#TPLF
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ እንዲሁም የፌዴራል መንግስትን ወክለው ከህወሓት ጋር የተደራደሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ስለ ህወሓት / TPLF ከሽብርተኛ ድርጅትነት ዝርዝር መሰረዝ በተመለከተ ምን አሉ ?
አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ፦
" #ሠላም ሰጥተን የምንቀበለው በመሆኑ በሁሉም ዘንድ ያሉ ቅሬታዎችን በይቅርታ በማለፍ የትግራይም ማህበረሰብ የሀገራችን አካል በመሆኑ፣ ዜጎች ማግኘት የሚገባቸውን አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ የትግራይ ሕዝብ በም/ ቤቱ መቀመጫ አግኝተው በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እኩል እንዲወስኑ እና እንዲሳተፉ ዕድል መስጠት የሚያስችል የሠላም ስምምነቱ አካል በመሆኑ የህወሓትን የአሸባሪነት ስያሜ ማንሳት ያስፈልጋል።
ሌሎች ቀሪ ስራዎች አካታች ሀገራዊ የምክክር መድረኮችን በማመቻቸት በሀገራችን ዘላቂ ሠላም ለማስፈን ይሰራል። "
ህወሓት በህ/ተ/ም/ቤ ከአሸባሪ ድርጅትነት በ61 ተቃውሞ ፣ በ5 ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ተሰርዟል።
@tikvahethiopia