TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NBE

በባንኮች እና በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ገንዘብ አስቀማጮች ዋስትና ለመስጠት የተቋቋመው የተቀማጭ ገንዘብ መድን ፈንድ እስከ 200 ሺሕ ብር ተቀማጭ ገንዘብ ላላቸው ዋስትና እንደሚሰጥ ተገለጸ፡፡

ባንኮች እና የማክሮ ፋይናንስ ተቋማት በየዓመቱ ከተቀማጭ ገንዘባቸው 0.2 በመቶ ለፈንዱ ገቢ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ አቶ ሰለሞን ደስታ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተከታዩን ብለዋል ፦

" በየባንኩ ለእያንዳንዱ አስቀማጭ እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆን ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋን ይሰጣል፡፡

የመድን ሽፋኑ መጠን እስከ 200 ሺሕ ብር ለሚሆነው ተቀማጭ ገንዘብ የዋስትና ሽፋኑ እንዲሰጥ የተወሰነው፣ 96 በመቶ ያህል አስቀማጮች የተቀማጭ ገንዘባቸው መጠን የተጠቀሰውን ያህል ስለሆነ ነው።

በዚህ መሠረት የመድን ሽፋኑ ይሰጣል። ይህ ውሳኔ አብዛኞቹን አስቀማጮች የሚሸፍን ነው።

ባንኮች ለዚህ ዋስትና ሽፋን ተቀማጭ የሚያደርጉት በየዓመቱ ከጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘባቸው 0.2 በመቶ የሚሆነውን በማስላት ለፈንዱ ገቢ በማድረግ ተፈጻሚ ይሆናል።

የተቀማጭ ገንዘብ ዋስትና ፈንድ አገልግሎት ሲጀመር ባንኮቹ የሚከፍሉት ክፍያ ይኖራል። የገንዘቡ መጠን ግን ገና አልተወሰነም ። "

More : https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-05-07

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
" የ10 በመቶ የተርን ኦቨር ታክስ ተነስቷል "

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ የሜትር ታክሲ አገልግሎት ከሚሰጡ ተሽከርካሪዎች ይሰበስብ የነበረውን አሥር በመቶ የተርን ኦቨር ታክስ (ቲኦቲ) ማንሳቱን ሪፖርተር አስነብቧል።

ቢሮው ከገንዘብ ሚኒስቴር አገኘሁት ባለው ማብራሪያ መሠረት፣ በኮድ 03 የሜትር ታክሲ አገልግሎት የሚሰጡትን ተሽከርካሪዎች ነው የተጨማሪ እሴት ታክስና ተርን ኦቨር ታክስ ተግባራዊ እንዳይሆንባቸው የወሰነው፡፡

ተሽከርካሪዎቹ በንግድ ሥራ ፈቃዳቸው ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ቢልም፣ ሊብሬያቸው የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ እንደሆኑ በመጥቀሱ አሥር በመቶው የአገልግሎት ሰጪዎች ተርን ኦቨር ታክስ ተግባራዊ ይደረግባቸው ነበር፡፡

ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. በታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ታዬ ማስረሻ ተፈርሞ ለአሥራ አንዱም ክፍላተ ከተሞችና ለአምስት ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች የተላከው ደብዳቤ፣ አገልግሎቱን የሚሰጡ የሜትር ታክሲ ተሽከርካሪዎች ከሁለቱ ታክሶች ነፃ እንዲሆኑ አስታውቋል፡፡

ደብዳቤው ላይ " የሚሰጡት አገልግሎት የትራንስፖርት በመሆኑ የንግድ ሥራ ገቢ ግብርን በተመለከተ ግብር ከፋዮች የሚያቀርቡት የሒሳብ መዝገብ፣ የሒሳብ መዝገብ ካልያዙ ደግሞ በመረጃ እንዲስተናገዱ "  ይላል።

በገቢዎች ቢሮ የግብር አወሳሰንና አሰባሰብ ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኘሁ ካሳዬ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፥

" የሜትር ታክሲዎች የብቃት ማረጋገጫቸው የመኪና ኪራይ የሚልና ኮድ 3 ሰሌዳ የሚወስዱ ቢሆንም፣ በኮድ 1 ተሽከርካሪዎችም ተመሳሳይ አገልግሎት ይሰጣል፡፡

ይህ ደግሞ ተመሳሳይ አገልግሎት የሚሰጡትን የተለያየ የታክስ አከፋፈል ስለሚተገበርባቸው ቅሬታ ሲያስነሳ ነበር።

የኅብረተሰቡን የትራንስፖርት ጫና በማየትና ተሽከርካሪዎችን እንደ ኮድ 1 በመቁጠር፣ ቢሮው ታክሱን አንስቷል።

በኮድ 3 የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን ከታክሱ ነፃ መሆን ዕድል ተጠቃሚ እንዳይሆኑ፣ እነሱን ለመለየት በሲስተሙ ላይ እየሠራ ነው።

የሜትር ታክሲ አገልግሎት ከሚያቀላጥፉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችም መረጃ እየሰበሰብን ነው። "  ሲሉ አስረድተዋል፡፡

Credit : #ሪፖርተር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
' ሕዝበ ውሳኔ ' የአማራ ክልል መንግሥት የማንነት እና የወሰን ጥያቄ በሕዝበ ውሳኔ እንዲፈታ ስራዎች እየተሰሩ ነው ሲል አሳወቀ። የክልሉ መንግሥት ይህን ያሳወቀው ዛሬ በኮሚኒኬሽን ቢሮው በኩል በሰጠው መግለጫ ነው። የክልሉ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫቸው ፤ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች ጥያቄ የሚያነሱባቸውን የማንነት እና የወሰን ጉዳዮችን…
" እኛ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየጠበቅን ነው " - ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

የአማራ እና የትግራይ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን የወልቃይት፣ የጠለምትና የራያ አካባቢዎችን " ይገባኛል " ጥያቄን በተመለከተ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየተጠበቁ መሆናቸውን ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል አሳውቀዋል።

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በአሁን ሰዓት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ  ምክትል አስተዳዳሪ እና የሰላምና የፀጥታ መምርያ ኃላፊ በመሆን እያገለገሉ ሲሆን በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ በቀረቡበት ወቅት " ሁለቱ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን አካባቢዎች በሕዝብ ውሳኔና በሕጋዊ መንገድ መፍታት አለባቸው " በሚል ስለሰጡት አስተያየት ተጠይቀው መልሰዋል።

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ምን አሉ ?

" በወልቃይት ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሳኔ እናደርጋለን ሲሉ በግልጽ አልሰማንም፡፡

ነገር ግን በሕጋዊ መንገድ ቢፈታ ይሻላል የሚለውን ምክር አዘል ነገር ለፓርላማው ሲናገሩ ሰምተናል፡፡

ግን በዚህኛው ቀጣና በዚህኛው ዞን ብለው ሲያነሱ እኔም በግል አልሰማሁም፣ እኛም የምናውቀው ነገርም የለም። ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ በየትኛው መንገድ ነው ሊፈታ የሚገባው የሚለውን ቀደም ሲል በተደጋጋሚ ተናግረናል፡፡

ሊፈታ በሚገባው መንገድ እንዲፈታ ለመንግሥት አመልክተናል።

ራያም፣ ጠለምትም፣ ወልቃይትም ስላሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለየትኛው እንደተናገሩ ግልጽ አልሆነልኝም። በግምት መልስ ለመስጠት ያስቸግራል።

ብዙ ሰው መላምት ሊኖረው ይችላል፡፡ ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ ሊፈታ የሚገባበትን መንገድ ጠቅሰን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ስላቀረብን ውሳኔውን እየጠበቅን ነው።

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅትም ሆነ አሁን ከማኅበረሰቡ ጋር ነኝ ፤ የአገር መከላከያ ሠራዊት የወልቃይት አካባቢን እየተከላከለና እየጠበቀ እንዳለ ነው የምናውቀው።

በአካባቢው ከመከላከያ ጋር ምንም ዓይነት ጦርነት የለም፣ ተባብረን ነው እየሠራን ያለነው፡፡ አካባቢው ሰላማዊ በመሆኑ ፋኖ በሚል ምክንያት ምንም ዓይነት ግጭትም ሆነ ጦርነት የለም። "

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳዳር በበኩሉ የክልሉ አስተዳደራዊ ወሰን ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ፣ በጦርነቱ ምክንያት ከምዕራብ ትግራይና ከሌሎች የአማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈናቀሉ የክልሉ ነዋሪዎቸ በአፋጣኝ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ በተደጋጋሚ ጥያቄ እያቀረበ ነው፡፡

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#Russia #Africa

በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ፤ በሁለተኛው የአፍሪካ ራሺያ የጋር ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ሩስያ፤ ሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ይገኛል።

ልዑካን ቡድኑ ከሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በመገናኘት፣ በሁለቱ አገራት ትብብርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይም መክሯል።

ነገ ከሚጀመረው የሩስያ - አፍሪካ የጋራ ጉባኤ ጎን ለጎን ኢትዮጵያና ሩስያ 15 የሚደርሱ የሁለትዮሽ የትብብር ስምምነቶችን እንደሚፈራረሙ ፕሬዝዳንት ፑቲን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ ገልጸውላቸዋል።

የትብብር ስምምነት ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ፣ ኢትዮጵያ ከአቶሚክ ኃይል ኤሌክትሪክ ለማመንጨትና ለመጠቀም የሚያስችላት የትብብር ፍኖተ ካርታ እንደሆነ ፕሬዝዳንት ፑቲን ገልጸዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ሁለቱ አገራት በሳይበር ደህንነትና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መስክ ለመተባበር ስምምነት እንደሚፈራረሙ ታውቋል።

" በሩስያ ቆይታዎ ወቅት የትብብር ስምምነት የምናደርግባቸውን የሰነዶች ፓኬጅ አዘጋጅተናል፤ ከነዚህም መካከል የመረጃ ደህንነት ስምምነት ፣ በአየር ትራፊክ ፣ በኢንፎርሜሽንና የግንኙነት ቴክኖሎጂዎች መስክ የመግባቢያ ሰነድ ፣ የአቶሚክ ኢነርጂን ለመጠቀም የሚያስችል የትብብር ፍኖተ ካርታ ፣ በጉምሩክ አገልግሎቶች ፕሮቶኮልና ሌሎች " ሲሉ ፕሬዚደንት ፑቲን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ ተናግርዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ በበኩላቸው ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ግልጽ ውይይት ማድረጋቸውን አመልክተዋል።

" ታሪካዊ ትሥሥራችንን መሠረት አድርገን ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን እና ኢኮኖሚያዊ ትብብራችንን ማሳደግ እንቀጥላለን " ሲሉ አሳውቀዋል።

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

• " ትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔውን መልሶ ያጢን " - የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር

• " ታስቦበት ኪሳራና ትርፍን ተመዝኖ የተሻለውን ማድረግ እንደሚሻል ታምኖበት የተወሰነ ውሳኔ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ.ም የክረምት ትምህርት መርሐግብር እንዳይሰጥ ያስተላለፈውን ውሳኔ መልሶ እንዲያጤነው የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ጠየቀ፡፡

ባለፉት ዓመታት የኮቪድ-19 ወረርሽኝና ጦርነት በክረምት ሥልጠና መርሐግብር ሥልጠና ላይ ያሳደረው ጫና ሳይካካስ፣ በ2015 የመምህራንና የትምህርት አመራሮች የክረምት ሥልጠና እንደማይሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቁ ማኅበሩን እንዳሳሰበው ለትምህርት ሚኒስቴር በላከው ደብዳቤ አስገንዝቧል፡፡

የሚኒስቴሩ ክልከላ በቀጣይም ችግር የሚፈጥርና የመልካም አስተዳደር ግድፈት ምንጭ እንደሚሆን ማኅበሩ አሳስቧል፡፡

የአሠራር ሥርዓት ሳይዘረጋለት ሥልጠናውን ማቋረጡ ተገቢ ስለማይሆን፣ ሐምሌ 2015 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላለፈው ሰርኩላር እንደገና እንዲታይ ጠይቋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር በተለያዩ ምክንያቶች ላለፉት ዓመታት የተዛነፈውን የትምህርት ካላንደር ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ለማስተካከል እየሠራ መሆኑን ለተቋማቱ በላከው ሰርኩላር ጠቁሟል።

ሚኒስቴሩ ደብዳቤውን ከመጻፉ በፊት ምንም ዓይነት የቅድመ ማስጠንቀቂያ ለማኅበሩም ሆነ ለመምህራኑ አለመስጠቱን የአዲስ አበባ መምህራን ማኅበር ፕሬዝዳንት ድንቃለም ቶሎሳ ለሪፖርተር ተናግረዋል።

ትምህርታቸው ከተስተጓጎለባቸው መምህራን መካከል በዚህ ዓመት መጨረስ የነበረባቸው ፣ የመመረቂያ ጽሑፍ ብቻ የቀራቸው እንዲሁም በሚሠሩባቸው ተቋማት ትምህርቱን ጨርሰው የደረጃ ዕድገት ሊያገኙ የሚገባቸው የነበሩ ቢሆንም በሚኒስቴሩ ደብዳቤ ምክንያት ይህን ማግኘት አልቻሉም ተብሏል፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ደኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) " በአንድ ወር ትምህርት ተሰጥቶ መምህር መፍጠር አይቻልም፣ በዚህ በኩል ትምህርት ጥራት እየተባለ በሌላ በኩል በአንድ ወር ዲግሪ እንደተማረ ተደርጎ ይነገራል፣ ይህ አብሮ አይሄድም ስለዚህ መታረም አለበት " ብለዋል፡፡

ዶ/ር ሳሙኤል ፤ የትምህርት ሚኒስቴር በራሱ ዕቅድ የሚሄድ በመሆኑ ታስቦበት ኪሳራና ትርፍን መዝኖ የተሻለውን ማድረግ እንደሚሻል ታምኖበት የተወሰነ ውሳኔ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

#ሪፖርተር

More : @tikvahuniversity
#AddisAbaba

" የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተን ለማደር ተቸግረናል " - ነዋሪዎች

በአዲስ አበባ ከተማ ከጤፍ ዋጋ መጨመር ጋር ተያይዞ የእንጀራ ዋጋ በመጨመሩ በልተው ለማደር መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ።

ለሪፖርተር ጋዜጣ ቃላቸውን የሰጡ የከተማው ነዋሪዎች ፤ ሰሞኑን የአንድ እንጀራ ዋጋ ቀደም ሲል ከነበረበት 17 ብር ወደ 22 እና 24 ብር ከፍ በማለቱ፣ ገዝተው ለመጠቀም ተቸግረዋል፡፡

እንጀራን ጋግረው ለመጠቀም ባለመቻላቸው ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን የተናገሩት እንዲት ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ እናት፣ የሚከፈላቸው የ3,000 ብር ደመወዝ ከወር ስለማያደርሳቸው በብድር እንደሚጠቀሙ ገልጸዋል፡፡

እንጀራን ጨምሮ ሌሎች ሸቀጦች ላይ እየታየ ያለው የዋጋ ጭማሪም እንዳማረራቸውም እኚሁ እናት አክለዋል።

በተመሳሳይ መልኩ የእንጀራ ዋጋ በአንድ ጊዜ ከአምስት እስከ ሰባት ብር መጨመሩን የተናገረው ወጣት ሻምበል ቢሆነኝ፣ ወጣቱ እንዳለው ከሆነ እንጀራን በቤት እንኳን ለማስጋገር አከራዮች " መብራት ይቆጥርብናል " በማለት ፈቃደኛ ስለማይሆኑ እየገዛ ለመብላት መገደዱን ተናግሯል፡፡

በዚህም ሰሞኑን በእንጀራ ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ከሚከፈለው የወር ደመወዝ ጋር ፈፅሞ የማይመጣጠን ነው ሲል አብራርቷል።

እንጀራ ሻጮችን ዋጋ ለምን እንደጨመሩ ሲጠይቃቸው፣ " ጤፍ ጨምሯል ስለተባልን ነው "  እንደሚሉት ገልጿል።

ጋዜጣው በአንዳንድ የእንጀራ መሸጫ ሱቆች  ተዘዋውሬ ተመልክቻለው ባለው የእንጀራ ዋጋ ከ14 ብር ጀምሮ 17፣ 22 እና 24 ብር እየተሸጠ ነው።

የእንጀራ መሸጫ ዋጋ በዚህን ያህል የዋጋ ልዩነት ለምን እንዳሳየ ነጋዴዎች ሲጠየቁ የእንጀራው መወፈርና መሳሳት፣ እንዲሁም በጤፉ ላይ የሚቀላቀለው እህል መብዛት እንደሆነ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ስለዋጋው ጭማሪ ደግሞ የጤፍ ዋጋ ከመጨመሩ ጋር ተያይዞ እንደሆነም ጠቁመዋል። ተደረገ የተባለው የዋጋ ጭማሪ በመርካቶ እህል በረንዳ ባሉ መጋዘኖችም እንደታየ ተመላክቷል።

ብዙ የጤፍ አቅርቦት እንደሌለና የሚመጣው ጤፍ ደግሞ ዋጋው እየጨመረ መሆኑን አንዳንድ ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ ነጋዴዎች ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ፤ በተለይ በቢሾፍቱና በዱከም አካባቢ ወደ አዲስ አበባ የሚገባውን ጤፍ፣ በአካባቢው ያሉ ሆቴሎች አርሶ አደሮችም ሆኑ ነጋዴዎች አዲስ አበባ አምጥተው ከሚሸጡበት ዋጋ በላይ ስለሚገዟቸው በአቅርቦቱ ላይ ጫና ማሳደሩን ተናግረዋል።

በአማራ ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ ግጭት ከጎጃምና አካባቢው ወደ መዲናዋ የሚገባው ጤፍ መቅረቱ ደግሞ አሁን ለታየው የዋጋ ጭማሪ ሌላው መንስዔ መሆኑን ነጋዴዎቹ አብራርተዋል።

ሰኞ ነሐሴ 15 ቀን 2015 ዓ.ም፣ በእህል በረንዳ በነበረው ወቅታዊ ግብይት ፦
- ማኛ ነጭ ጤፍ 13,500 ብር እየተሸጠ ሲሆን፣
- ሠርገኛ ጤፍ ከ10,000 ብር እስከ 10,700 ብር፣
- ቀይ ጤፍ ከ9,500 ብር እስከ 10,000 ሺሕ ብር ሲሸጥ መቆየቱን ለመመልከት ተችሏል።

ሌሎች ነጋዴዎች እንዳሉት ከሆነ ደግሞ በጎጃም በኩል የሚገባው ጤፍ መቅረቱ የተወሰነ እጥረትን ቢያስከትልም፣ ከአርባ ምንጭና ከባሌ፣ እንዲሁም ከሌሎች አካባቢዎች የሚገባው ጤፍ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረው፣ አከፋፋዮችም የቻሉትን ያህል እየጫኑና እየወዱ ነው። በዚህም የምርት እጥረት አለ የሚባለውን እንደማያምኑበት ነው የተናገሩት።

ያንብቡ - https://telegra.ph/Reporter-08-23-3

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#የዋጋ_ንረት📈

መስከረም 2015 መጀመርያ ላይ ከ6 ሺሕ ብር በታች ይሸጥ የነበረ አንድ ኩንታል ነጭ ጤፍ ለመጀመርያ ጊዜ ከ10 ሺሕ ብር በላይ ዋጋ ያወጣው ሊጠናቀቅ ሰዓታት በቀሩትና አሮጌ ብለን ልንሸኘው በተዘጋጀው 2015 ዓ.ም. ነው፡፡ የጤፍ ዋጋ ነሐሴ 2015 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ እስከ 15 ሺሕ ብር ሲደርስ ይኸው የዋጋ ጭማሪ 1 ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከዕጥፍ በላይ እንደደረሰ ያመለክታል።

#የስንዴ_ገበያም በተመሳሳይ ከፍተኛ የሆነ ዋጋ የተመዘገበበት ዓመት ይኼው 2015 ዓ.ም. ነው፡፡

በአጠቃላይ ከጤፍና ስንዴ በተጨማሪ በሌሊችም ምግብ ነክ እና ምግብ ነክ ባለሆኑ ሸቀጦች ላይ በዚህ ልንሸኘው ጥቂት ሰዓታት በቀረን 2015 ከፍተኛ የሆነ ዋጋ ተመዝግቧል።

የኢኮኖሚው ባለሙያ አቶ አወት ተክኤ ምን ይላሉ ?

" በሀገሪቱ ከፀጥታና አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች የዋጋ ንረትን በማባባስ ዓይነተኛ ሚና ነበራቸው። አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች እንዳይስፋፉ ጭምር አድርገዋል።

በ2015 ዓ/ም በጀት ዓመት ለዋጋ ንረቱ መባባስ በተደጋጋሚ ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ባሻገር፣ መንግሥት የወሰዳቸው የፖሊሲ ዕርምጃዎች ለዋጋ ንረቱ አስተዋጽኦ ነበራቸው።

ለአብነት የኢኮኖሚ የነዳጅ ጭማሪ እና ሌሎች የመንግሥት የፖሊሲ ውሳኔዎች ለዋጋ ንረቱ የራሳቸው አስተዋጽኦ አድርገዋል።

ይህ የዋጋ ንረት በቀጣይ ዓመትም እንዳይተላለፍ ለችግሩ መንስዔ የነበሩት፣ ለምሳሌ የፀጥታና ያለ መረጋጋቶች መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡

በቅርቡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ውሳኔዎችን በአግባቡ መተግበር ለዋጋ ንረት መርገብ መፍትሔ ሊሆኑ ይገባል፡፡ "

ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Ethiopianreporter-09-11

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ለግብፅ መግለጫ ምን ምላሽ ተሰጠ ?

" ግብፆቹ ስለ4ኛው ሙሌት በደንብ ያውቃሉ ፤ ምንም የተጣሰ መርህ የለም " - ኢ/ር ጌዲዮን አስፋው

ከሰሞኑን ኢትዮጵያ 4ኛውን ዙር የአባይ ግድብ የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን በይፋ ካሳወቀች በኃላ ግብፅ ሙሌቱ ህገወጥ እንደሆነና እ.ኤ.አ. በ2015 በሱዳን፣ በግብፅና በኢትዮጵያ የተፈረመውን የመርህ ስምምነት  የጣሰ ነው በሚል ቁጣ አዘል መግለጫ አውጥታ ነበር።

ለዚህ ግብፅ መግለጫ ምላሽ የሰጡት የኢትዮጵያ ተደራዳሪዎችና ባለስልጣናት " ምንም የተጣሰ ነገር የለም ፤  መግለጫዋ ለሀገር ውስጥ የሚዲያ ፍጆታ የሚውል ነው " ብለውታል።

የኢትዮጵያ የግድቡ ተደራዳሪ ኢንጂነር ጌዲዮን አስፋው ምን አሉ ?

" ምንም የተጣሰ ነገር የለም፡፡ ግብፆች ያወጡት ነገር ትክክል አይደለም፡፡ የመርህ ስምምነቱ አልተጣሰም፡፡

በመርህ ስምምነቱ መሠረት የወጣ የሙሌት ሠንጠረዥ አለ፣ በእሱ መሠረት ነው አሁን የሞላነው፡፡

አሁን በቅርቡ የተጀመረው ድርድር የአገሮቹ መሪዎች በሰጡት መመርያ መሠረት የተጀመረና የተካሄደ ነው።

የሦስትዮሽ ድርድር ከአንድ ዓመት በላይ ተቋርጦ የነበረው ከቆመበት መቀጠል እንጂ፣ አዲስ ድርድር አይደለም።

አራተኛው ሙሌት በቅርቡ ከተጀመረው ድርድር ጋር ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡

ግብፆቹ ስለአራተኛው ሙሌት በደንብ ያውቃሉ፡፡ በተስማማነው መሠረት ነው የተሞላው። "

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ምን አሉ ?

" ሙሌቱ በሌሎች የተፋሰሱ አገሮች ላይ ትርጉም ያለው ተፅዕኖ የለውም።

የእነሱ የሚዲያ እንካ ሰላንቲያ የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የቀጠለ ነው፡፡

አሁን ያወጡት መግለጫም የተለመደ የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ፍጆታ ነው፣ ለውስጥ ፍጆታ የሚጠቀሙበት ነው፡፡

እኛ የእነሱ የሚዲያ እንካ ሰላንቲያ ውስጥ መግባት አንፈልግም፡፡

ይኼ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያከብረው ፕሮጀክት ነው፡፡ ግድቡ የትብብር እንጂ የፉክክር ምንጭ መሆን የለበትም። "

Credit - #ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች አስጠልላቸው የሚገኙ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ስደተኞች የዕርዳታ እህል በመቋረጡ፣ ሕይወታቸው አደጋ ላይ መሆኑንና ለአገርም የደኅንነት ሥጋት መደቀኑ ተነገረ፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት የዓለም የምግብ ፕሮግራምና የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (USAID) በኢትዮጵያ ተፈጸመ ባሉት የዕርዳታ እህል ዝርፊያ ምክንያት ለኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ዕርዳታ ማቆማቸው ይታወሳል፡፡

የምግብ አቅርቦቱ እንደገና እንዲጀመር የኢትዮጵያ መንግሥት እየተነጋገርኩበት ነው ቢልም፣ ዕርዳታው እየቀረበ ባለመሆኑ በኢትዮጵያ የተጠለሉ የውጭ አገሮች ስደተኞች በምግብ ዕጦት እየሞቱና ሕመም ላይ መውደቃቸውን፣ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት አስታውቋል፡፡

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ምን አለ ?

- ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ ስታስተናግድ የዓለም አቀፉን ሕግ መሠረት በማድረግ ከለላና ጥበቃ የምታደርግ ቢሆንም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለስደተኞች የሚቀርበው ዕርዳታ በመቆሙ ቀውስ ተፈጥሯል።

- በምግብ እጥረት ምክንያት የሚሞቱትና የሚታመሙት ወይም የሚቸገሩት ስደተኞች ብቻ ሳይሆኑ፣ ችግር ሲፈጠር በመሠረታዊነት የመጀመርያ ተጎጂ ሕፃናትና ሴቶች ናቸው።

- በመጠለያ ካምፕ የሚገኝን ሀብት አፈላልጎ ለመመገብ ጥረት በሚያደርግበት ወቅት፣ ስደተኞቹ ከአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር ግጭት ውስጥ ይገቡና ሰላማዊ የኑሮ ሁኔታን የሚያናጋ ነገር እየተፈጠረ ነው።

- በአሁኑ ወቅት ምግብ ነክ ድጋፎች እየቀረቡ ባለመሆናቸእ በቀጣይ አፋጣኝ ዕርምጃ ካልተወሰደ ችግሩ የከፋ ሊሆን ይቻላል። በሁሉም የአገሪቱ መጠለያ ካምፖች ችግሩ ተከቷል።

- በኢትዮጵያ የሚገኙ ስደተኞችን ለመታደግ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ንግግር እየተደረገ ነው ፤ በአጭር ጊዜ ዕርዳታው እንደገና ይጀመራል የሚል እምነት አለ።

በስደተኛ ቁጥር ፦
👉 በጋምቤላ ወደ 400,000
👉 በቦሎ መልካዲዳ በሶማሌ ክልል 200,000፣
👉 በቤኒሻንጉል አሶሳ ወደ 90,000፣
👉 በአፋር 68,000፣
👉 በሶማሌ ጅግጅጋ ወደ 50,000፣
👉 አማራ ክልል ባባት 25,000፣ መተማ ወደ 40,000፣ እንዲሁም በአዲስ አበባ ወደ 80,000 ስደኞች ይገኛሉ።

ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ስደተኞች መካከል ከ900,000 በላይ የሚሆኑት በመጠለያ ካምፕ ውስጥ ናቸው።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ፣ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ዕርዳታ ለተረጂዎች እየቀረበ ባለመሆኑ ወደ 400,000 የሚጠጉ በጋምቤላ ክልል ውስጥ በካምፕ የሚገኙ ስደተኞች ሕይወት አደጋ ውስጥ መውደቁን ገልጾ አፋጣኝ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠይቋል፡፡

በጋምቤላ ክልል ከግንቦት 2015 ዓ.ም. ወር ጀምሮ ዕርዳታ ያላገኙ ስደተኞች (አብዛኞቹ ከደ/ሱዳን የተሰደዱ) በምግብ እጥረት የተነሳ በሚመጣ ረሃብ ለሞትና ለከፋ ሕመም እየተጋለጡ መሆናቸውን አረጋግጧል።

ኮሚሽኑ ከስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ተቋም አገኘሁት ባለው መረጃ በምግብ እጥረት ምክንያት በጋምቤላ ብቻ 30 ሰዎች መሞታቸውን፣ 5 ዓመት ያልሞላቸው ሕፃናት ለከፋ ሕመም መጋለጣቸውን አስታውቋል፡፡

በተከሰተው የምግብ እጥረት የተነሳ ከስደተኞች መጠለያ ካምፕ ወጥተው ወደ ማኅበረሰቡ በሚገቡበት ወቅት ለሰላም ችግር መንስዔ መሆናቸው በኮሚሽኑ ሪፖርት የተገለጸ ሲሆን፣ ከመጠለያ ወጥተው በምግብ ስርቆት በመሰማራታቸውና ከቆሻሻ ላይ ምግብ ለማንሳት ሲጥሩ ሕይወታቸው ያለፉ መኖራቸውንም አስታውቋል፡፡

አሁን ላይ በርካታ ስደተኞች አደጋ ላይ በመሆናቸው የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትም ሆኑ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅቶች አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጡ ኢሰመኮ አሳስቧል።

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
" ኢትዮጵያ ውሉ በጠፋና ተለዋዋጭ በሆነ ጊዜ ውስጥ ናት " - ጥናት

አገር በቀሉ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ተቋም የማኅበራዊ ጥናት መድረክ (ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ) ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው ጥናት ኢትዮጵያ ውሉ በጠፋና ተለዋዋጭ በሆነ ጊዜ ውስጥ እንደምትገኝ ገለጸ፡፡ 

ይፋ ባደረገው ጥናቱ የኢትዮጵያን ወቅታዊና የወደፊት መፃዒ ሁኔታ ዳሷል፡፡

"ኢትዮጵያ ወዴት? ቢሆንታዎች" በሚል ርዕስ የቀረበው ይኼው ጥናት የአገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ መንገራገጭ፣ የሐምሌ ጨለማና ፀደይ በማለት በሦስት ቢሆንታዎች (Scenarios) ለማስቀመጥ የሞከረ ነበር፡፡

የቢሆንታዎችን ምንነትን ወደኋላ በመመለስ ከታሪካዊ ዳራ ተነስቶ ብይን ለመስጠት የሚሞክረው ጥናቱ፣ የወቅቱን የአገሪቱን ሁኔታም ፍቺ ለመስጠት ሞክሯል፡፡

" በአንድ ማኅበረሰብ የመንግሥት ተዓማኒነት እየተሽከረከረ ሲሄድ፣ ማኅበረሰባዊ ትስስር ሲመነምንና በሕዝብ ዘንድ የፍትሕ መጓደል/ ተበዳይነት ስሜቶች ሲያንዣብቡ #ጽንፈኝነት ይነግሣል " በማለት ነው ይኸው ጥናት የኢትዮጵያን ገጽታ በማስቀመጥ ወደ ሐተታው የሚንደረደረው።

ጥናቱ በአሁኗ ኢትዮጵያ እነዚህ ሁሉ ሁኔታዎች እንደሚታዩ ገልጾ ፖለቲካዊ መግባባት በአገሪቱ መፍጠር ከምንም በላይ አስፈላጊ መሆኑን ያሰምርበታል፡፡

ያም ቢሆን ግን ባለፉት 50 ዓመታት በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች ችግሮችን ተወያይቶ የመፍታት ባህል አለመዳበሩ ትልቁ ራስ ምታት እንደሆነ ያወሳል፡፡

በዘውዳዊው ሥርዓት መውደቅ ማግሥት አምባገነናዊ ሥርዓት በኢትዮጵያ በማቆጥቆጡ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ተስፋው መምከኑን ያስረዳል፡፡

ደርግ ወድቆ በ1983 ዓ/ም የመንግሥት ለውጥ ሲደረግ " የሕዝቦች እኩልነት ይፈጠራል " የሚል ተስፋ መፈጠሩን ይሁን እንጂ ይህንን ለውጥ ተከትሎ የተቀረፀው ሕገ መንግሥት የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት ይፈጥራል ቢባልም ነገር ግን በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የጭቅጭቅ ምዕራፍ መክፈቱን ያትታል፡፡

በየታሪክ ምዕራፉ ለዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ሽግግር ተስፋ የፈነጠቁ አጋጣሚዎችን አለፍ ገደም እያለ የሚዘረዝረው ጥናቱ፣ በ2010 ዓ.ም. የተፈጠረውን የፖለቲካ ለውጥ እንደ አንዱ አጋጣሚ ያነሳዋል፡፡ 

" ለውጡ ከፈጠረው ከፍተኛ የሕዝብ ፈንጠዚያ ጀርባ ግን በለውጥ አቀንቃኞችና በቀድሞ ሥርዓት ናፋቂዎች መካከል ውስጥ ውስጡን ውጥረት ሰፈነ " ይላል፡፡

የአዲስ ተስፋው ፍንጣቂ በለውጡ  ማግሥት ብዙም ሳይዘገይ በመጣው " የነውጥ ጊዜ " እንደተተካም ነው ጥናት ያመላከተው፡፡

የኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ታሪክ በብዙ ፈታኝ ውጣ ውረዶች ውስጥ የማለፍ አስገራሚ ፅናት የተላበሰ መሆኑን ጥናቱ ያብራራል፡፡

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ባህል ግን ፈላጭ ቆራጭነት የሰፈነበት ሆኖ መቆየቱን ይገልጻል። በኢኮኖሚውም መስክ በአስከፊ ድህነት ውስጥ አገሪቱ ተዘፍቃ መኖሯን ያትታል፡፡

ከዚህ ሁሉ ተነስቶ አገሪቱ የሐምሌ ጨለማ፣ መንገጫገጭና ፀደይ የሚል ስም የተሰጣቸው ቢሆንታዎችን ልታስተናግድ እንደምትችል ሰፊ ትንተና ያቀርባል፡፡

በሌላ በኩል የመበታተን አደጋን እንደ አንድ ቢሆንታ ያነሳዋል። " አስደንጋጭ ቢሆንም የአገሪቱ የመበታተን አደጋ የማይታሰብ ነው ለማለት አይቻልም " ሲል ነው ጥናቱ ያብራራው።

ጥናቱ ከአፍሪካ ቀንድ ሁኔታ እስከ አየር ንብረት ለውጥ #ከሃይማኖት እና #ፖለቲካ ፅንፈኝነት እስከ የብሔርና ያልተማከለ አስተዳደር ውጥረት አገሪቱን ሊፈትኑ የሚችሉ ነጥቦችን ይፈትሻል፡፡

ከኢኮኖሚ አለመረጋጋት እስከ የዋጋ ንረት ውጣ ውረዶንችም ያነሳል፡፡

በሌላ በኩል፤ የአማራ ክልልና አገሪቱን ወጥረው የያዙ በየአቅጣጫው ያሉ የግጭት ሁኔታዎችን ተፅዕኖም የፈተሸ ነው። #ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#ኮንትሮባንድ

የመንግሥት ሆኑ ሌሎች በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ተቋማት ለኮንትሮባንድ ንግድ መቆም መፍትሔ ከመሆን ይልቅ፣ ሕገወጥ ንግድን የሚያባብሱ ሆነው አግኝተናቸዋል ሲሉ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኃላፊዎች ገለጹ፡፡

በየአካባቢው ያሉ ተቋማት በኮንትሮባንድ ዙሪያ የሚያከናውኑትን በሚመለከት ሲያስረዱ፣ ድርጊቱን በመቃወም አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የመንግሥትና ሌሎች አካላት እንዳሉ ሁሉ፣ " ከችግሩ ጋር አብረው የሚኖሩና የሚተገብሩም " እንዳሉ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ ተናግረዋል፡፡

የተቋማቱን ስምና አድራሻ ሳይገልጹ እነዚህ ተቋማት ምንም እንኳን ዕርምጃ እየተወሰደባቸው ቢሆንም፣ የኮንትሮባንዲስቶቹ አካልና ተባባሪ ሆነው እየሠሩ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡

" ሁኔታ የሚያመቻቹ፣ የሚያሳልፉ፣ መረጃ የሚሰጡ፣ ሕገወጦችን የሚከላከሉላቸው፣ የሚደብቁ፣ እንዳይያዙና እንዳይመረመሩ የሚያደርጉ፣ ዕቃዎቻቸውን በሽፋን የሚያሳልፉ፣ ሐሰተኛ ሰነድ በመሥራት የሚተባበሩ… " ሲሉ አቶ ደበሌ በሕገወጥ ንግድ ላይ " ቀላል ቁጥር የሌላቸው " ተቋማት እንዴት እንደሚሳተፉ አብራርተዋል፡፡

ስለኮንትሮባንድና ሕገወጥ ንግድ ሲነገር እነዚህ ችግሮች በበርካታ ተቋማት እንደሚፈጸሙ፣ ወደታችኛው የአስተዳደር አካል ሲወረድ ደግሞ ችግሮቹ " በጣም በከፍተኛ ደረጃ እየሰፉ ነው " ሲሉ ኮሚሽነሩ ይገልጻሉ፡፡

ችግሩን በመቃወም አስተዋጽኦ እያበረከቱ ካሉ ተቋማት መካከል፣ ከጉምሩክ ኮሚሽንና ከገቢዎች ሚኒስቴር በተጨማሪ የፌዴራል ፖሊስ፣ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ ዓቃቢያነ ሕጎች፣ የክልል የፀጥታ አካላትና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እንደሚገኝበት አስረድተዋል፡፡

ኮንትሮባንዲስቶች ሊጠቀሙባቸው የሚችሏቸው በርካታ መንገዶች እንዳሉ ሁሉ፣ ከሁለት ሺሕ ኪሎ ሜትር በላይ የሚረዝመውን ከምሥራቅ ኢትዮጵያ ክፍል እስከ ኬንያ ድንበር ድረስ ያለውን ሥፍራም ለዝውውር እንደሚጠቀሙበት ተገልጿል፡፡

በችግሮቹ ግዝፈትና አስከፊነት ልክ አቅም ያላቸው ተቋማትን መገንባት አንደኛው ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ፣ እንደ ሕግ አስከባሪ ዓይነት ተቋማትንም በሚገባ ማደራጀት እንደሚያስፈልግ ኮሚሽነሩ አውስተዋል፡፡

አቅምን ከመገንባት ባለፈም የሚወሰደው ዕርምጃ ትልቅ ሊሆን እንደሚገባና ከዚህ በፊት የተወዱት ዕርምጃዎችም ጥሩ እንደሆኑ ሲገልጹ፣ በተጠናቀቀው ዓመት ብቻ እስከ 80 ቢሊዮን ብር የተገመቱ የተለያዩ የኮንትሮባንድ ቁሳቁሶች እንደተያዙ ገልጸዋል፡፡

" ይህ ቁጥር የሕገወጥነትን ጉልበት በልኩ የሚናገር፣ የተወሰደውን ዕርምጃ በልኩ የሚናገር፣ ቀጣይ ምን መሥራት እንደሚገባንም የሚናገር ነው " ሲሉ አቶ ደበሌ ቃበታ ከሰሞኑን መናገራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። #ሪፖርተር

@tikvahethiopia