107 ፓርቲዎች

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ እባካችሁ ተዋሃዱ ብሎ ሲማፀናቸው የነበሩት ወደ ሰማንያ (80) አካባቢ የሚገመቱ ፓርቲዎች በጥቂት ወራት ውስጥ 107 ደርሰዋል።
--
ከ 107ቱ ውስጥ ሰላሳ ሶስቱ (33) "#ኢትዮጵያ "ን በፓርቲያቸው ስያሜ ውስጥ ተጠቅመዋል። #አማራ የሚል ስያሜአቸው ውስጥ ያላቸው
#አምስት ሲሆኑ #አስራ_ሶስቱ ደግሞ #የኦሮሚያ ፓርቲዎች ናቸው። እነ አንዳርጋቸው ፅጌ ብዙ ጊዜ ክፍፍል ያለው "በዘውግ" የተደራጁ ፓርቲዎች ላይ ነው ቢሉም በኢትዮጵያዊነት ስም የተደራጁት 33 ፓርቲዎች ራሱ ተቀራርበው መዋሃድ አልቻሉም። #ሰማያዊ_ፓርቲ ለምሳሌ #ከአግ7ጋር ተዋህዶ ፈርሷል ቢባልም ዝርዝሩ ውስጥ ተካቷል።
--
ኢህአዴግ እንደ ግንባርም በተናጠልም የፈረመበት ምክንያት ግራ ያጋባል። በዛ ላይ የተፈረመበት ሰነድ ላይ አዴፓ እና ኦዴፓ ሳይሆን #ብአዴን እና #ኦህዴድ ነው የሚለው። አንድ ወጥ ሀገር አቀፍ ፓርቲ ሆነው በድጋሚ ለመመዝገብ ነው ለስያሜው እንኳን ቸልተኛ የሆኑት?
--
ለማንኛውም ሰማንያ አካባቢ ፓርቲ የተሳተፈበት የ 1997 (2005) ምርጫ ላይ የክልል ምክር ቤት መቀመጫ ያሸነፉት ፓርቲዎች ከላይ ያሉት ነበሩ። በርካቶቹ አንድም መቀመጫ እንዳላገኙ የሚታወቅ ነው።

Via THE FINFINNE INTERCEPT
@tsegabwolde @tikvahethiopia