TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Alert ቴፒ‼️

በቴፒ ከተማ ከትንላንት ጀምሮ ዳግም #ያገረሸው #አለመረጋጋት ዛሬም ቀጥሏል። ዛሬም በተለያዩ የከተማይቱ አካባቢዎች ተደጋጋሚ የጥይት ድምፅ እየተሰማ እንደሚገኝ በከተማው የሚኖሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል። ነዋሪዎች በከተማው ያለው ውጥረት ወደ ሌላ ደረጃ ሳይሸጋገር የኢትዮጵያ መንግስት መፍትሄ እንዲፈልግ ጠይቀዋል። ከትላንት ጀምሮ በተፈጠረው አለመረጋጋት ሳቢያ ስለደረሰው ጉዳት የተረጋገጡ መረጃዎችን ሳገኝ ወደእናተ አደርሳለሁ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 23/2011 ዓ.ም.

ከትራንስፓርት ሚንስቴርና ከሌሎች ሚንስቴር መስሪያ ቤቶች የተወጣጣው የሉኡካን ቡድን የጅቡቲ ወደብን ጎብኝቷል።
.
.
ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ በምዕራብ እንዲሁም ምሥራቅ ጉጂ በኢትዮጵያ መከላከያ ኃይልና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ታጣቂዎች መካከል በታካሄደ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን በርካቶች ከቤታቸው መፈናቀላቸው ተናግረዋል።
.
.
ከአመት በፊት ሳውዲ አረቢያ ጀምራው የነበረውን መጠነ ሰፊ የፀረ-ሙስና ዘመቻ እንዳጠናቀቀች አስታውቃለች፡፡ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት 100 ቢሊዮን ዶላር በጥሬ ገንዘብ እና በቁስ መልክ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ሰዎች መሰብሰቡን አስታውቋል።
.
.
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ የፀደቀውን #የስደተኞች_አዋጅ በመቃወም ነገ በጋምቤላ ከተማ ሊደረግ ለታሰበው የተቃውሞ ሰልፍ ፈቃድ #ከልክሏል
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ6 ሺህ ነጋዴዎች ግብር ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ ግብር ስረዛው ከ2003 እስከ 2010 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከፍተኛ የግብር ተመን ተጥሎባቸው አቤቱታ ሲያቀርቡ የቆዩትን ነጋዴዎች ያካትታል፡፡
.
.
4ኛው የህዝብና ቤት ቆጠራ ከመጋቢት 29 ቀን ጀምሮ ይካሄዳል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህግን ተከትለው የሚሰሩ የሪል ስቴት አልሚዎችን እንደሚደግፍ ነገር ግን ህገወጥ የሆኑት ላይ #ዕርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ወረዳ በጫነው አሸዋ ላይ 31 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ ተገልብጦ የሰዎች ህይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
.
.
በቴፒ ከተማ ከትንላንት ጀምሮ ዳግም #ያገረሸው #አለመረጋጋት ዛሬም ቀጥሏል። የንግድ እና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተቋርጦ ውሏል። ከተማዋ በፀጥታ ሃይሎች በከፍተኛ ደረጃ እየተጠበቀች ነው።
.
.
ዛሬ በስራ ላይ የሚውለውን የነዳጅ ዋጋ መጨመር ተከትሎ ምንም አይነት #የትራንስፖርት_ታሪፍ  ጭማሪ #እንደማይኖር የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ገልጿል።
.
.
ጅቡቲ በተካሄደው 15ኛው የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ የተካፈሉ የኢትዮጵያ ልዑካን ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያይተዋል።
.
.
በኦሮሚያ ክልል ለመንግስት ሰራተኞች #አዲስ የስራ ምደባ እየካሄደ መሆኑን የክልሉ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።
.
.
#ኮማንድ_ፖስቱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 3 ወረዳዎች ላይ በቁጥጥር ስር ካዋላቸዉ 528 ተጠርጣሪዎች 440 የሚሆኑትን በነፃ አሰናብቷል።
.
.
የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ የሆነው ከአዋሽ እስከ ኮምቦልቻ ያለው 270 ኪሎ ሜትር የባቡር መንገድ ግንባታ 97 በመቶ #መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ገልጿል።
.
.
በሱማሌ ክልል ከምሽቱ 4 ሰዓት ጀምሮ ሰዓት ዕላፊ ገደብ ተጥሏል፡፡ የአደባባይ ስብሰባም ተከልክሏል፡፡
.
.
#ቴዎድሮስ_አዲሱ(ቴዲ ማንጁስ) በ80 ሺህ ብር ዋስ ቢፈቀድለትም #በሙስና_ወንጀል ተጠርጥሮ በእስር ላይ እንደሚገኝ ተሰምቷል።
.
.
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ለሚያልፉ ዐለም ዐቀፍ መንገደኞች #የነጻ ጉብኝት መርሃ ግብር ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡
.
.
የኢትዮጵያ ሚዲያ ካውንስል፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ዘርፍ ማህበር እና #የሰላም_ሚኒስቴር በጋራ በመሆን የሰላም ሚዲያ ህብረት ትስሰር ለመፍጠር የሚያስችል ውይይት ዛሬ ማምሻውን አካሂደዋል።
.
.
የሐረሪ ክልል የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ #መሻሻል ማሳየቱን የክልሉ ፍትህና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ  አስታውቋል።
.
.
#ብሄሬን መሰረት ተደርጎ ጥቃት ተፈፅሞብኛል በሚል በሀሰት የሽንት መሽኛ #ብልቱን በፋሻና ፕላስተር በመጠቅለል ግጭት ለመቀስቀስ የሞከረው ግለስብ ድሬ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ በዳቦ ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ አግባብነት የሌለውና ህብረተሰቡን ያላማከለ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
.
.
በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አንድ #ኢትዮጵያዊ በእስራኤል ፖሊስ መገደሉን በመቃወም ቴላቪቭ ውስጥ ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።
.
.
በአሜሪካ በተከሰተው ከፍተኛ ቅዝቃዜ እስካሁን ቢያንስ ስምንት ሰዎች #መሞታቸው ተገለጸ፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በአሜሪካ ሜድ ዌስት የተከሰተው ቅዝቃዜ በአስር አመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ አደገኛ ነው፡፡
.
.
ምንጭ፦ etv፣ የጀርመን ራድዮ፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ ዋዜማ ራድዮ፣ fbc፣ ኢዜአ፣ bbc፣ VOA፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምዕራብ ወለጋ‼️

በምዕራብ ወለጋ ዞን በነበረው #አለመረጋጋት የተዘረፉ የጦር መሣሪያዎችና ንብረት #ተመለሱ። በዞኑ ሁሉም የመንግሥት መዋቅሮችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ መደበኛ ሥራቸው መመለሳቸውም ተገልጿል።

የኮማንድ ፖስቱ ጽህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ #ደጀኔ_ገብረማርያም እንደገለጹት በዞኑ በነበረው የፀጥታ ችግር የተዘረፉ የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ንብረት ተመልሰዋል። ከነዚህም 110 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች፣ 41ሽጉጦችና 20 የእጅ ቦምቦች ይገኙበታል። እንዲሁም 326 ኋላ ቀር ጠመንጃዎችና ከአራት ሺህ የሚበልጡ ጥይቶች መመለሳቸውን አስረድተዋል።

በተጨማሪም 50 በርሜል ነዳጅ፣ 14 የመንግሥትና የግል ተሽከርካሪዎችና 28 የሞተር ቢስክሌቶች መመለሳቸውን አቶ ደጀኔ ተናግረዋል።

የዞኑ ሕዝብ የተዘረፉትን የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ንብረት ለማስመለስ በተደረገው ጥረት ከፀጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው መንቀሳቀሱን ገልጸዋል።

በዞኑ በ20 የገጠር ወረዳዎችና ሦስት ከተሞች በተካሄዱት የሰላም ኮንፈረንሶች አንፃራዊ #ሠላም በመስፈኑ ሁሉም የመንግሥት መዋቅሮችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ መደበኛ ሥራቸው መመለሳቸውን አስተባባሪው አስረድተዋል፡፡ በካማሺና የምዕራብ ወለጋ ዞኖች መካከል የሕዝብ ለሕዝብ እንቅስቃሴ መጀመሩንም አመልክተዋል፡፡

የመነ ሲቡ ወረዳ የአስተዳደርና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ #ለታ_አባተ በሰጡት አስተያየት ሕዝቡና ኮማንድ ፖስቱ ባደረጉት ክትትልና ቁጥጥር የጦር መሣሪያዎቹ መመለሳቸው ለዞኑ ሰላምና ጸጥታ መከበር አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል፡፡ አሁንም ያልተመለሱትን የጦር መሣሪያዎች ለማስመለስ ተቀናጅቶ እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡

የመንዲ ከተማ የአስተዳርና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ #ዳኖ_ኢተፋ በበኩላቸው የተዘረፉት የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ንብረት መመለሳቸው ለሰላም ያላቸው ፋይዳው ጉልህ ነው ብለዋል። የምዕራብ ኢትዮጵያ ከዚህ ዓመት መግቢያ ጀምሮ በተከሰተው ግጭት ሰላምና ጸጥታው ታውኮ መቆየቱ ይታወሳል።

Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞የካቲት 12/2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ሰማዕታት ቀን 82ኛ ዓመት የመታሰቢያ ስነ ስርዓት በዛሬው እለት ተካሂዷል። መታሰቢያ ስነ ስርዓቱ በተለይ 6 ኪሎ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሰማእታት አደባባይ ከማለዳው ጀምሮ በተለያዩ ስነ ስርዓቶች ነው የተካሄደው።
.
.
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከጣልያኑ ትጥቅ አምራች ኩባንያ ኤሬአ ጋር የነበረውን ስምምነት ቀይሮ ከእንግሊዙ አምብሮ ኩባንያ ጋር የአራት አመት የትጥቅ ልብስ ማቅረብ ስምምነት ተፈራርሟል።
.
.
በአማራ ክልል የተፈናቀሉ ወገኖችን ለማቋቋም የክልሉ መንግስት ያደረገውን ጥሪ ተከትሎ #ጥረት_ኮርፖሬሽን የ10 ሚሊዮን ብር የመጀመሪያ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል።
.
.
ግሎባል አልያንስ ከምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር #ለተፈናቀሉ 46ሺ ለሚሆኑ ዜጎች 20ሺ የአሜሪካን ዶላር ወይንም በኢትዮጵያ 6 መቶ ሺ ብር #መለገሱን አስታውቋል።
.
.
በፌደራል ስርዓቱ ላይ ከማንም ጋር #ለድርድር እንደማይቀመጥ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዲፒ) አስታውቋል። ፓርቲው በትናነትናው እለት ባወጣው መግለጫው፥ ኦዲፒ በአጀንዳነት ይዞ ከሚታገልባቸው ጉዳዮች ውስጥ ዋነኛው የፌደራል ስርዓቱ ነው ብሏል።
.
.
በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን #ያአበሎ_ወረዳ በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ ከ15 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል።
.
.
“ጉዞ ሉሲ ለሰላምና ለፍቅር” የሽኝት መርሃ ግብር ከነገ በስቲያ በይፋ እንደሚካሄድ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታውቋል።
.
.
ከነገ በስቲያ/ሀሙስ የካቲት 14/2011 ዓ.ም. የሲዳማ ሪፈረንደም ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ በሀዋሳ ከተማ የጠራው #ሰላማዊ_ሰልፍ በመንግስት ፍቃድ አግኝቷል።
.
.
ጥቅምት 4/2011 ዓ/ም ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (#ቴዲ_አፍሮ) በሚሊኒየም አዳራሽ ያቀረበው የሙዚቃ ዝግጅት ደረጃውን በጠበቀ የድምፅ እና የምስል ጥራት #በዲቪዲ የፊታችን ቅዳሜ የካቲት 16 ለገበያ ይቀርባል ተብሏል።
.
.
#የኤርትራ ፐብሊክ ዲፕሎማሲና የባህል ልኡክ አባላት #ከሀዋሳ_ከተማ ነዋሪዎች ጋር #ተወያይተዋል
.
.
ድሬዳዋ ውስጥ በዓመት 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቶን ማዳበሪያ የሚያመርት ፋብሪካ #ሊገነባ መሆኑን የኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ተገልጿል።
.
.
#ቂሊንጦ_ማረሚያ_ቤት ላይ በደረሰው ቃጠሎ በተነሳው ረብሻ ምክንያት የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈፅመዋል በሚል የተጠረጠሩ የማረሚያ ቤት የፖሊስ አባላት ላይ ክስ ተመስርቷል።
.
.
በኢፌዲሪ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የሁለተኛ ዙር የ100 ቀን ዕቅድ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተርሩ አቶ #ዝናቡ_ቱኑ አስታውቀዋል።
.
.
የሱማሊያ ጫት ነጋዴዎች ከኬንያ ጫት ማስገባታቸውን ትተው #የኢትዮጵያን_ጫት ለመግዛት መወሰናቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኻን ዘግበዋል፡፡
.
.
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር #ወርቅነህ_ገበየሁ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባደሳደር ዶ/ር #አላስቴይር_ዲቪድ ማክፌይል በዛሬው ዕለት የካቲት 12 ቀን 2011 ዓ.ም በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
.
.
በምዕራብ ወለጋ ዞን በነበረው #አለመረጋጋት የተዘረፉ የጦር መሣሪያዎችና ንብረቶች #ተመለሱ። በዞኑ ሁሉም የመንግሥት መዋቅሮችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ መደበኛ ሥራቸው መመለሳቸውም ተገልጿል።
.
.
የለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር በህገወጥ መንገድ ተገንብተዋል ያላቸውን መኖሪያቤቶች ማፍረስ ጀምሯል።
.
.
በምዕራብ ወለጋ ዞን የኦነግ አባላት ህዝቡን #እየተቀላቀሉ ሲሆን፣ በዞኑ፣ መነ ሲቡ ወረዳ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል።
.
.
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ብሄራዊ አስተባባሪ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት እና በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በጋራ የተዘጋጀው የእግር ኳስ ውድድር ከየካቲት 22 እስከ 24 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

ምንጭ፦ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ fbc፣ etv፣ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት፣ wazemaradio፣ የጀርመን ራድዮ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሸዋሮቢት~መንገዶች ተከፍተዋል‼️

በሸዋሮቢት ከተማ የተከስቶ የነበረው #አለመረጋጋት በአሁኑ ሰዓት ወደ ነበረበት እየተመለሰ መሆኑን የሸዋሮቢት ከተማ ከንቲባ አቶ #አካሉ_ወንድሙ ተናገሩ።

እንደ ከንቲባው ገለጻ በአሁኑ ሰዓት የተዘጉ መንገዶች #ተከፍተው የጸጥታ ሀያሉ እና የአካባቢው ማህበረሰብ መንገደኞችን #በመሸኘት ላይ መሆናቸውን ተናግረው የሸዋሮቢት ከተማ ህዝብ #መቻቻልና #መረዳዳት ባህሉና ወጉ የሆነው ህዝባችን ድርቶችን ሁሉ በተለመደውን የችግር መፍቻ መንገዶችን፣ ህግን በማክበርና በማስከበር ስራ ላይ #ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የጸጥታ ሀይሉ፣ የሀይማኖት አባቶች እና ሀገር ሽማግሌዎች ከተማውን #ለማረጋጋት ላያደረጉት ጥረት ምስጋና አቅርበዋል። በአሁኑ ሰዓት ሽዋሮቢት ወደነበረችበት #ሰላምና መረጋጋት እየተመለሰች መሆኑን ከንቲባው ተናግረዋል።

Via Shewa Robit City Administration Kentiba office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሸዋሮቢት ከተማ ፖሊስ‼️

ትላንት በሸዋሮቢት ከተማ ተፈጥሮ የነበረው #አለመረጋጋት ሙሉ በሙሉ ተወግዶ ዛሬ ሸዋሮቢት ወደነበረው ሰላሟ ተመልሳ ማህበረሰቡ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ መሆኑን #የሸዋሮቢት_ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡ የጽ/ቤቱ ኃላፊ ኢንስፔክተር #ሞገስ_ባየህ እንደገለፁት ማህበረሰቡ በአሁን ሰአት በተሰማራበት የስራ መስክ በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ጠቅሰው በከተማው አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ሙሉ በሙሉ በስራ ላይ ናቸው ብለዋል፡፡ #ከጉዳት_መጠን ጋር ተያይዞ #የሚናፈሱ አሉባልታዎች መሰረተ-ቢስ ናቸው በሰው ህይወት ላይም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት #የለም ስለዚህ ማህበረሰቡ ከአሉባልታ በፀዳ መንገድ የተለመደ ተግባሩን ማከናወን እንዳለበት ፖሊስ አስታውቀዋል፡፡

Via Shewa Robit City Administration Kentiba office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቬንዙዌላ ድንበሯን ዘጋች‼️

የቬንዙዌላ ፕሬዘዳንት #ኒኮላስ_ማዱሮ #በሰብዓዊነት ስም በተቃዋሚ ፓርቲዎች አማካኝነት ከአሜሪካ የሚደረገውን እርዳታ ለማስቆም አገራቸው #ከብራዚል ጋር የሚያዋስናትን ድንበር መዝጋቷን አስታወቁ፡፡

በዚህ ምክንያትም በርካታ ተሽከርካሪዎች በሁለቱ አገራት ድንበር ላይ ቆመው እንዳሉም ተገልጿል።

ፕሬዘዳንቱ በአገራቸው ከመንግስት አቅም በላይ የሆነ ሰብዓዊ ቀውስ እንደሌለና ምንም አይነት የእርዳታ ጥሪም እንዳልተደረገ ገልፀዋል፡፡

በአገሪቱ በተፈጠረው #አለመረጋጋት አጣብቂኝ ውስጥ የሚገኘው ግራ ዘመሙ መሪ #ማዱሮ በአገሪቱ የቴሌቭዥን ጣቢያ ወጥተው እንደገለፁት የተቃዋሚ መሪዎች በሰብዓዊ እርዳታ ስም ከአሜሪካና ሌሎች አጋሮቿ የሚላከውን ለማስቆም የኮሎንቢያ ድንበርንም ጨምረው እንደሚዘጉ ገልፀዋል፡፡

ይህን ተከትሎም የተቃዋሚ ፓርቲ መሪው ጁዓን ገይዱ በበርካታ አውቶቡሶችና ሌሎች ተሽከርካሪዎች ታጅቦ ከቬንዙዌላ ዋና ከተማ ካራካስ ወደ #ኮሎንቢያ ድንበር ማቅናታቸው ተገልጿል፡፡

በቅርቡ የተካሄደውን ምርጫ ተከትሎ በአገሪቱ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት መፈጠሩ ይታወሳል፡፡

ምንጭ፡-ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አንፃራዊ ሰላም ሰፍኗል‼️

መንግስት የጦር መሳሪያ ሊያስፈታ ነው የሚለው ቅስቀሳ ከእውነት የራቀ መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በምዕራብ እና በማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች አንፃራ ሰላም መስፈኑንም ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

ኮሚሽኑ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው በሁለቱ ዞኖች አንፃራዊ ሰላም መታየቱን ያስታወቀው፡፡ በአካባቢው የነበረውን #አለመረጋጋት ወደ #ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለመመለስ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ክልከላ እና ሌሎች እገዳዎች ከተላለፉበት ቀን ጀምሮ በሰውም ይሁን በንብረት ላይ ይደርስ የነበረው ጉዳት መቀነሱን ገልፃል፡፡

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘላለም ልጃለም እንደጠቆሙት የፌደራል እና የክልል የፀጥታ ሀይሎች ከህብረተሰቡ ጋር እየሰሩት ባለው ተግባር በቡድን ሲፈፀሙ የነበሩ የግድያ እና የንብረት ማጥፋት ወንጀሎች ቀንሰዋል፡፡

ከእገዳው በኋላ በጥምረት በተሰራው ስራም 11 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ተናግረዋል። አሁንም አልፎ አልፎ በግለሰብ ደረጃ የሚፈፀሙ ወንጀሎች መኖራቸውንም ጠቁመዋል።
ከአሁን ቀደም ታግተው የነበሩ ግለሰቦችም ሙሉ በሙሉ መለቀቃቻን ኮሚሽነሩ አረጋግጠዋል፡፡

ከጎንደር መተማም ይሁን ከጎንደር ሁመራ የተሽከርካሪ መጓጓዣ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡ በጎንደር ከተማ ከአሁን ቀደም የጥይት ተኩስ ይሰማ ነበር ያሉት ኮሚሽነር ዘላለም እገዳው ከተደረገ ወዲህ መቀነሱን አመላክተዋል፡፡

ይህ ደግሞ የፀጥታ ሀይሉ ከማህበረሰቡ ጋር በጋራ ሆኖ በመስራቱ የመጣ ነው፤ የጎንደር ከተማ ወጣቶች ለሰላም እያሳዩ ያሉት ትብብርም የሚደነቅ ነው ብለዋል፡፡

ወንድማማች ህዝቦቹ ካለፈው ጥፋት ተምረው በጋራ ችግሮቻቸውን ለመቅረፍ እየተወያዩ መሆናቸውም ታውቋል።

እገዳ በተደረገባቸው አካባቢዎች የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ መከልከሉን ምክንያት አድርገው መንግስት የጦር መሳርያ #ሊያስፈታ ነው እያሉ ቅስቀሳ የሚያደርጉ አካላት አሉ፡፡ "ቅስቀሳው ከእውነት የራቀ ነው፤ #ብጥብጥ በመፍጠር ክልሉን ለማዳከም የታለመ ሀሳብ በመሆኑ ማህበረሰቡ በአሉባልታዎች እንዳይታለል" ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ...

በተቋሙ ውስጥ በተፈጠረ #አለመረጋጋት ሳቢያ ለሳምንታት ተቋርጦ የነበረው የመማር ማስተማር ሂደት በዛሬው ዕለት #ተጀምሯል። በትላንትናው ዕለት በግቢው ውስጥ የእርቅ ስነ ስርዓት መካሄዱ ይታወሳል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደቡብ ክልል የጎብኚ ቁጥር አሽቆልቁሏል!

በደቡብ ክልል #የሀዋሳ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተው #አለመረጋጋት የጎብኚዎች ቁጥር ማሽቆልቆሉን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው የስራ ሃላፊ እንዳሉት በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ክልሉን የጎበኙ የውጭ አገር ጉብኚዎች ቁጥር አምና ከነበረው በአራባ ዘጠኝ ሺህ ያህል ቀንሶል።

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የደቡብ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሰብለ ፀጋ አየለ እንዳሉት በክልሉ የሀዋሳ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተው አለመረጋጋት በጎብኚዎች እንቅስቃሴ ላይ የራሱን ተፅህኖ አሳድሯል።

ለአብነትም በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ወደ ክልሉ የመጡ የውጭ አገር ጎብኚዎች አምና ከነበረው በአራባ ዘጠኝ ሺህ ያህል ቀንሶ መገኘቱን ነው የቢሮ ሃላፊዋ ወይዘሮ ሰብለ ፀጋ የጠቀሱት። የቱሪዝም ዘርፈ ጥንቃቄ የሚያሻው በትንሽ ስጋት ሊደናቀፍ የሚችል መሆኑን የጠቆሙት ወይዘሮ ሰብለ ፀጋ በቀጣይ መስህቦችን መልሶ የማስተዋወቅ ስራ ያስፈልጋል ብለዋል።

በደቡብ ክልል የሆቴሎች ህብረት ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ደጀኔ ጌታቸው በከተማው ተፈጥሮ በነበረው ሁከት የጎብኚዎች ቁጥር አስከመቆም በመደረሱ በከተማው በሆቴል ዘርፍ ላይ በተሰማሩ ድርጅቶች ላይ የገበያ መቀዛቀዝ ማጋመጠሙን ተናገረዋል። ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ መንግስት ባከናወናቸው የማረጋጋት ስራዎች ዘርፉ አንፃራዊ መሻሻል እያሳየ መምጣቱን ነው ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ደጀኔ የገለጹ።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ገለቱ ገረመው በበኩላቸው የአስተዳደሩ የፀጥታ መዋቅር ከጊዚያዊ ኮማንድ ፖስትና ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት መስራት ከጀመረ ወዲህ ከተማዋ ወደ ነበረ ሰላሟ እየተመለሰች ትገኛለች ብለዋል።

Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia