TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በኤርትራ የነበሩት የአርበኞች ግንቦት 7 ታጣቂዎች ኢትዮጵያ ሲገቡ ለግዜው ከመንግስት በኩል በተዘጋጀላቸው #አምስት ካምፖች ይቀመጣሉ ተብሏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሟቾች ቁጥር 21 ደረሰ‼️

በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ በሚገኝ ባለ አምስት ኮከቡ ዱሲት ዲ2 ሆቴልና የንግድ ማዕከል ባሳለፍነው ማክሰኞ #በታጠቁ_ኃይሎች በተፈጸመው ጥቃት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 21 ደርሷል።

ጥቃቱ ከተከፈተበት ቅንጡ ሆቴልና የገበያ ማዕከል በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ጉዳት ሳይደርስባቸው የወጡ ሲሆን 28 ሰዎች ቆስለዋል። የኬንያ ቀይ መስቀል ማህበር እንዳስታወቀው 19 ሰዎች እስካሁን የገቡበት አልታወቀም።

አልሸባብ እጄ አለበት ያለውን ጥቃት ለመቆጣጠር የፀጥታ ኃይሎች 19 ሰዓታት ወስዶባቸዋል።

የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ትናንት በበብሔራዊ ቴሌቪዥን ባደረጉት ንግግር ጥቃተን የፈፀሙት #አምስት ታጣቂዎችን #በመግደል የኦፕሬሽን ስራው #መጠናቀቁን ተናግረዋል።

ከጥቃቱ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የተጠረጠሩ ሁለት ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።

ኬንያ አልሸባብን ለመዋጋት ወታደሮቿን ወደ ሶማሊያ ከላከችበትከፈረንጆቹ 2011 ጥቅምት ጀምሮ የሽብር ቡድኑ የጥቃት ዒላማ ሆናለች።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኦነግ/WBO‼️

የ'ኦነግ' የቅበላ ቀነ ገደብ ተጠናቋል!
(*የልዩ ሁነት #አምስት የመጨረሻ ቀናት አሉ)
.
.
ከመንግሥት ጋር በተፈጠረው ያለመግባባት ዳግም በውጊያና የተለያዩ ግጭቶች ላይ የቆየው የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት የከበረውን የገዳ ሥርዓት መርሖዎችና ሕጎች መሰረት አድርጎ ለቀረበው ጥሪና የሰላም አዋጅ ላለፉት ሶስት ቀናት ሲደረግለት የቆየው አቀባበል ትላንት ምሽት 12:00 ላይ መጠናቀቁን የእርቀ ሰላሙ የቴክኒክ ኮሚቴ ይፋ አድርጓል።

በመንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት መካከል እርቀ ሰላም ለማውረድ፤ በኦሮሚያ አባገዳዎች፣ በሀደ ሲንቄዎች(Haadha Siinqee)፣ በአገር ሽማግሌዎች፣ በምሁራንና ለሰላም መስፈን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያደርጉ በቆዩ በርካታ ዜጎች እንቅስቃሴ ጥረቱ መልካም ፍሬ አፍርቶ #በጫካ የነበረው ሠራዊት ላላፉት ሦስት ቀናት በኦሮሚያ 12 ዞኖችና 22 ወረዳዎች አቀባበል ሲደረግለት ቆይቷል።

ጥር 14 ቀን 2011 ዓ.ም በአምቦ ዩኒቨርሲቲ በአባገዳዎች #የሰላም_አዋጅ ታውጆ የእርቀ ሰላም ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን ጥሪው በጎ ምላሽ አግኝቶ ሠራዊቱ መሳርያውን ለአባገዳዎችና ለቴክኒክ ኮሚቴው በማስረከብ ባሕላዊ አቀባበል፣ ባርኮት(Muuda) እና ፍቅራዊ ክብካቤ እየተደረገለት ቆይቷል።

ከነገ ጀምሮም በተዘጋጀለት ካምፕ በመግባት በሰላም ተጠሪዎች፣ በሕግ ባለሙያዎች እና በሌሎች ምሁራን የተለያዩ ስልጠናዎች መውሰድ ይጀምራል። ከሁለት ወር በማይበልጠው በዚህ ቆይታ የሠራዊቱ አባላት እንደየፍላጎታቸው እና ችሎታቸው ስልጠና ወስደው በመስካቸው የሚመደቡ ሲሆን በቆይታቸውም በአባገዳዎች፣ በቴክኒክ ኮሚቴው አባላትና በሰላም ተጠሪዎች አያያዛቸው የሚጎበኝ ይሆናል።

እስካሁን በነበረው ሂደትና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የቴክኒክ ኮሚቴው የፊታችን እሁድ ተገናኝቶ አጠቃላይ ምክክርና ግምገማ የሚያደርግ ሲሆን ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በተያያዘ ዜና -- በ'ልዩ ሁነት' በቀነ ገደቡ መግባት ላልቻሉ የሠራዊቱ አባላት ተጨማሪ #አምስት ቀን የተሰጠ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በየወረዳው የሰላም ክፍሎች በመገኘት #መሳርያቸውን ማስረከብና ወደካምፕ ገብተው ለቀጣይ ሰላማዊ ሕይወታቸው ጠቃሚ የሆኑትን #ስልጠናዎች መውሰድ እንደሚችሉ ተገልጿል።

Via Gulale Post
@tsegabwolde @tikvahethiopia
107 ፓርቲዎች

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ እባካችሁ ተዋሃዱ ብሎ ሲማፀናቸው የነበሩት ወደ ሰማንያ (80) አካባቢ የሚገመቱ ፓርቲዎች በጥቂት ወራት ውስጥ 107 ደርሰዋል።
--
ከ 107ቱ ውስጥ ሰላሳ ሶስቱ (33) "#ኢትዮጵያ "ን በፓርቲያቸው ስያሜ ውስጥ ተጠቅመዋል። #አማራ የሚል ስያሜአቸው ውስጥ ያላቸው
#አምስት ሲሆኑ #አስራ_ሶስቱ ደግሞ #የኦሮሚያ ፓርቲዎች ናቸው። እነ አንዳርጋቸው ፅጌ ብዙ ጊዜ ክፍፍል ያለው "በዘውግ" የተደራጁ ፓርቲዎች ላይ ነው ቢሉም በኢትዮጵያዊነት ስም የተደራጁት 33 ፓርቲዎች ራሱ ተቀራርበው መዋሃድ አልቻሉም። #ሰማያዊ_ፓርቲ ለምሳሌ #ከአግ7ጋር ተዋህዶ ፈርሷል ቢባልም ዝርዝሩ ውስጥ ተካቷል።
--
ኢህአዴግ እንደ ግንባርም በተናጠልም የፈረመበት ምክንያት ግራ ያጋባል። በዛ ላይ የተፈረመበት ሰነድ ላይ አዴፓ እና ኦዴፓ ሳይሆን #ብአዴን እና #ኦህዴድ ነው የሚለው። አንድ ወጥ ሀገር አቀፍ ፓርቲ ሆነው በድጋሚ ለመመዝገብ ነው ለስያሜው እንኳን ቸልተኛ የሆኑት?
--
ለማንኛውም ሰማንያ አካባቢ ፓርቲ የተሳተፈበት የ 1997 (2005) ምርጫ ላይ የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ያሸነፉት ፓርቲዎች ከላይ ያሉት ነበሩ። በርካቶቹ አንድም መቀመጫ እንዳላገኙ የሚታወቅ ነው።

Via THE FINFINNE INTERCEPT
@tsegabwolde @tikvahethiopia