የሚጠበቅባቸውንም በጎ ምላሽ እንዲሰጡ ታሳስባለች። "

(ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#መልዕክት🕊

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በላከልን አጭር መልዕክት በመንግስት እና ህወሓት መካከል የተደረገውን የሰላም ስምምነት እንደሚያበረታታ እና በደስታ እንደተቀበለው ገልጿል።

የሰላም ስምምነቱ በሰው ልጆች ላይ የሚደርሰውን ስቃይ ለመከላከል እና ለመቀነስ እንዲሁም ለሰው ልጆች ደህንነትና ለሰላም መስፋፋት የበኩላችንን አስተዋፅኦ ከማበርከት ጋር ተያይዞ የሚሄድ ነው ብሏል።

" እንደተለመደው መላው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ቤተሰብ አቅማቸውን ለሰብአዊ ድጋፍ እና የልማት ስራዎች ለማንቀሳቀስ ተዘጋጅተዋል ። " ብሏል ማህበሩ በላከል አጭር የፅሁፍ መልዕክት

@tikvahethiopia
#መልዕክት🕊

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የፕሪቶሪያውን የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ስምምነት አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ መላው ህዝብ በጦርነቱ ሳቢያ የተጎዱ ወገኖችን ለመደገፍ እና ለዘላቂ ሰላም እንዲነሳ ጥሪ አቅርቧል።

የካውንስሉ ፀሀፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ ካስተላለፉት መልዕክት

" የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊ እንዲሆንና ሕዝባችን ከፍርሃት፣ ከጭንቀት፣ ከስድትና መከራ ያርፍ ዘንድ የሁሉንም ወገኖች ጥረት ይጠይቃል።

መላው ሕዝባችን አፍራሽ ከሆነ ተግባር በመራቅ እና ባለፉት ሁለት ዓመታት በደረሰባቸው ጉዳት ያዘኑትን ወገኖች በማጽናናት፣ ቤታቸውና ንብረታቸው የወደመባቸውን መልሶ በማቋቋም፤ የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን በመደገፍ እና በማበርታት ለዘላቂ ሰላም በአንድነት እንድንነሳ ጥሪያችን እናስተላልፋለን።

ስምምነቱ እውን እንዳይሆንና ተመልሰን ወደ ግጭት እንድንገባ የሚያደርጉ ቅስቀሳዎች ሊኖሩ ይችላሉ ፤ በልዩ ልዩ የመገናኛ ዘዴዎች የሚተላለፉ አፍራሽ መልዕክቶችን ቸል በማለት ለስምምነቱ ተግባራዊ መሆን ተግተን ልንሰራ ይገባል።

ከዚህ በተጨማሪም በጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የትግራይ፣ የአማራና የአፋር ሕዝቦች ለጋራ ሰላምና ዕድገት በይቅርታ ተቀራርበው እውተኛ እርቅ እንዲያከናውኑ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በአንድነት በመቆም መስራት ይገባል።

... የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል አቅም በፈቀደው ሁሉ ለሀገር ሰላምና ለሕዝቦችዋ ዕድገት አስፈላጊውን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኋላ አይልም። "

@tikvahethiopia
#መልዕክት

እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት ፦

- የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት፣
- የቫይታሚን ኤ ጠብታ፣
- የአንጀት ጥገኛ ትላትል መድሀኒት፣
- የህፃናት የዞረ እግር ልየታ
- የምግብ እጥረት ልየታ እንዲሁም
- ለእናቶች ከወሊድ ጋር የተያያዘ ፊስቱላ ልየታ ከትላንት ታህሳስ 13 ጀምሮ በጤና ተቋማት እና በጊዜያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።

ይኸው ዘመቻ የሚዘልቀው እስከ 22 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

በተለይ የቫይታሚን ኤ ጠብታ ህፃናት #በሽታን_የመከላከል አቅማቸው እንዲጎለብት እና በዳፍንት በሽታ በቀላሉ እንዳይጠቁ ያደርጋል።

በተቀናጀ የኩፍኝ ክትባት ወቅት እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የቫይታሚን ኤ ጠብታ ስለሚሰጥ ወላጆች በአቅራቢ ወደሚገኝ የጤና ተቋም ወይም ጊዜያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያ በመሄድ ልጃችሁን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ አድርጉ።

ውድ ቤተሰቦቻችን ይህን መልዕክት ላልሰሙት ይደርስ ዘንድ ሼር / ፎርዋርድ ያድርጉላቸው።

@tikvahethiopia
#መልዕክት

የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ፦

" የገና በዓል ሲከበር ህብረተሰቡ ከእሳትና ድንገተኛ አደጋ አጋላጭ ነገሮች ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባል።

በበዓሉ ወቅት ድንገተኛ አደጋ ቢያጋጥም በፍጥነት ለመቆጣጠር ከተለያዩ ተቋማት ጋር ቅንጅታዊ አሰራር ተዘርግቷል።

እሳትና ድንገተኛ አደጋ ቢያጋጥም በነጻ የስልክ መስመር 939 ፤ በቀጥታ የስልክ መስመሮች 011 155 53 00 ወይም በ 011 156 86 01 ደውሎ ማሳወቅ ይቻላል። "

#ENA

@tikvahethiopia
#መልዕክት

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ልደትን አስመልክተው " የእንኳን አደረሳችሁ " መልእክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸው የሀገራችንን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ አንስተው አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ቅዱስናታቸው ባስተላለፉት መልዕክት ፥ " ቸርነቱ የማያልቅበት እግዚአብሔር አምላክ በአሁኑ ጊዜ #በሀገራችን የተከሠተው ችግር በከፊልም ቢሆን ረገብ ብሎ የሰላም ጭላንጭል እንድናይ አድርጎናል " ያሉ ሲሆን " ይህ ሰላም የእግዚአብሔር ስጦታ ነውና #ልንወደው #ልናከብረውና #ልንጠብቀው ይገባል " ብለዋል።

" ሰላም በጠፋ ጊዜ በወገኖቻችን ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰ በዓይናችን አይተናል። " ያሉት ቅዱስነታቸው " ይህ ዓይነቱ ክሥተት ሊቆም እንጂ ሊቀጥል አይገባም " ሲሉ አስገንዝበዋል።

የተገኘው የሰላም ጭላንጭል ወደ ፍጹም አስተማማኝ ደረጃ በሙሉነት እንዲያድግ ሁሉም በኃላፊነት እንዲሰራ በአጽንዖት አደራ ብለዋል።

በተከሠተው አለመግባባት በአጠቃላይ በሕዝብ ላይ የደረሰው ስብራት ከባድ በመሆኑ የዓለም ማኅበረሰብ የተቻለውን ድጋፍ ሁሉ በማድረግ ሕዝባችንን እንዲያግዝ  መንግሥትና ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች የተጀመረውን የሰላም ጉዞ እንዳይቀለበስ በከፍተኛ ኃላፊነት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ቅዱስነታቸው ፤ " ኢትዮጵያውያን የሆናችሁ ልጆቻችን በተለመደው የመተጋገዝ ቅዱስ ባህላችን መሠረት እርስ በርስ #በመረዳዳት ይህንን ፈተና እንድናልፈው በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን ከአደራ ጋር እናስተላልፋለን። " ብለዋል።

(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያያዟል)

@tikvahethiopia
#መልዕክት

የጥምቀት በዓል የቤተክርስቲያኒቱን ክብር በጠበቀ መልክና በሰላም እንዲከወን ኮሚቴዎች ተዋቅረው እየሰሩ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አሳውቃለች።

የጥምቀት በዓል የቤተክርስቲያኒቱ መገለጫና ትልቅ በዓል በመሆኑ በዓሉን ለማስፈፀም በተለያየ ዘርፍ የተቋቋሙ የበዓሉን መርሐ ግብር በተሟላ ሁኔታ የሚያግዙ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ስራቸውን እየሰሩ ይገኛሉ።

ቤተክርስቲያኗ፤በዓሉ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የዓለም ህዝብም የሚያደንቀው የቤተክርስቲያን በዓል ነው ብላለች።

ከበዓሉ ላይ በተያያዘ ሊደረጉ የማይገባቸው ጉዳዮች ተነስተው መልዕክት ተላልፏል። ይህም በዋናነት የባንዲራና የአለባበስ ሥነ ሥርዓትን የሚመለከት ነው።

አለባበስን በተመለከተ ካህናት የቤተክርስቲያኒቱን ሥርዓት በጠበቀ መልኩ መልበስ እንዳለባቸው ተገልጿል።

ምዕመናንም እንደተለመደው #ነጭ_ልብስ ለብሰው መገኘት እንዳለባቸው መልዕክት ተላልፏል።

በተጨማሪ በዓሉን ላይ የሚያዙ ጥቅሶች የሚያስማሙ እንጂ የሚያጋጩ ሊሆኑ እንደማይገባቸው ቤተክርስቲያን መልዕክቷን አስተላልፋለች።

ባንዲራን አስመልክቶ ምዕመናን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያጸደቀችው የቤተክርስቲያኒቱ አርማ ያለበትን ባንዲራ እና የፌዴራል መንግስቱን ባንዲራን መያዝ እንደሚችሉ ከዚያ ውጪ ግን ይዞ መውጣት እንዳልተፈቀደ አስገንዝባለች።

በተጨማሪ ምዕመናን የሚመጡት በዓሉን ለማክበር እንደመሆኑ በዓሉን የጸብና የመታገያ መድረክ ሊያደርጉት እንደማይገባ ማሳስቢያ ተላልፏል።

"ማንም የፖለቲካ ሀሳቡን በቤቱ  እንጂ የእምነት ማስፈጸሚያ ቦታ ላይ ሊተገብረው አይገባም፤ እንዲህ ያለ ድርጊት በእግዚአብሔርም በሰውም ዘንድ ያስወግዛልም፤ የፖለቲካ ሀሳባቸውን ለማስፈጸሚያ የሚጠቀሙ የቤተክርስቲያኒቱ ጠላቶች ናቸውም " ተብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መልዕክት

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩወርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፦

" ታቦታትን ይዘን ስንጓዝ ጣራ የለውም እንጂ #ቤተክርስቲያንን ይዘን እንደምንጓዝ ነው የሚቆጠረው ፤ ስለሆነም ታቦታትን ስናጅብ በዚህ ልክ ተረድተን #በትህትና እና #በሥርዓት መጓዝ ይኖርብናል። "

(የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት)

@tikvahethiopia
#መልዕክት

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2016 ዓ/ም የመስቀል ደመራ በዓልን አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው መካከል የተወሰደ ፦

" እባካችሁ ንስሐ ገብተን በመስቀሉ ቃል ተቀራርበንና ተስማምተን ይቅር ተባብለን በአንድነት በእኩልነት በሰላምና በፍቅር እንኑር።

በምድራችን ፍትሕ ርትዕ ይንገሥ፥ ሰብአዊ መብት ይከበር፥ የተበደለ ይካስ ፥ እግዚአብሔር ይደመጥ መስቀል ማክበር ማለት ይህ ነው፡፡

ይህ ሲሆን ሀገር በመንፈሳዊና በቊሳዊ በረከት ትባረካለች፤ ትለማለችም፤ ታድግማለች፤ እግዚአብሔርም በተግባሩ ወይም በፍጥረቱ ይደሰታል፡፡ "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

Grap. Tikvah Family

@tikvahethiopia
#መልዕክት

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፦

" . . . ሃይማኖትና ፈሪሐ እግዚአብሔር ከሌለ ፍትሕ ይጐድላል፣ ፍትሕ ከጐደለ ብሶት ይፈጠራል፣ ብሶት ካለ ሰላም ሊኖር አይችልም።

በሁሉም የዓለማችን ክፍል ሃይማኖትና ፈሪሐ እግዚብሔር እየተዘነጋ በመሄዱ ቀውሱ ተባብሶ ይታያል፤ የሰው ልጅ ኑሮ በየትም ይሁን በየት በስጋት የተሞላ ሆኖአል፤ የሚወራው ሁሉ ስለ ግጭት ስለአየር ብክለት ስለ ረኃብና እልቂት ሆኖአል።

ዓለም የጉልበተኞችና የባለ ሀብቶች ብቻ እንድትሆን የተፈጠረች እስክትመስል ድረስ ከባድ የፍትሕ መዛባት አጋጥሞአታል፤ የዝቅተኛው ማኅበረ ሰብ ሰብአዊ መብት ተዘንግቶአል፤ ከዚህ አኳያ ዓለም በዚህ እስከ ቀጠለች ድረስ ሰላም የማግኘቷ ዕድል በጣም አጠራጣሪ ነው።

የክርስቶስ ልደት ያስተማረን ግን እንደዚህ አልነበረም፤ ጌታችን የተወለደው በተዋበና ምቹ በሆነ የሀብታም ቤት ሳይሆን #በከብቶች_በረት ነበረ፤ የተገለጠውም ለባለሥልጣኖች ሳይሆን ዝቅተኞች ለሚባሉ እረኞች ነበረ፤ ልዑላኑ ሰማያውያንና ትሑታኑ ምድራውያን በአንድነት አገናኝቶ ስለ #ሰላም በጋራ እንዲዘምሩ አደረገ፤ አሳዳጅ ሳይሆን ተሳዳጅ ሆኖ በግብጽ አገር በመንከራተት አደገ፤ ይህን ሁሉ ያደረገው እኛ እሱን እያየን እንደ ሰንደቅ ዓላማ እንድንከተለው ነበር።

ጌታችን ከባለሥልጣናቱና ከባለሀብቶቹ ይልቅ በድሆቹ ደረጃ የተወለደው ለድሆቹና ለዝቅተኞቹ ትኩረት እንድንሰጥ ለማስተማር ነው። የእኛ ድርጊት ግን #ግልባጩ ሆኖ እየተስተዋለ ነው፡፡

እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ ክርስቲያን ነኝ ብሎ፣ በስመ እግዚአብሔር ተሰይሞ፣ መስቀልን በአንገቱ ተሸክሞ የእሱ መሰል በሆነው ወይም መስቀል በተሸከመው ወንድሙ እና እኅቱ እንዲሁም በመሰል ፍጡር ላይ ያለ ርኅራኄ ሲጨክን መታየቱ ነው፤ እንዲህ እየሆነ እንዴት ሰላም ይምጣ? እግዚአብሔርስ እንዴት በረከቱ ይሰጣል? ይህ እጅግ በጣም ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን  ምእመናንና ምእመናት!

እኛ ኢትዮጵያውያን ከእንዲህ ዓይነቱ የሃይማኖትና የሞራል ዝቅጠት በአስቸኳይ መውጣት አለብን፤ ጠቡ፣ መለያየቱ፣ መጨካከኑ፣ ለኔ ለኔ መባባሉ ከረምንበት፤ ሆኖም ያመጣልን ነገር ቢኖር ሁለንተና ውድመት ብቻ ነው። ያስገኘልን ትርፍ ይህ መሆኑ እያወቅን በዚሁ ልንቀጥል አይገባም።

ሰው ችግሩን በልቡ እያወቀ በዓይኑ እያየ እንዴት ገደል ውስጥ ይገባል ? ዕርቅና ይቅርታ ማንን ጐዳ ? ሰላምና አንድነት ማንን አከሰረ ? ሰበብ አስባብ እየተፈለገ በሆነውም ባልሆነውም ከመተላለቅ ለምን ኢትዮጵያ የሁላችን ናት ብለን በእኩልነትና በስምምነት መኖር አቃተን ?  ሦስት ሺሕ ዘመናት አብረው የኖሩ ሕዝቦች እንዴት ችግራቸውን በጠባይና በብልሐት ማስወገድ አቃታቸው ? ይህ ከቶ ሊሆን አይገባም።

ሁላችንም ሰከን ብለን እናስብ፤ ለሁሉም የማሰቢያና የመመካከሪያ ጊዜ ፈጥረን ችግሩን በስፍሐ አእምሮ እንፍታው፤ችግርን በምክክርና በይቅርታ መፍታት አማራጭ የሌለው ጥበብ ነው። የሃይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራንና ልኂቃን በዚህ ተግተን ልንሰራ ይገባል፤ መንግሥትና የፓለቲካ ፓርቲዎችም ለዚህ የበኩላቸውን ድጋፍ ያድርጉ፤ በዚህም ሰላማችንን እንመልስ፡፡ "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#መልዕክት

ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነየሱስ ሱራፌል የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳሳት ፦

" . . . የክርስቶስን መወለድ በአግባቡ ለማክበር ለሰው ልጆች ሕይወት፣ ለእግዚአብሔር ቤተክርስቲያንና ለእርሱ ቅዱስ ስፍራዎች ክብርን እንስጥ፡፡

ከራስ ወዳድነት መንፈስ እንውጣ በመላው አገራችን #ሞት_ይብቃ#ሰላም_ይስፋፋ፡፡

የተራቡ ፣ የተጠሙ ፣ የታረዙ ፣ የተበደሉ፣ የታመሙና የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን እናስታውስ፡፡

ከጎናቸው እንሁን እንርዳቸው እናጽናናቸው፡፡ ለኛ ምን ይደረግልን ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ምን እናድርግ እንበል፤ መጠጊያ ለሌላቸው መሸሸጊያ እንሁንላቸው፡፡

የሚገለሉ ባይተዋርነት እንዳይሰማቸው እናድርግ፡፡  ዘመዳቸው እንሁን፡፡ ምክንያቱም የልደት በዓል ክርስቶስ ዘመዳችን እንደሆነ የሚያበሥረን በዓል ነውና፡፡

በልደት ምስጢር ማንም እንግዳ ሊሆን አይገባውም፡፡

እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ ጠንካራ ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡ በግብጽ ባርነት ሳላችሁ በመገለል፣ በመማረር ኖራችኋል፡፡ ስለሆነም እንግዳ እንዳታማርሩ ይላል፡፡ ይህ ትልቅ የፈጣሪ ትዕዛዝ ነው፡፡ ሁላችንም ልናቀርበው የሚገባው ጥያቄ የሚከተለው ነው፡፡

‹‹እንግዳ አባርሬ ይሆን››? እንግዳን ከሚያዋርድ ሐሳብ፣ ትምህርት፣ መልዕክት ጋር ተባብሬ ይሆን? የእኔ ባሕል ሙሉ ስለሆነ ሌላውን መጫን፣ ማግለል አለብኝ ብዬ ይሆን ? ይህ ዓይነት ሐሳብ ከእግዚአብሔር ቃል እንደሚርቅ ተረድቼ ይሆን? ከእንደዚህ ዓይነት ሐሳብ ለመውጣትስ ምን ማድረግ ይገባኛል ልበል፡፡ 

ከዚህ ሐሳብና ይህ ዓይነት ሐሳብ ከሚገለጥባቸው ተግባራት ነፃ መውጣት የምንችለው ወደ ገና በዓልና ወደ ትንሣኤ ምስጢር ስንቀርብ ነው፡፡ በዚያን ጊዜ ሰማይና ምድር ከእኛ ጋር አብረው ለታላቁ ጌታ ታላቅ የምስጋና መዝሙር ይዘምራሉ፡፡ "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#መልዕክት

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዜዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ፦

" . . . በዓለማችን #የሰላም ጉዳይ እጅግ አሳሳቢ በሆነበት በአሁኑ ጊዜ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ስናከብር እግዚአብሔር በራሱና በሰው ልጆች መካከል፤ እንዲሁም በሰው ልጆች መካከል የነበረውን ጥል አስወግዶ ሰላምን ለማውረድ ያደረገውን ማሰብ ብቻ ሳይሆን የክርስቶስን ምሳሌነት ለመከተል መወሰንን ይጨምራል፡፡

በተለይም በአሁኑ ጊዜ  በአገራችን የሚታዩት ግጭቶችና አለመረጋጋቶች ተወግደው ሰላም እንዲሰፍንና አገራዊ አንድነት እንዲረጋገጥ መላው የአገራችን ሕዝቦችና ሕዝበ ምዕመኑ እንደወትሮው የእግዚአብሔር አምላካችንን ጣልቃ ገብነት ተግተው መለመንና አቅም የፈቀደውን ሁሉ ለማድረግ መዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል፡፡  

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በአገራችን በተለያዩ ቦታዎች ለሚነሱ  አዳዲስ ግጭቶችም ሆነ ለሰነበቱት አለመግባባቶች ዋነኛ መፍትሔ ሊሆን የሚችለው #በሰላማዊ_መንገድ  ተቀራርቦ መመካከርና መነጋገር ብቻ እንደሆነና የትጥቅ ፍልሚያ ሰላም ሊያመጣ እንደማይችል ታምናለች፡፡

የሰው ልጆች አብረው በሰላምና በፍቅር እንዲኖሩ የሰላም ወንጌልን ትሰብካለች፡፡ ከሰላም እጦት የተነሳ የሚፈጠረውን ሞትና እንግልት ትቃወማለች፤ በበኩልዋም ችግሮች ሲፈጠሩ ለእርቅና ለሰላም ጥረቶች የምትጠየቀውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆንዋንም በየጊዜው ስትገልጽ  ቆይታለች፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱም ራስዋ በየጊዜው በተለያዩ ታጣቂ ኃይላት መካከል በሚከሰቱ ግጭቶች ቀጥታ ተጠቂ የሆነችባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው፡፡

ለዚህም በቅርብ ጊዜ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በቄለም ወለጋ ዞን በጊዳሚ ወረዳ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በጸሎት ላይ በነበሩ ንጹሐን ምዕመናኖቻችን ላይ  የደረሰው የጅምላ ግድያ በማሳያነት ሊጠቀስ የሚችል ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱ በጊዜው ድርጊቱን ከመቃወምና ከማውገዝ ባሻገር ሁኔታውን አስመልክቶ ክትትል እንዲደረግና ለህዝብ ይፋ እንዲሆን ጥሪ ማድረግዋ የሚታወስ ነው፡፡

አያይዛም እንዲህ ዓይነቱን ድርጊት ላንዴና ለመጨረሻ ለማስወገድ የትጥቅ ፊልሚያዎችን አቁሞ ለሰላማዊ ምክክር ዕድል መስጠት ብቸኛ አማራጭ እንደሆነም አስታውሳለች፡፡

አሁንም ይህንኑ ጥሪ ደግማ ደጋግማ ማሰማትዋን ትቀጥላለች፤ ምዕመናንዋንም በዚሁ መስመር በጸሎት በማትጋት ላይ ትገኛለች፡፡ በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥም፤ እርሱ የምህረት ፊቱን ይመልስልናል፤ ሰላሙንም በእርግጥ ይሰጠናል፡፡ "

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል ! " - ቋሚ ሲኖዶስ ቋሚ ሲኖዶስ ፥ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም አወጀ። በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን ፣ ምሕላ ይታወጃል። ምሕላ የሚታወጀው ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ…
🔈#መልዕክት

" ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና ምእመናን ሀገራዊ ፦
- ሰላምን፣ 
- መረጋጋትን
- ፍቅርን
- አንድነትን ለማስፈን ጾም እና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ " - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ


#ኢትዮጵያ🙏

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM