#መልዕክት

እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት ፦

- የኩፍኝ በሽታ መከላከያ ክትባት፣
- የቫይታሚን ኤ ጠብታ፣
- የአንጀት ጥገኛ ትላትል መድሀኒት፣
- የህፃናት የዞረ እግር ልየታ
- የምግብ እጥረት ልየታ እንዲሁም
- ለእናቶች ከወሊድ ጋር የተያያዘ ፊስቱላ ልየታ ከትላንት ታህሳስ 13 ጀምሮ በጤና ተቋማት እና በጊዜያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።

ይኸው ዘመቻ የሚዘልቀው እስከ 22 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

በተለይ የቫይታሚን ኤ ጠብታ ህፃናት #በሽታን_የመከላከል አቅማቸው እንዲጎለብት እና በዳፍንት በሽታ በቀላሉ እንዳይጠቁ ያደርጋል።

በተቀናጀ የኩፍኝ ክትባት ወቅት እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ህፃናት የቫይታሚን ኤ ጠብታ ስለሚሰጥ ወላጆች በአቅራቢ ወደሚገኝ የጤና ተቋም ወይም ጊዜያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያ በመሄድ ልጃችሁን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ አድርጉ።

ውድ ቤተሰቦቻችን ይህን መልዕክት ላልሰሙት ይደርስ ዘንድ ሼር / ፎርዋርድ ያድርጉላቸው።

@tikvahethiopia