TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ukraine #Russia

ሩሲያ የዩክሬንን የአየር ክልል ለመዝጋት ከሚሞክር ኃይል ጋር ጦርነት እንደምትከፍት ገለፀች።

ሀገሪቱ ይህን የገለፀችው በዩክሬን እያካሄድኩ ነው ያለችውን “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” የመጀመሪያውን ምዕራፍ ማጠናቀቋን ባሳወቀችበት ወቅት ነው።

ሀገሪቱ ተጠናቋል ባለችው የመጀመሪያ ምዕራፍ ያስቀመጠችው ግቦች እንደተሳኩ የገለጸች ሲሆን ብዙ የዩክሬን ግዛቶችን መቆጣጠሯን አሳውቃለች።

ሩስያ ጦሯ የዩክሬንን ዋና ከተማ ኪቭን ጨምሮ ካርኪቭ፣ ቼርኒሂቭመ ሱሚ እና ሚኮላይቭ የተባሉ አካባቢዎችን መክበቡን ገልፃለች። በተጨማሪ ኬርሶን እና ዛፖሮዚ የተባሉ የዩክሬን ግዛቶች አሁን ላይ በእጇ ላይ መውደቁን አሳውቃለች።

በዩክሬን የተገንጣዮች ግዛት የሆነችውን ሉሃንስክን ደግሞ 93 በመቶ መቆጣጠሯን አሳውቃለች።

የዩክሬንን የአየር ክልል ለመዝጋት ከሚሞክር ኃይል ጋር ጦርነት እንደምትከፍትም ዝታለች።

4 ሳምንታት ባስቆጠረው የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ምክንያት ቁጥራቸው በውል የማይታወቁ ሰዎች ሲያልቁ ከ3 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዋል።

መረጃው የአልዓይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia
#Ukraine #Russia

የሩስያን ድንበር ጥሰው ገቡ የተባሉ ሁለት የዩክሬን ጦር ሂሊኮፕተሮች የነዳጅ ማከማቻ ላይ ጥቃት መፈፀማቸው ተሰማ።

ሁለት የዩክሬን ሄሊኮፕተሮች የሩሲያን ድንበር ጥሰው በሀገሪቱ ምዕራባዊ ከተማ ቤልጎሮድ የነዳጅ ማከማቻ ቦታ ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን የአከባቢው አስተዳዳር ዛሬ አስታውቋል።

የአካባቢው አስተዳዳሪ የሆኑት ቫያቼስላቭ ግላድኮቭ በቴሌግራም ቻናላቸው ላይ ሁለት የዩክሬን ጦር ሄሊኮፕተሮች በፈፀሙት የአየር ጥቃት በሚያስተዳድሩት አካባቢ ባለ የነዳጅ ማከማቻ ላይ የእሳት ቃጠሎ መነሳቱን ጽፈዋል።

በቃጠሎው ምክንያት በነዳጅ ማከማቻው ውስጥ የነበሩ ሁለት ሰራተኞች መቁሰላቸው ተገልጿል።

የዩክሬን እና ሩስያ ጦርነት ከተጀመረበት ጊዜ አብስቶ ሩስያ ፤ ዩክሬን ድንበሯን አልፋ ጥቃት ፈፀመችብኝ ብላ ሪፖርት ስታደርግ ይህ የመጀመሪያ ነው።

የ2ቱ ሀገራት ጦርነት እስካሁን ድረስ ይህን ነው የሚባል መፍትሄ ሳይገኝለት ከወር በላይ ተቆጥሯል።

አሁንም ጦርነቱ እንዲቆም ለማድረግ ንግግሮች ቢኖሩም ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ ግጭት እንዲቀጥል የሚያደርጉ ወታደራዊ ሁኔታዎች እንደሚስተዋሉ እየተነገረ ነው።

በሀገራቱ ጦርነት ምክንያት ከሚጠፋው የሰው ህይወት ፣ ከሚሰደደው ሰው ባለፈ በዓለም ኢኮኖሚ እና በሀገራት የኑሮ ውድነት ላይ በየዕለቱ እያሳደረ ያለው ግልፅ ተፅእኖ እየከፋ ነው።

@tikvahethiopia
#Russia

ሩስያ ወደ ውጭ በሚላክ ስንዴ፣ በቆሎ እና ገብስ ላይ የታክስ ጭማሪ አደረገች።

የሩሲያ መንግስት ወደ ውጭ በሚላከው ስንዴ ፣ በቆሎ እና ገብስ ላይ የታክስ ጭማሪ ማደረጉን የሀገሪቱ ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ፤ ከሀገሪቱ ወደ ውጭ በሚላክ ስንዴ ላይ የተደረገው የታክስ ጭማሪ በዚህ ሳምንት ተግባራዊ ይደረጋል ብሏል፡፡

በዚህም መሰረት አንድ ቶን ስንዴ ወደ ውጭ ሲላክ 101 ነጥብ 4 ዶላር እንዲከፈል መንግስት ወስኗል።

በተጨማሪም ወደ ውጭ ሀገራት የሚላኩ የበቆሎ እና ገብስ ምርት ላይ በተደረገድ የታክስ ጭማሪ አንድ ቶን በቆሎ ወደ ውጭ ሲላክ የሚከፈለው ታክስ 70 ነጥብ 6 እንዲሂም አንድ ቶን ገብስ ወደ ውጭ ሲላክ 75 ነጥብ 4 ዶላር እንዲሆን ውሳኔ ተላልፏል።

በስንዴ፣ ገብስና በቆሎ ላይ የተደረገው የታክስ ጭማሪ በምርቶቹም ላይ የዋጋ ጭማሪ እንደሚያመጣ አመላካች ነውም ተብሏል።

በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ሳቢያ በስንዴ ምርት ላይ ከፍተኛ እጥረት አሊያም የዋጋ ጭማሪ ሊከሰት እንደሚችል ፍርሃቶች መኖራቸው እየተገለፀ መሆኑን አል ዓይን ኒውስ (Al AIN) ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#Russia

የሩሲያው ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሀገራቸውን ሩስያን ለማግለል የሚደረገው ሙከራ አይሳካም ሲሉ ምእራባውያንን አስጠነቀቁ።

ሩስያ በዩክሬን የጀመረችውን " ልዩ ወታራዊ ዘመቻ " ተከትሎ ጠንከር ያሉ ማዕቀቦችን በጣሉባት ምእራባውያን እና አሜሪካ ላይ እምነት እንደማይኖራት ገልጻለች፡፡

ፕሬዜዳንት ፑቲን ፥ " በሶቬት ህብረት ጊዜ ጠቅላላ ማእቀብ ተጥሎ ነበር፤ ሙሉ በሙሉ ተገልላም ነበር፤ ነገርግን ሶቬት አሁንም በስፔስ ቀዳሚ ነች " ሲሉ ተደምጠዋል።

ፕሬዝደንቱ የመገለል ፍላጎት እንደሌላቸው እና በዚህ ዘመናዊ አለም ማግለል እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡

በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት ሩሲያ በዩሪ ጋጋሪ አማካኝነት ወደ ስፔስ ያደረገችው በረራ እና በፈረንጆቹ 1957 የስፑትኒክ አንደኛ ወደ ስፔስ መብረር አሜሪካን አስደንግጦ ነበር፡፡ በወቅቱ አሜሪካ ከሩሲያ ጋር ለመወዳደር ስትል ናሳን አቋቁማ ነበር፡፡

ፕሬዜዳንት ፑቲን በዩክሬን " ወታደራዊ ዘመቻ " ለማድረግ የተገደዱት፤ አሜሪካ ዩክሬንን እና ኔቶን በመጠቀም ለማስፈራራት ስለሞከረች እና ይህንም መከላከል ሲለሚገባ ነው ብለዋል፡፡

ፑቲን ሩሲያ በዩክሬን ሁሉንም የምትፈልገውን አላማ ታሳካለች ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሩስያ ፥ ስዊድንን እና ፊንላንድን አስጠነቀቀች። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስዊድን እና ፊንላንድ NATOን ለመቀላቀል ከሞከሩ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ] እንደሚኖሩ አስጠንቅቋል። አሁን በዩክሬን እና ሩስያ መካከል ያለው ጦርነት ተባብሶ በቀጠለበት ሁኔታ ሩስያ ፊንላንድ እና ስዊድንን ማስፈራራቷ ሌላ ዓለም አቀፋዊ ስጋት ፈጥሯል። የኃያላን ሀገራቱ ግብግብ በተለይ…
#Russia #Finland #Sewden

ሩስያ NATOን ለመቀላቀል ከሞከራችሁ እጅግ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ] ይኖራል ስትል ካስጠነቀቀቻቸው ስውዲን እና ፊንላንድ መካከል ስውዲን NATOን ለመቀላቀል ለማመልከት መወሰኗ ተሰምቷል።

የስዊዲን ጠ/ሚ ማግዳሌና አንደርሰን ሀገራቸው በሰኔ ወር መጨረሻ ላይ ለNATO ጥምረት አባልነት ለማመልከት መወሰኗን ገልፀዋል።

ፊንላንድ በበኩሏ ፤ አሁን ይኽ ነው የሚባል ውሳኔ ላይ ባትደርስም በሚቀጠሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ NATOን ለመቀላቀል የማመልከት ውሳኔ ላይ እደርሳለሁ ብላለች።

የፊንላንድ ጠ/ሚ ሳንና ማሪን እና የስዊድን ጠ/ሚ ማግዳሌና አንደርሰን በአካባቢው የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ዛሬ በስቶክሆልም ተገናኝተው ተወያይተዋል።

በሩስያ እና ዩክሬን መካከል ያለው ጦርነት አሁንም መፍትሄ የላገኘ ሲሆን ሩስያ ዩክሬን ላይ እርምጃ መውሰድ ከጀመረችባቸው ዋነኛ ምክንያቶች አንዱ NATOን ለመቀላቀል ሙከራ ማድረጓና ለደህንነቷ ስጋትን በመደቀኗ መሆኑ ይታወቃል።

የዩክሬን ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኃላ ሩስያ ፤ ስውዲን እና ፊንላድ እንዲህ ያለውን ነገር እንዳይሞክሩት ፤ የሚያደርጉት ከሆነ ግን ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጎጂ ውጤቶች እንደሚኖሩ አስጠንቅቃቸው ነበር።

አሁን ላይ ስውዲን NATOን ለመቀላቀል ጥያቄ እንደምታቀርብ መወሰኗ ፤ ፊንላንድም በቀጣይ ሳምንታት ውሳኔ ላይ ደርሳለሁ ማለቷ ትልቅ ስጋትን ፈጥሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UNGA በአሜሪካ አነሳሽነት 193 አባል ሀገራት ላሉት የተመድ ጠቅላለ ጉባኤ የቀረበው ሩስያን ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ም/ቤት የማገድ የውሳኔ ሀሳብ በአብላጫ ድምፅ ዛሬ ፀድቋል። የውሳኔ ሃሳቡን ከ193 አባልት 93 ሀገራት የደገፉት ሲሆን 58 ሀገራት ድምጸ ተአቅቦ አድርገዋል፤ 24 ሀገራት ደግሞ ተቃውመዋል። በዚህም በአብላጫ ድምጽ ሩሲያን ከሰብአዊ መብቶች ም/ቤት ታግዳለች። የውሳኔ ሃሳቡ ለጉባኤው…
#RUSSIA #ETHIOPIA

ሀገራችን #ኢትዮጵያ በቅርቡ በተደረገው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ሩስያ ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ም/ ቤት እንድትታገድ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ለምን የተቃውሞ ድምፅ ሰጠች ?

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ሲመልሱ ፦

" ...እኛ ሀገሮችን በማግለል፤ እንደ UN ካሉት ዓለም አቀፍ ተቋም በማስወጣት ጥቅም አይመጣም ሰላምም በእንዲህ አይነት አይመጣም ከሚል የመነጨ ነው በዋናነት።

አሁንም ቢሆን ይሄ ነገር በሰላም እንዲዘጋ እንደምንፈልግ ገልፀናል። በሰላማዊ መንገድ ፤ በሰላማዊ ሂደት ይሄ ነገር እንዲቆም ነው እንጂ #አንድን_ወገን_ለይቶ_በማግለል ሊመጣ የሚችል ሰላም የለም ከሚል የመነጨ አቋም ነው።

ከተባለው ሀገር (ሩስያ) ጋርም ያለን ግንኙነት በጣም ጠንካራ ስለሆነ ነው። እንደሚታወቀው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት መድረክ የሰጡን ድጋፍ የሚታወስ ነው። " ብለዋል።

ከጥቂት ቀናት በፊት 193 አባል ሀገራት ላሉት የተመድ ጠቅላለ ጉባኤ የቀረበው ሩስያን ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ም/ቤት የማገድ የውሳኔ ሀሳብ በአብላጫ ድምፅ መፅደቁ ፤ ሩስያም ከም/ቤቱ መታገዷ ይታወሳል።

በወቅቱ የውሳኔ ሃሳቡን ከ193 አባልት 93 ሀገራት የደገፉት ሲሆን 58 ሀገራት ድምጸ ተአቅቦ አድርገዋል፤ 24 ሀገራት ደግሞ ተቃውመዋል፤ ከተቃወሙት 24 ሀገራት አንዷ ሀገራችን ኢትዮጵያ ናት።

@tikvahethiopia
#Russia #Ukraine

ሰሞኑን አዲስ አበባ በሚገኘው የሩሲያ ኤምባሲ በር ላይ በርካታ " ኢትዮጵያዊያን ሩሲያን ወግነው ዩክሬንን ለመውጋት " ለመመዝገብ ወረፋ በመጠባበቅ ላይ ናቸው የሚል ምስል ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት እየተሰራጨ ነው።

ኢትዮጵያውያኑ በእጃቸው ላይ ዶክመት ይዘው ተሰልፈው ይታያል።

የሩስያ ኤምባሲ ፕረስ አታቼ የሆኑት ማሪያ ቸርኑኪና ለአል ዐይን በሰጡት ቃል ፤ " ሩሲያ ለዩክሬን ጦርነት ኢትዮጵያዊያንን ለመቅጠር ማስታወቂያ አላወጣችም፣ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው መረጃም ሀሰተኛ ነው " ሲሉ መልሰዋል።

ነገር ግን ኢትዮጵያውን ወደ ኢምባሲው መሄዳቸው እውነት መሆኑን ገልፀዋል።

ኢትዮጵያውያን ወደ ሩሲያ ኢምባሲ የሄዱት ለምልመላ ሳይሆን ለሩሲያ ያላቸውን አጋርነት ለማሳየት መሆኑን ነው የገለፁት።

ይሁንና ሩሲያ ከዩክሬን ጋር እያደረገችው ባለው ጦርነት " በርካታ ኢትዮጵያዊያን በኢሜይል እና በአካል ከሩሲያ ጎን መሆናቸውን እያሳወቁን ነው ለዚህ እናመሰግናለን " ሲሉም አክለዋል።

ኢትዮጵያዊያን ይሄንን እያደረጉ ያለው ረጅም እና ታሪካዊ በሆነው የኢትዮጵያ እና ሩሲያ ወዳጅነት ላይ ስለሚተማመኑ እንደሆነ ኤምባሲው ተገልጿል።

የዩክሬን ኤምባሲ ደግሞ ሩስያ ምልመላ እያደረገች ነው በሚል የተሰራጨውን መረጃ በተመለከተ ለኢትዮጵያ ቼክ መረጃ ማጣሪያ ድረገፅ በሰጠው ቃል ፤ "ይህ አሳዛኝ ድርጊት ነው። አንድ ኢትዮጵያዊ በዚህ ጦርነት ህይወቱ ቢያልፍ ለዩክሬንም ሆነ ለኢትዮጵያ አሳዛኝ ክስተት ይሆናል። " ብሏል።

መረጃው የአል ዓይን ኒውስ እና የኢትዮጵያ ቼክ የመረጀ ማጣሪያ ድረገፅ ነው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Russia

ሩስያ ተጨማሪ አሜሪካውያንን ' ወደ ሀገሬ ድርሽ እንዳይሉ ስትል " እገዳ ጣለች።

ሩስያ በዛሬው ዕለት የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስ፣ የፌስቡክ (Facebook) መስራች ማርክ ዙከርበርግን ጨምሮ 29 የአሜሪካ ባለስልጣናት ፣ የንግድ ሰዎች እና ጋዜጠኞች ወደ ሀገሯ እንዳይደርሱ እገዳ ጥላባቸዋለች።

በሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይፋ በተደረገው የማዕቀብ ዝርዝር ከምክትል ፕሬዜዳንት ካማላ ሃሪስ እና ከፌስቡክ መስራች ማርክ ዙከርበርግ በተጨማሪ ምክትል የመከላከያ ሚኒስትር ካትሊን ሂክስ እና የፔንታጎን ቃል አቀባይ ጆን ኪርቢ ይገኙበታል።

ሚኒስቴሩ ይፋ ባደረገው ዝርዝር ላይ ፤ " እነዚህ ግለሰቦች ላልተወሰነ ጊዜ ወደ ሩሲያ ፌዴሬሽን እንዳይገቡ ተከልክለዋል " ብሏል።

@tikvahethiopia
#EU #RUSSIA

የአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት በሩስያ የነዳጅ ግብይት ላይ ማዕቀብ ጣሉ።

27ቱ አውሮጳ ህብረት አባል ሃገራት በሩስያ የነዳጅ ግብይት ላይ ማዕቀብ መጣላቸውን ይፋ አድርገዋል።

አባልሃገራቱ በግዙፉ የሩስያ ባንክ ስቤር ባንክንም ከዓለማቀፉ የባንኮች የክፍያ ስረዓት ወይም ስዊፍት ማስወጣታቸውን አስታውቀዋል።

በስምምነቱ መሰረት ወደ አውሮፓ የሚገባው የሩስያ ነዳጅ ሁለት ሶስተኛው እንደሚታቀብ የህብረቱ ፕሬዚደንት ቻርለስ ሚሸል ተናግረዋል።

ማዕቀቡ " የሩስያ የፋይናንስ ምንጭ በከፍተኛ ደረጃ በማንኮታኮት " ሩስያ በዩክሬን ላይ የከፈተችውን ጦርነት ገትታ ከሀገሪቱ ለቃ እንድትወጣ ያስገድዳታል " ሲሉ ፕሬዚደንቱ ተናግረዋል።

የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልስም " ስምምነቱ የጋራችን ነው " ብለዋል። ነገር ግን ከሃያ ሰባቱ ሃገራት መካከል ፦
➡️ ሃንጋሪ ፣
➡️ ስሎቫኪያ ፣
➡️ ቼክ ሪፐብሊክ እና ቡልጋሪያ ከሩስያ ነዳጅ ማስገባት #እንደማያቋርጡ አስታውቀዋል።

ይህንኑ በተመለከተ የሃንጋሪው ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን የነዳጅ ማዕቀቡ የህብረቱ አጀንዳ መሆን የለበትም ሲሉም ተቃውሟቸውን አሰምተው እንደነበር የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#RUSSIA #AFRICA

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬን ወደ አፍሪካ ለሚገቡ የስንዴ ምርቶች ሁኔታዎችን እንደሚያመቻቹ አሳውቀዋል።

ፑቲን የስንዴ ምርቶች ወደ አፍሪካ መላካቸውን ለማረጋገጥ ሃገራቸው እንደምትሰራም ገልጸዋል፡፡

ይህን የገለፁት ከወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር እና ከሴኔጋል ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል ጋር ከጦርነቱ ጋር በተያያዙ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሶቺ ከተማ በተወያዩበት ወቅት ነው።

በውይይቱ ወቅት ማኪ ሳል አፍሪካ በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ቀጥተኛ ተሳትፎ ባይኖራትም በጦርነቱ ምክንያት ሰለባ መሆኗን ገልፀዋል።

በተለይ ከዩክሬንና ሩሲያ ይገቡ የነበሩ የግብርና ምርቶች እና ግብዓቶች ጉዳይ አፍሪካን ለከፋ የምግብ ዋስትና ችግር እንደዳረጋት አስረድተዋል።

ሩሲያን ጨምሮ የአፍሪካ አጋር የሆኑ ሁሉም ሃገራት የጣሏቸውንና በስንዴ እና በማዳበሪያ ላይ ያነጣጠሩ ማዕቀቦቻቸውን እንዲያነሱም ጠይቀዋል፡፡

የሩሲያ ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሀገራቸው ሩድያ የምግዜም የአፍሪካ አጋር መሆኗን ገልፀው ከዩክሬን ወደ አፍሪካ ለሚገቡ የስንዴ ምርቶች በወደብ ላይ ለቀሩትም ጭምር ሁኔታዎችን እንደሚያመቻቹ ገልጸዋል፡፡

ፕሬዜዳንት ፑቲን ሰው ሰራሽ #የአፈር_ማዳበሪያ ምርቶች አፍሪካ መድረሳቸውን ለማረጋገጥ ዝግጁ ስለመሆናቸውም አሳውቀዋል።

ከ40 በመቶ የሚልቀው የአፍሪካ የስንዴ ፍጆታ በዩክሬን እና በሩሲያ የስንዴ ምርቶች የሚሸፈን ነው፡፡

መረጃው የአል አይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia
#Russia #Africa

በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ፤ በሁለተኛው የአፍሪካ ራሺያ የጋር ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ሩስያ፤ ሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ይገኛል።

ልዑካን ቡድኑ ከሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በመገናኘት፣ በሁለቱ አገራት ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይም መክሯል።

ነገ ከሚጀመረው የሩስያ - አፍሪካ የጋራ ጉባኤ ጎን ለጎን ኢትዮጵያና ሩስያ 15 የሚደርሱ የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነቶችን እንደሚፈራረሙ ፕሬዝዳንት ፑቲን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ ገልጸውላቸዋል።

የትብብር ስምምነት ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ፣ ኢትዮጵያ ከአቶሚክ ኃይል ኤሌክትሪክ ለማመንጨትና ለመጠቀም የሚያስችላት የትብብር ፍኖተ ካርታ እንደሆነ ፕሬዝዳንት ፑቲን ገልጸዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ሁለቱ አገራት በሳይበር ደህንነትና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መስክ ለመተባበር ስምምነት እንደሚፈራረሙ ታውቋል።

" በሩስያ ቆይታዎ ወቅት የትብብር ስምምነት የምናደርግባቸውን የሰነዶች ፓኬጅ አዘጋጅተናል፤ ከነዚህም መካከል የመረጃ ደህንነት ስምምነት ፣ በአየር ትራፊክ ፣ በኢንፎርሜሽንና የግንኙነት ቴክኖሎጂዎች መስክ የመግባቢያ ሰነድ ፣ የአቶሚክ ኢነርጂን ለመጠቀም የሚያስችል የትብብር ፍኖተ ካርታ ፣ በጉምሩክ አገልግሎቶች ፕሮቶኮልና ሌሎች " ሲሉ ፕሬዚደንት ፑቲን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ ተናግርዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ በበኩላቸው ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ግልጽ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል።

" ታሪካዊ ትሥሥራችንን መሠረት አድርገን ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ኢኮኖሚያዊ ትብብራችንን ማሳደግ እንቀጥላለን " ሲሉ አሳውቀዋል።

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#Amaharic #Russia

ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ በሞስኮ የሚገኙ ት/ቤቶች የአፍሪካ ቋንቋዎችን ማስተማር ይጀምራሉ ተባለ።

በዚህም የአማርኛ ቋንቋ አንዱ ሆኖ ይሰጣል።

የሞስኮ ትምህርትና ሳይንስ ክፍልን ዋቢ በማድረግ ስፑትኒክ እንደዘገበው ፤ ሩሲያ ባለፈው ግንቦት ወር ላይ ከመስከረም ወር ጀምሮ #አማርኛ እና #ስህዋህሊ ቋንቋዎችን በሞስኮ በሚገኙ በአራት ት/ቤቶች ማስተማር እንደምትጀምር ባሳወቀችው መሰረት ትምህርቱ መሰጠት ይጀምራል።

እንደ ዘገባው ከሆነ " 1517 " የተሰኘው የፔዳጎጂ ትምህርት ቤት ስዋህሊ ቋንቋን ሁለተኛው የውጭ ቋንቋ አድርጎ ያስተምራል።

" 1522 " የተሰኘው ትምህርት ቤት ደግሞ አማርኛ ቋንቋን እንደሚያስተምር ተገልጿል።

ሩሲያ የአፍሪካ እና ሞስኮን ወዳጅነት ለማጠናከር በሳምንት አንድ ወይም ሁለት የትምህርት ክፍለ ጊዜዎች ለአፍሪካ ቋንቋዎች ማስተማሪያ እንዲውሉ ይደረጋል ብላለች።

ሩሲያ በቀጣይ በምዕራብ አፍሪካ ሰፊ ተናጋሪ ያለው ዩርባ ቋንቋን ማስተማር እንደምትጀምር ገልጻለች።

በመቀጥልም #ሶማልኛ እና የዙሉ ቋንቋዎችን በሩሲያ ትምህርት ቤቶች ለማስተማር የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ ነው።

ሌላኛዋ ሀገር ቻይና አማርኛ ቋንቋን በመጀመሪያ ድግሪ ደረጃ ማስተማር እንደምትጀምር ከዚህ ቀደም መግለጿ ይታወቃል።

አማርኛ ቋንቋ በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) ከሚሰጡ 101 የውጭ ቋንቋ ትምህርቶች አንዱ ሆኖ ይሰጣል ተብሏል።

መረጃው የ #አልዓይን (ስፑትኒክ) ነው።

ስፑትኒክ አፍሪካ ፦ https://www.facebook.com/100091796831512/posts/pfbid02Zf2NYdkBuBFDA8UDxBbtf5ZBGbRVPjYGUWzgeLVL365qBrKQgthGS622GJqo2PNul/?app=fbl

@tikvahethiopia
#RUSSIA

ሩስያ ባለፈው ሳምንት ማንኛውም የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት እንቀስቃሴን #ሕገወጥ በማለት ፈርጃለች።

የሩሲያ ጠቅላይ ፍ/ቤት ዓለም አቀፍ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት የአደባባይ እንቅስቃሴን " #ጽንፈኛ " በማለት ማንኛውንም እንቅስቃሴዎችን አግዷል።

ይህ እገዳ ይፋ ከተደረገ በኃላ ባለፈው አርብ ምሽት የሩስያ ፀጥታ ኃይሎች በሞስኮ ከተማ በሚገኙ ፦
° የተመሳሳይ ጾታ የምሽት ክበቦች (ክለቦች) ° የተመሳሳይ ፆታ ፓርቲዎችን ያዘጋጃሉ በተባሉ ባሮች
° የወንዶች ሳውና ቤቶች ላይ ዘመቻ ማካሄዳቸው ተነግሯል።

ፖሊስ በርካታ የተመሳሳይ ጾታ ክለቦችን ውስጥ በመግባት የተወሰኑትን ታዳሚዎች አጠር ላለ ጊዜ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ታውቋል።

በተጨማሪም የአንዳንዶች ፖስፖርት ተወስዶ ፎቶ እንዲነሳ ተደርጓል ተብሏል።

ፖሊስ የምሽት ክበቦች ላይ ዘመቻ ያካሄድኩት " አደንዛዥ እፅ ለመፈለግ ነው " ማለቱ ተነግሯል።

ሩስያ ፦

- ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት የአደባባይ እንቅስቃሴ ጽንፈኛ ነው በማለት ማንኛውንም እንቅስቃሴዎች አግዷል።

- እግድ የተላለፈው የፍትህ ሚኒስቴር ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ነው።

- በሩሲያ የተመሳሳይ ጾታ ጥምረት እውቅና #የለውም

- በሩሲያ #ትዳር ማለት የወንድ እና የሴት ጥምረት ማለት ስለመሆኑ ትርጉም ለመስጠት የአገሪቱ ሕገ መንግሥት ከ3 ዓመታት በፊት ተቀይሮ ነበር።

- እኤአ 2013 ላይ ከተለመደው ውጪ ያለ ጾታዊ ግንኙነት ላይ የሚደረግ ፕሮፖጋንዳን የሚከለክል ሕግ አውጥታለች።

- የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪያንን የሚያመለክቱ ይዘቶች ከመጽሓፍት፣ ከፊልሞች፣ ከማስታወቂያዎች እና ከቴሌቪዥን ፕሮግራሞች እንዲሰረዙ ተደርገዋል።

- በቅርቡ አንድ የሩሲያ የቴሌቪዥን ጣቢያ የፕሮፓጋንዳውን ሕግ ጥሷል ተብሎ እንዳይከሰስ በደቡብ ኮሪያ የፖፕ ሙዚቃ ቪዲዮ ላይ የነበረውን የተመሳሳይ ፆታ መግለጫ የሆነውን ቀለም እንዲለውጥ መገደዱን ገልጿል።

መረጃው ከቢቢሲ / አስቶሮዥኖ ኖቮስቲ / ፣ ሮይተርስ፣ አልጀዚራ  የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
ቱርክ #ኢትዮጵያም ያለችበትን የBRICS ስብሰብ ትቀላቀል ይሆን ?

ባለፈው ሳምንት የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን የBRICS አባሏን ቻይናን ጎብኝተው ነበር።

በጉብኝታቸው ወቅት ከቻይና ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

በወቅቱ ሀገራቸው ቱርክ የBRICS ስብስብን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተጠይቀው ፥ " በእርግጥም #እንፈልጋለን። ለምን አንፈልግም ? " ብለዋል።

" በእርግጥም ፤ የBRICS አባል መሆን እንፈልጋለን " ያሉት ፊዳን " ስለዚህ በዚህ አመት እንዴት እንደሚሄድ እናያለን " ሲሉ ተናግረዋል።

ተጨማሪ ነገር ከመናገር ግን ተቆጥበዋል።

አናዱሉ እንደዘገበው ደግሞ ቱርክ የBRICS  አባላት ሀገራትን ትብብር እየተመለከተች ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሁለት ቀን በፊትም ወደ ሩስያ አቅንተው ከBRICS አባሏ ሩስያ ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በዝግ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።

በBRICS አባል ሀገራት ስብሰባ ላይ ተገኝተዋል።

ፑቲን ከሚኒስትሩ ጋር በነበራቸው ስብሰባ ቱርክ ስብስቡን ለመቀላቀል (አብሮ ለመስራት) ያሳየችውን ፍላጎት በደስታ ተቀብለው ፤ ወደ ስብስቡ እንድትቀላቀል ሙሉ ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ ገልጸዋል።

የቱርክ መንግሥት BRICS'ን ለመቀላቀል ርምጃ ይወስድ እንደሆነ እስካሁን የሚታወቅ ነገር የለም። ከዚህ ቀደም በይፋ ስብሰቡን ለመቀላቀል ያለውን ፍላጎት በይፋ አሳውቆ አያውቅም።

ቱርክ የ #NATO አባል ሀገር እንደሆነች ይታወቃል።

#BRICS+ ኢትዮጵያን ጨምሮ የሩስያ ፣ የብራዚል ፣ የቻይና ፣ የህንድ ፣ የደቡብ አፍሪካ ፣ የኢራን ፣ የግብፅ ፣ የዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ ስብስብ ነው።

#BRICS
#Turkey
#China
#Russia

@tikvahethiopia