TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች በሁሉም ክልሎች የሚያደርጉትን የሠላም ጉዞ ዛሬ ጀመሩ። “ስለ አገራችን #ሠላም ዝም አንልም” ያሉት የሀይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎቹ ጉዞ የአገሪቱን ሰላምና አንድነት ለማጠናከር ያለመ  መሆኑን የኢትዮጵያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስታውቋል። የሰላም ጉዞው “ሰላም ለሁላችን በሁላችን“ በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄድ ሲሆን የአገሪቱን ሰላምና አንድነት ለማጠናከርና እያንዣንባበ ያለውን ውጥረት ለማርገብ የሚያስችል ውይይት የሚካሄድበት ነው።

©ኢ.ዜ.አ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሠላም_ይስጠን!

ሠላም ይስጠን እግዜር ገናና
#ከጋረደን ጥቁር ደመና
ጊዜው ይሆን እላለሁ እኔ
የሚሆነውን ሳስተውል ባ'ይኔ

እንደው አንዳንዴ ይገርማል
አረ እንደው አንዳንዴስ ይደንቃል
እንዴት ተንዶ ፍቅራችን
ማነው ያራራቀን ከእውነት ቃል
በጊዜ አስታከን በዘመን
ራስን መውደድ አስቀድመን
ይቅርታ ራቀ ካ'ፋችን
ስናይ እየተጠማ ልባችን

አንቃን...

ይብቃችሁ በለን የፍቅር አምላክ ጌታ
አንቃን
ቅድስቷን ምድር ሠላም አውርሳት ደስታ
አንቃን
ከቁጣ አብርደህ ቀን ወዳጅ አ'ርገህ አንቀን
አንቃን

የት ይደረሳል
ምን ይወረሳል
ይብቃን
አቤቱ ..... አቤቱ
አውጣን ከመአቱ
ማረን ..... ማረን
ከክፉ አድነን

አፉ ቅዱስ ሰው ምግባሩ ሌላ
እንዳንሆን አውጣን ከዚህ #ፈተና
አፉ ቅዱስ ሰው ምግባሩ ሌላ
እንዳንሆን አውጣን እግዚኦ ማርና
.
.
ሠላም ይስጠን እግዜር ገናና
ከጋረደን ጥቁር ደመና
ጊዜው ይሆን እላለሁ እኔ
የሚሆነውን ሳስተውል ባ'ይኔ

በሀሜት በወሬ ታጅበን
በግላዊ ምቾት ተከበን
በዚች ጊዜያዊ ከንቱ ዓለም
ዘላ'ለም ቋሚ ግን አንድ የለም
ንብረት ከሰው ልጅ አብልጠን
ክፋት ምቀኝነትን መርጠን
ዘመን አለፈ ስንኖር
የፅድቁን መንገድ የሚያሳይ አጥተን

አንቃን
ይብቃችሁ በለን የፍቅር አምላክ ጌታ
አንቃን
ቅድስቷን ምድር ሠላም አውርሳት ደስታ
አንቃን
ከቁጣ አብርደህ ቀን ወዳጅ አ'ርገህ አንቀን
አንቃን
የት ይደረሳል
ምን ይወረሳል
ይብቃን
አቤቱ ..... አቤቱ
አውጣን ከመአቱ
#እግዚኦ
ማረን ..... ማረን
ከክፉ አድነን

አፉ ቅዱስ ሰው ምግባሩ ሌላ
እንዳንሆን አውጣን ከዚህ ፈተና
አፉ ቅዱስ ሰው ምግባሩ ሌላ
እንዳንሆን አውጣን እግዚኦ ማርና
አቤቱ ..... አቤቱ
አውጣን ከመአቱ
#እግዚኦ
ማረን ..... ማረን
ከክፉ አድነን

ድምፃዊ #ጎሳዬ_ተስፋዬ
#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiop
ምዕራብ ወለጋ‼️

በምዕራብ ወለጋ ዞን በነበረው #አለመረጋጋት የተዘረፉ የጦር መሣሪያዎችና ንብረት #ተመለሱ። በዞኑ ሁሉም የመንግሥት መዋቅሮችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ መደበኛ ሥራቸው መመለሳቸውም ተገልጿል።

የኮማንድ ፖስቱ ጽህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ #ደጀኔ_ገብረማርያም እንደገለጹት በዞኑ በነበረው የፀጥታ ችግር የተዘረፉ የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ንብረት ተመልሰዋል። ከነዚህም 110 ክላሽንኮቭ ጠመንጃዎች፣ 41ሽጉጦችና 20 የእጅ ቦምቦች ይገኙበታል። እንዲሁም 326 ኋላ ቀር ጠመንጃዎችና ከአራት ሺህ የሚበልጡ ጥይቶች መመለሳቸውን አስረድተዋል።

በተጨማሪም 50 በርሜል ነዳጅ፣ 14 የመንግሥትና የግል ተሽከርካሪዎችና 28 የሞተር ቢስክሌቶች መመለሳቸውን አቶ ደጀኔ ተናግረዋል።

የዞኑ ሕዝብ የተዘረፉትን የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ንብረት ለማስመለስ በተደረገው ጥረት ከፀጥታ አካላት ጋር ተቀናጅተው መንቀሳቀሱን ገልጸዋል።

በዞኑ በ20 የገጠር ወረዳዎችና ሦስት ከተሞች በተካሄዱት የሰላም ኮንፈረንሶች አንፃራዊ #ሠላም በመስፈኑ ሁሉም የመንግሥት መዋቅሮችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ወደ መደበኛ ሥራቸው መመለሳቸውን አስተባባሪው አስረድተዋል፡፡ በካማሺና የምዕራብ ወለጋ ዞኖች መካከል የሕዝብ ለሕዝብ እንቅስቃሴ መጀመሩንም አመልክተዋል፡፡

የመነ ሲቡ ወረዳ የአስተዳደርና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ምክትል ሃላፊ አቶ #ለታ_አባተ በሰጡት አስተያየት ሕዝቡና ኮማንድ ፖስቱ ባደረጉት ክትትልና ቁጥጥር የጦር መሣሪያዎቹ መመለሳቸው ለዞኑ ሰላምና ጸጥታ መከበር አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል፡፡ አሁንም ያልተመለሱትን የጦር መሣሪያዎች ለማስመለስ ተቀናጅቶ እንዲሰራ ጠይቀዋል፡፡

የመንዲ ከተማ የአስተዳርና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ #ዳኖ_ኢተፋ በበኩላቸው የተዘረፉት የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ንብረት መመለሳቸው ለሰላም ያላቸው ፋይዳው ጉልህ ነው ብለዋል። የምዕራብ ኢትዮጵያ ከዚህ ዓመት መግቢያ ጀምሮ በተከሰተው ግጭት ሰላምና ጸጥታው ታውኮ መቆየቱ ይታወሳል።

Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADAMA

"አዳማ ዛሬ ከነጋ ጀምሮ በሁሉም አቅጣጫ #ሠላም ነው። ሠላማዊ ህይወት እንድቀጥል ህዝባችን በማህበራዊ ሚድያ በማይታወቁ እና አከባቢው ላይ በማይገኙ ሰዎች የሚረጨውን የክፍፍል ወሬ ችላ በማለት ለሠላም ሊተጋ ይገባል።" ባይሳ(ቲክቫህ ቤተሰብ) ከአዳማ ፖስታቤት አከባቢ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ / ህወሓት / ከሽብርተኛ ድርጅትነት በተሰረዘበት የዛሬው የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ልዩ ስብሰባ ላይ 280 የፓርላማ አባላት ተገኝተው ነበር። ከተገኙት የፓርላማ አባላት መካከል 61 የፓርላማ አባላት ህወሓት ከሽብርተኛ ድርጅትነት መሰረዙን #ተቃውመው ድምፅ ሰጥተዋል። 5 የፓርላማ አባላት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል። በዚህም #በአብላጫ_ድምፅ ህወሓት ከሽብርተኛ…
#TPLF

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ እንዲሁም የፌዴራል መንግስትን ወክለው ከህወሓት ጋር የተደራደሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ስለ ህወሓት / TPLF ከሽብርተኛ ድርጅትነት ዝርዝር መሰረዝ በተመለከተ ምን አሉ ?

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፦

" #ሠላም ሰጥተን የምንቀበለው በመሆኑ በሁሉም ዘንድ ያሉ ቅሬታዎችን በይቅርታ በማለፍ የትግራይም ማህበረሰብ የሀገራችን አካል በመሆኑ፣ ዜጎች ማግኘት የሚገባቸውን አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ የትግራይ ሕዝብ በም/ ቤቱ መቀመጫ አግኝተው በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እኩል እንዲወስኑ እና እንዲሳተፉ ዕድል መስጠት የሚያስችል የሠላም ስምምነቱ አካል በመሆኑ የህወሓትን የአሸባሪነት ስያሜ ማንሳት ያስፈልጋል።

ሌሎች ቀሪ ስራዎች አካታች ሀገራዊ የምክክር መድረኮችን በማመቻቸት በሀገራችን ዘላቂ ሠላም ለማስፈን ይሰራል። "

ህወሓት በህ/ተ/ም/ቤ ከአሸባሪ ድርጅትነት በ61 ተቃውሞ ፣ በ5 ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል።

@tikvahethiopia